የእግዚአብሔርን ቃል ለልጆቻችንና ለወጣቶቻችን ማስተማርና በሕይወት መንገድ መምራት አደራ የተጣለብን ታላቅ መንፈሳዊ ኃላፊነት ነው (ዘዳ 6:6-7)፡፡ ሕጻናትን በሚሄዱበት መንገድ ማሰልጠን በሸመገሉ ጊዜ እንኳ ከእርሱ እንዳይርቁ ያደርጋል (ምሳሌ 22:6)፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ለእግራችን መብራት ለመንገዳችንም ብርሃን ነው (መዝ 119:105)፡፡ በመሆኑም ከሕጻናት እስከ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ድረስ ለእያንዳንዱ የእድሜ ክልል በጥናት ላይ ተደግፈውና በታላቅ ጥንቃቄ የተዘጋጁ መንፈሳዊ ሥርዓተ ትምህርቶችን ለቤተክርስቲያን አገልጋዮች፣ ለወላጆችና ትውልድን ማነጽ ሸክማቸው ለሆነ ሁሉ ከዚህ በታች አቅርበናል፡፡ በርእሶቹ ላይ ያለውን ሊንክ (መስፈንጠሪያ) በመጫን መጽሐፎቹን በፒ.ዲ.ኤፍ. ፋይል አውርደው አልያም እዚሁ (ኦንላይን) በማንበብ እንዲጠቀሟቸው በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡
1. ዕድሜያቸው ከ 9 ዓመት በታች ላሉ ሕጻናት የተዘጋጀ ሥርዓተ ትምህርት
ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታዎችና ውርሶች ናቸው (መዝ 127:3)፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሕጻናት ወደ እርሱ ይመጡ ዘንድ እንድንተውና እንዳንከለክላቸው አዞናል (ማቴ 19:14)፡፡ ይህ በጥናት ላይ የተደገፈና በታላቅ ጥንቃቄ የተዘጋጀ ሥርዓተ ትምህርት፣ ሕጻናት ውብ በሆኑ ምስሎች በመታገዝ የአምላካቸውን ቃል በቀላሉ የሚማሩበትንና ጠንካራ መንፈሳዊ መሠረት የሚጥሉበትን ማራኪ አውድ ይፈጥራል፡፡
2. ዕድሜያቸው ከ 9-12 ዓመት ላሉ ታዳጊዎች የተዘጋጀ ሥርዓተ ትምህርት
ታዳጊዎች መንገዳቸውን በሚገባ የሚያነጹትና የሚያጠሩት እንደ እግዚአብሔር ቃል በመጠበቅ ነው (መዝ 119:9)፡፡ በዚህ ወሳኝ የእድገት ዘመን ላይ ለሚገኙ ታዳጊዎች በጥናት ላይ የተደገፈና በታላቅ ጥንቃቄ የተዘጋጀው ይህ ሥርዓተ ትምህርት፣ የእግዚአብሔርን ሕግጋት በልባቸው ውስጥ እንዲያኖሩና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ጥልቅ ሕብረት እንዲጀምሩ ያግዛቸዋል፡፡
3. ዕድሜያቸው ከ 13-18 ዓመት ላሉ ወጣቶች የተዘጋጀ ሥርዓተ ትምህርት
ማንም ሰው የወጣቶችን ዕድሜ እንዳይናቅ፣ ነገር ግን በቃል፣ በኑሮ፣ በፍቅር፣ በመንፈስ፣ በእምነትና በንግህና ለሚያምኑቱ ምሳሌ መሆን እንደሚገባቸው ቅዱስ ቃሉ ያስተምረናል (1ኛ ጢሞ 4:12)፡፡ ለዚህ የእድሜ ክልል በጥናት ላይ የተደገፈና በታላቅ ጥንቃቄ የተዘጋጀው ይህ ሥርዓተ ትምህርት፣ ወጣቶች በክርስቶስ ኢየሱስ ያለውን እውነት አጥብቀው እንዲይዙና በዘመናችን ካሉት ዓለማዊ ተጽዕኖዎች ተለይተው በቅድስና እንዲመላለሱ ያበረታታቸዋል፡፡
4. ለ2ኛ ደረጃ እና ለኮሌጅ/ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተዘጋጀ ሥርዓተ ትምህርት
የክርስቶስ ኢየሱስ በጎ ወታደር በመሆን መከራን መቀበልና በጽናት መቆም ከእያንዳንዱ አማኝ የሚጠበቅ ጥሪ ነው (2ኛ ጢሞ 2:3)፡፡ ይህ ሥርዓተ ትምህርት ተማሪዎች በካምፓስና በከፍተኛ ትምህርት አውድ ውስጥ ለሚገጥማቸው አዕምሯዊ፣ ሥነ-ምግባራዊና መንፈሳዊ ፈተናዎች ማዘጋጀትና የዲያብሎስን ሽንገላ መቃወም እንዲችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ በማስለበስ የኢየሱስ በጎ ወታደር እንዲሆኑ መርዳትን ዓላማ ያደረገ ነው (ኤፌ 6:11)፡፡
እነዚህን በጥልቀትና በጸሎት የተዘጋጁ ሥርዓተ ትምህርቶች በመጠቀም ትውልድን በእውነትና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል አብረን እናንጽ፡፡ ሌሎች ተጨማሪ የስልጠና መጽሐፎችን ማግኘት የሚሹ ከሆነ የሚከተለውን ልንክ ይጫኑ፡- የመጽሐፎችና የስልጠና ማኑዋሎች ማህደር
