መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)
ጥያቄ፡- ሮሜ 12፡1-8 በጥንቃቄ አንብብ። ሀ) እግዚአብሔር ከእኛ የሚፈልገው መሥዋዕት ወይም መንፈሳዊ የአምልኮ ተግባር ምን ዓይነት ነው? ለ) መለወጥ ያላበት የእኛነታችን ክፍል የትኛው ነው? የመላወጡስ ውጤት ምንድን ነው? ሐ) እራሳችንን ከሌሎች ጋር እያወዳደርን በምናይበት ጊዜ ራሳችንን እንዴት መመልከት እንዳለብን ጳውሎስ የሰጠን ማስጠንቀቂያ ምንድን ነው? መ) ለእያንዳንዱ ሰው ‹የእምነትን መጠን› የሚሰጠው ማን ነው? ሠ) ቤተ ክርስቲያን ከአንድ አካል ጋር የምትመሳሰለው እንዴት ነው? ረ) በዚህ ስፍራ የተጠቀሱት ስጦታዎች ምን ያህል ናቸው? ሰ) በስጦታዎች መካከል ካለው ልዩነትና ከስጦታዎች አጠቃቀም በዚህ ክፍል ልንማር የምንችላቸው ጠቃሚ እውነቶች ምንድን ናቸው? የሮሜ 12፡1-8 መሠረት የሮሜ መጽሐፍ እግዚአብሔር ለድነት (ደኅንነት) ያለው ዕቅድ በአጭሩ የቀረበበት ነው። በዚህ መጽሐፍ የመጀመሪያዎቹ ምዕራፎች ጳውሎስ ዓለም ሁሉ በእግዚአብሔር ላይ ኃጢአት በመሥራት ምክንያት ጥፋተኛ መሆኑን አሳውቋል። ማንኛውም ሰው የሚድንበት ብቸኛው መንገድ ደግሞ በእምነት ወደ ክርስቶስ በመመለስ እንጂ የእርሱን ጽድቅ በመፈለግ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመድረስ የራሱን መንገድ በመፈለግ እንዳልሆነ አስረድቶአል። የሮሜ መጽሐፍ ከሚያተኩርባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች አንዱ እግዚአብሔር ለአይሁድ ሕዝብ የሰጠው የብሉይ ኪዳን ሕግ ከአዲሱ የእግዚአብሔር ሕዝብ ማለትም ክርስቲያኖች ጋር እንዴት እንደሚዛመድ ማጤን ነው። ጳውሎስ ሲናገር የብሉይ ኪዳን ሕግ መልካምና እግዚአብሔር የተጠቀመበት ቢሆንም እንኳ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከእንግዲህ በኋላ አስፈላጊ አይደለም ይላል። ታዲያ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን የተለማመዱትና (ለምሳሌ የአሣማ ሥጋን የማይበሉ) የራሳቸው ባሕል ያላቸው ክርስቲያን አይሁዶች፥ በአብዛኞቹ የብሉይ ኪዳን ሕግጋት ሥር ከማይተዳደሩት (ለምሳሌ የአሣማ ሥጋን ከሚበሉት) የአሕዛብ ክርስቲያኖች ጋር አብረው የሚኖሩት እንዴት ነው? (ሮሜ 12-16 ለዚህ ተግባራዊ ችግር መልስ በመስጠት ላይ ያተኩራል። ሮሜ 12፡1-2 ሮሜ 12፡1-2 ጳውሎስ መንፈሳዊ ስጦታዎችን ጨምሮ ሌሎች ትምህርቶቹን ሁሉ የመሠረተበትን አጠቃላይ የመከራከሪያ አሳብ የሚያቀርብበት ክፍል ነው። በመጀመሪያ፥ ጳውሎስ ሲናገር ክርስቲያኖች በእግዚአብሔር ምሕረት ላይ አትኩሮት ማድረግ አለባቸው ይላል። የአይሁድ ክርስቲያኖች ፈጽሞ የተላየ ታሪካዊ መሠረት ካላቸው ከአሕዛብ ጋር ተስማምተው ለመኖር ፈቃደኛ የሚሆኑት የሚያድናቸው ባሕላቸው ቅርሳቸው ወይም የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን መጠበቃቸው ሳይሆን የእግዚአብሔር ምሕረት መሆኑን ከተነገዘቡ ብቻ ነው። የዳንንና ከእግዚአብሔር ጋር ትክክለኛ ግንኙነት ያለን ማንኛችንም አብረን መኖር የምንችልበት መሠረት የእግዚአብሔር ምሕረት ነው። ከተለያየ ብሔር መውጣታችንን ለመክፋፈላችን ምክንያት ካደረግን መሠረታዊውን እውነት ዘንግተናል ማለት ነው። ከየትኛውም ባሕል ወይም ነገድ እንውጣ፥ ምንም ያህል ድሃ ወይም ሀብታም ብንሆን፥ ወንድም ሆነ ሌት እንሁን በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት እኩል እንቀርባለን (ገላ. 3፡28-29)። በዚያ ያለነው ክምሕረቱ የተነሣ ብቻ ነው። በክርስቲያኖች መካከል ስለ መንፈስ ቅዱስ እንኳ የሚደረግ የቃላት ጦርነት በእግዚአብሔር ምሕረት ላይ ከማተኮር ይልቅ በትዕቢት በራስ ጽድቅ በማጉላት ላይ ያነጣጠረ ነው። ጥያቄ፡- ሀ) በኢትዮጵያ ያሉ ክርስቲያኖች ብዙ ጊዜ የሚጋጩባቸውን ነገሮች በምሳሌነት ዘርዝር። ለ) በሚጋጩበት ጊዜ ያዳናቸውን የእግዚአብሔር ምሕረት የረሱ መሆኑን ይህ እንዴት ያሳያል? በሁለተኛ ደረጃ ፥ ጳውሎላ የሚነግረን ኃጢአተኞች ሳለን እግዚአብሔር ስላደረገው ምሕረት ስናስብ ከእኛ ዘንድ የሚጠብቀው ምላሽ ሰውነታችንን የተቀደሰ መሥዋዕት አድርጐ ማቅረብ መሆኑን ነው። መሥዋዕቶች ምን እንደሆኑ አይሁድም ሆኑ አሕዛብ ያውቁ ነበር። በብሉይ ኪዳን ሥርዓት አምልኮና አሕዛብ የአምልኮተ ጣዖት ሥርዓት መሥዋዕቶች የተለመዱ ነበር። በመሥዋዕት ውስጥ ሁልጊዜ የእንስሳት ሞት አላ ማለት ይቻላል ሰዎች በቀድሞ ዘመን እንስሳትን መሥዋዕት ያቀርቡ የነበረ ቢሆንም፥ ጳውሎስ ግን በቤተ ክርስቲያን እዲስ ዓይነት መሥዋዕት መኖሩን ገለጸ። ይህም እራሳችንን መልስን ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ማድረግ ነው። ለመሥዋዕት የሚቀርበው እንስሳ እንደሚሞት እንሞታለን ማለት አይደለም። ይልቁኑ ይህ ሥዕላዊ እገላላጽ ነው። በሮማ 6 ጳውሎስ የሚያስተምረው ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንደምንኖር ነው። ጳውሎስ ይህንኑ አባባል በሮሜ 12 ላይ በመጠቀም የሚያስተላልፍልን መልእክት፥ ስለ እኛ ለተደረገው የእግዚአብሔር ምሕረት ተመጣጣኝ ምላሽ የሚሆነው እራሳችንን ለእግዚአብሔር መልሰን ማስረከብ መሆኑን ነው። ለራሳችን የላዊ ፈቃድ መሞት አለብን። በሌላ ስፍራ ጳውሎስ በዋጋ ተገዝተናል ይላል (1ኛ ቆሮ. 6፡20)። እራሳችንን መሥዋዕት አድርገን ለእግዚአብሔር መስጠት ማለት ያለ ምንም ቅደመ-ሁኔታ ሕይወታችንን ሙሉ በሙሉ ለእርሱ እንሰጣለን ማለት ነው። አንተ ገዝተኻኛል እኔ የአንተ ነኝ በእኔ የምትፈልገውን – እድርግ። ወደ ፈልክበት ላከኝ ማለታችን ነው ዕቅዳችንን፥ ሕልማችንንና ፍላጐታችንን ሁሉ ለእርሱ ሰጠን ማለት ነው። ጳውሎስ እንደሚናገረው እራሳችንን ሕያውና ቅዱስ መሥዋዕት አድርጐ የማቅረብ ዝንባሌ «መንፈሳዊ የአምልኮ ተግባር» ነው። የአምልኮአችን፥ የዝማሬአችን፥ የስብከታችን፥ አሥራትን የመስጠታችንና መንፈሳዊ ስጦታዎችን የመጠቀማችን መሠረቱ በሙሉ እራሳችንን መሥዋዕት አድርጐ የማቅረብ ዝንባሌ መሆን አለበት። እራሳችንን ለመስጠት ካልፈለግን የምናደርጋቸው ማናቸውም ነገሮች በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት እያገኝም። ድምጻችን እስኪዘጋ ድረስ ብንዘምርም እንኳ መላ ሕይወታችንን ለእግዚአብሔር እስካልሰጠን ድረስ ቃላትን መለፍለፍ ብቻ ይሆናል። እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ያለንን ገንዘብ ሁሉ ብንሰጥም እንኳ መላ ሕይወታችንን ካልሰጠነው የምናደርገው ሁሉ ከንቱ ነው። 1ኛ ቆሮ. እንደሚያስተምረን የፍቅር መንፈስ ሊሰፍን ይገባል። ይህ የሚሆነው ደግሞ እራሳችንን ለእግዚአብሔር አሳልፈን ስንሰጥ ብቻ ነው። በሦስተኛ ደረጃ፥ ጳውሎስ የሚለው ከእግዚአብሔርና ከእኛ እጅግ ከሚለዩ ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር ሰላማዊ ግንኙነት እንዲኖረን እእምሮአችን መለወጥ አለበት። ክርስቲያኖች ከመሆናችን በፊት እናስባቸው የነበሩ ነገሮች፥ ለእኛ እጅግ ጠቃሚ የነበሩ ነገሮች፥ ይቆጣጠሩን የነበሩን ባሕላዊ ነገሮች ሁሉ አሁን መለወጥ አለባቸው። አስተሳሰባችንን የምንቀይረው እግዚአብሐር የሚፈልጋቸውን ነገሮች ለማድረግ በመፍቀድ ነው። እግዚአብሔር እንድናስባቸው የሚፈልጋቸውን ነገሮች ስናስብ፥ እግዚአብሔር አስፈላጊ ናቸው ያላቸውን ነገሮች ስናደርግ ያኔ እግዚአብሔር እንዴት እንድንመላለስ እንደሚፈልግ እናውቃለን። በሌላ አባባል ጳውሎስ እንዳለው «የእግዚአብሔርን ፈቃድ» እናውቃለን። ይህንን ስናደርግ የእግዚአብሔር መንገድና፥ «ፈቃድ መልካም ፍጹምና ደስ የሚያሰኝ» የመሆኑን እውነታ እንለማመዳለን (ሮሜ 12፡2)። ጳውሎስ በዚህ ቦታ ባይናገረውም እንኳ ሌሎች ክፍሎችን የምናጠና ብንሆን እራሳችንን ለእግዚአብሔር ማቅረብ አስተሳሰባችንንና ተግባራችንን መቀየር ስሰብአዊ ጥረት ብቻ ሊደረግ እንደማይቻል የተረዳን መሆኑን ማየት እንችል ነበር። ይልቁኑ ይህ በውስጣችን የሚሠራው የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት ነው። ጥያቄ፡– ከላይ የተጠቀሱትን ሦስት ነገሮች ብናስታውስ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከፍተኛ ስምምነት የሚኖረው እንዴትና በምን ዓይነት መንገድ ነው? ሮሜ 12፡3-8 ጳውሎስን ያሳሰበው ነገር አስተሳሰባችን የተለየ መሆን እንደሚገባው ብቻ አልነበረም። አእምሮአችን መታደስ ያለበት ተግባራችንም እንዲለወጥ ነው። ተግባራችን በኢየሱስ ክርስቶስ አካል ውስጥ የሚኖረንን የእርስ በርስ ግንኙነት ይወስናል። ጳውሎስ መንፈሳዊ ስጦታዎችን በታደሰ አእምሮ ቁጥጥር ሥር ከመኖር፥ ሰውነቱን ሕያው መሥዋዕት አድርጐ ከማቅረብ ጋር በጥብቅ ያቆራኘዋል። በዚህ ክፍል ውስጥ የሚከተሉትን እውነቶች ልብ በል። 1. መንፈሳዊ ሕይወቱና እግዚአብሔር የሰጠውን መንፈሳዊ ስጦታዎች ማወቅ የእያንዳንዱ ክርስቲያን ኃላፊነት ነው። ጳውሎስ ለክርስቲያኖች ሲናገር «እንደ ባለ አእምሮ ስለማሰብ» ተናግሯል። የዚህ ክፍል ቀዳሚ መልእክት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስለ መንፈሳዊ ስጦታዎች አጠቃቀም ጉዳይ ነው። ይህ ዐረፍተ ነገር የሚያሳየን ልንጠነቀቅባቸው የሚገቡ ሁለት በተለያየ አቅጣጫ የከረሩ አሳቦች መኖራቸውን ነው። የመጀመሪያው፥ የትዕቢት አሳብ ነው። በመታበይ ስለ ራሳችን በምናስብበት ጊዜ ለመገምገሚያ የምንጠቀመው የተሳሳተ መመዘኛን ነው። እራሳችንን ከሌሎች ከእኛ የባሱ ናቸው ብለን ከምናስባቸው ጋር እናወዳድራለን። በልባችን ትዕቢት በሚኖርበት ጊዜ የበላይነት ስሜት ያድርብናል። እኔ ወንድ ነኝ አንቺ ለት ነሽ ስለዚህ ከአንቺ እሻላለሁ። እኔ ከተማረ ቤተሰብ ሆንህ አንተ ከወዛደር ቤተሰብ ነህ። እኔ ከምርጥ ጐሳ ነኝ፤ እንተ የባሪያ ጐሳ ነህ። በዓለምም ሆነ በቤተ ክርስቲያን ፀብን የሚጋብዙ እንደነዚህ ዓይነት ዝንባሌዎች ሁሉ የሚመነጩት ክትዕቢት በሚወጣ እኔ እበልጥ እንተ ታንስ ባይነት ነው። ለላ ራሳችን ባላን በትዕቢት የተሞላ ግምት ሰዎች ሲያፋጥጡን ቁጡና ቀናተኞች ሆነን እንታያለን። ይህም ወደ ፀብና ክፍፍል ይመራናል። መንፈሳዊ አቋማችንን በመመልከት እራሳችንን ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር በማወዳደር ከእነርሱ የተሻልን እንደሆንን ካሰብን መንፈሳዊ ትዕቢት ይዞናል ማለት ነው። ወይም ስጦታዎችንንና ችሎታችንን ከሌሎች ጋር ስናወዳድር ወደ ትዕቢት ውስጥ እንገባለን። ከእከሌና ከእከሌ በተሻለ ሁኔታ ለማስተማር እችላለሁ የሚለው ብዙ ጊዜ በአእምሮኦችን ብልጭ የሚል አሳብ ነው። ማወዳደር ስንጀምር፥ እኛ ከሌሎች እንደምንቫል እራሳችንን በማሳመን ጥሩ ስሜት እንዲሰማን እናደርጋለን። በርካታ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች
መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8) Read More »
