የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት

በብሉይና በአዲስ ኪዳን መካከል የነበረው ዘመን

የውይይት ጥያቄ፦ ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙት ነገሮች ባለፉት 100 ዓመታት ከተፈጸሙት ድርጊቶች ጋር በጥብቅ የሚተሳሰሩ ናቸው። የምኒልክ፥ የኃይለ ሥላሴ፥ የደርግና የኢሕአዴግ የአገዛዝ ዘመናት ዛሬ በአገሪቱ ውስጥ የሚፈጸሙትን ክስተቶች በእጅጉ ይወስናሉ። የኢትዮጵያ ድንበሮች፥ የመሬት ይዞታ አመለካከቶች፥ የኦርቶዶክስና የእስልምና ሃይማኖት ግንኙነቶችና የመሳሰሉት ታሪካዊ መሠረት ያላቸው ነገሮች ናቸው፤ ስለዚህም ዛሬ የዚያን ታሪክ ፍሬ እንመገባለን። ይህም ሆኖ ዛሬ የሚከሰቱት ነገሮች ሁሉ የኢትዮጵያ ታሪክ ውጤቶች ብቻ አይደሉም። በሰፊው ዓለም ውስጥ የተፈጸሙት ነገሮችም በኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድረዋል። በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አውሮፓውያን አፍሪካን በቅኝ ለመግዛት ያካሄዷቸው ተግባራት፥ ለምሳሌ ጣሊያኖች አንዳንድ የኢትዮጵያ ክፍሎችን መግዛታቸው (ኤርትራን ጨምሮ) በዛሬዎቹ ክስተቶች ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል። በኃይለ ሥላሴና በደርግ ዘመን በሩሲያ (ሶቪየት ኅብረት) እና በአሜሪካ መካከል የነበረው የቀዝቃዛው ጦርነት ትግል ዛሬም በኢትዮጵያ ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩን ቀጥሏል። ለምሳሌ የምዕራቡ ዓለም ፈሊጥ የሆነው ፋሽን፥ ቪዲዮና የእንግሊዝኛ ቋንቋ በወጣቶቻችን ስሜትና ባህል ላይ ተጽዕኖ በማሳደር ላይ ይገኛል። በተመሳሳይ ሁኔታ፥ ከአዲስ ኪዳን ዘመን በፊትም ሆነ በአዲስ ኪዳን ዘመን በእስራኤልና በሌሎች አገሮች ውስጥ ይካሄዱ የነበሩ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን በምንገነዘብበት ጊዜ፥ ስለ አዲስ ኪዳንና ስለ ቤተ ክርስቲያን ዕድገት እጅግ ግልጽ አሳብ ይኖረናል። ክርስቶስ በእስራኤል አገር በተወለደ ጊዜ አገሪቱ በሮማውያን አስተዳደር ሥር ነበረች። ክርስቶስ ከመወለዱ ከ400 ዓመታት በፊት በእስራኤልና በአሕዛቡ ዓለም የተፈጸሙት ክስተቶችም በእስራኤልና በአይሁድ ሕዝብ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድረው ነበር። ሐዋርያው ጳውሎስ በገላትያ 4፡4-5 ላይ እንደገለጸው፦ «ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤ እንደ ልጆች እንሆን ዘንድ፥ ከሕግ በታች ያሉትን ይዋጅ ዘንድ።» ጳውሎስ ይህን ሲል ክርስቶስ ወደ ምድር መጥቶ እንዲሞትና ቤተ ክርስቲያንን እንዲመሠርት፥ በእግዚአብሔር ዕቅድ ውስጥ ሁሉም ነገር ታሪካዊ ዝግጅት ተደርጎለት እንደነበረ መግለጹ ነበር። ቤተ ክርስቲያን በጥንቱ ዓለም በፍጥነት ልታድግና በአንድ ትውልድ ዘመን ወንጌል በዚያ ደረጃ ሊስፋፋ የቻለው ለምን ነበር? መልሱን የምናገኘው እግዚአብሔር የዓለምን ታሪክ ቀድሞ ካደራጀበት ሁኔታ ነው። ምንም እንኳ ኢየሱስ ክርስቶስ በአዳምና በሔዋን፥ ወይም በዳዊት ወይም በኢሳይያስ ዘመን ወይም ዛሬ ሊመጣ ቢችልም፥ እነዚህ ሁሉ ዘመናት ከእግዚአብሔር ጥበብ አንጻር ገና ትክክል አልነበሩም። ነገር ግን በእስራኤልና በአሕዛብ አገሮች የነበረው የታሪክ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ምቹ ሲሆን እግዚአብሔር ልጁን ላከው። ይህን ጊዜ ምቹ እንዲሆን ያደረጉት ነገሮች ምን ምን ነበሩ? ይህን ጥያቄ ለመመለስ የእስራኤል ሕዝብ በ586 ዓ.ዓ. በምርኮ ከተወሰደ በኋላ በዓለም ውስጥ የተፈጸሙትን ታላላቅ ክስተቶች መመርመር ይኖርብናል። የውይይት ጥያቄ፦ ዳንኤል ምዕራፍ 7ን አንብብና ዳንኤል በራእዩ የተመለከታቸውን የተለያዩ እንስሳት ዘርዝር። እነዚህ እንስሳት ያመለከቱት የትኞቹን ታሪካዊ መንግሥታት ነበር? በባቢሎን ምርኮ ጊዜ እግዚአብሔር ለነቢዩ ዳንኤል በቀጣይ 600 ዓመታት ውስጥ በአይሁዶች ታሪክ ውስጥ ስለሚፈጸሙት ነገሮች በግልጽ ገልጦለት ነበር። በአራት እንስሳት የተመሰሉት አራት የተለያዩ የአሕዛብ መንግሥታት አይሁዶችን በየተራ እንደሚገዙ እግዚአብሔር ለዳንኤል አሳይቶታል፦ እነዚህ አራት መንግሥታት የአይሁድን ሕዝብ በየተራ ገዝተውት ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር የመሢሑንና የቤተ ክርስቲያንን መንገድ በጥበቡ ለማዘጋጀት ሲል፥ እነዚህን አረማውያን መንግሥታት በሉዓላዊ ኃይሉ ይቆጣጠር ነበር። እነዚህ መንግሥታት እያንዳንዳቸው እግዚአብሔር ለአይሁዶች በነበረው ታሪካዊ ዕቅድ ውስጥ የየራሳቸው ታላቅ ድርሻ ነበራቸው። የባቢሎን መንግሥት (626 ዓ.ዓ. – 539 ዓ.ዓ.) የውይይት ጥያቄ፦ 2ኛ ነገሥት ምዕራፍ 25ን አንብብ። አልፎ አልፎ የአሕዛብ አገሮች ከሚሠነዝሩባት ድንገተኛ ጥቃት ውጭ፥ እስራኤል ለ900 ዓመታት ያህል (ከ1400 እስከ 586 ዓ.ዓ.) ነፃ አገር ነበረች። አይሁዶች «የእግዚአብሔር ፈቃድና የጽዮን መቅደስ ሁልጊዜም ከውጭ አገሮች ጥቃት ይጠብቀናል፤ ድርጊታችንም ሆነ ማንኛውንም ጣዖት ማምለካችን ለእግዚአብሔር አሳሳቢ ጉዳይ አይደለም። እኛ የእግዚአብሔር ልዩ ሕዝብ ስለሆንን፥ ወደ ምርኮ ሊሰድደንና ሊያጠፋን ፈጽሞ አይፈልግም» ብለው በሐሰት ያስቡ ነበር። እግዚአብሔር ነቢያትን ደጋግሞ እየላከ ሕዝቡ በንስሐ ካልተመለሰ እንደሚቀጣ ቢያስጠነቅቅም ሕዝቡ ግን አልሰሟቸውም። የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነጾር ጦር በድንገት ኢየሩሳሌምን በመክበብ ከ605 እስከ 586 ዓ.ዓ. ድረስ 3 ታላላቅ ወረራዎችን አካሄደባት። በዚህ ጊዜ የይሁዳ አገር ፈጽማ ወደመች። ታላቁ የሰለሞን ቤተ መቅደስ ሙሉ በሙሉ ሲፈርስና የእንስሳት መሥዋዕቱ ሲቆም፥ ለ500 ዓመታት ያህል ያለማቋረጥ ሲካሄድ የነበረው የቤተ መቅደሱ ዘላቂ አምልኮ ተቋረጠ። የውይይት ጥያቄ፦ በባቢሎን ምርኮ ዘመን የአይሁድን ሕይወት የለወጡ 5 ታላላቅ ክስተቶች፦ የሰባ ዓመቱ የባቢሎን ምርኮ የአይሁድ ሕዝቦችን ማኅበራዊና መንፈሳዊ ሕይወት ሙሉ በሙሉ የለወጠ መለኮታዊ ሂደት ነበር። ክርስቶስ ወደ ምድር በመጣ ጊዜ የአይሁዶች አኗኗርና የአምልኮ ሁኔታ በዳዊትና በኢሳይያስ ዘመን ከነበረው ፍጹም የተለየ ነበር። በምርኮ ዘመን የተለወጡ 5 ዋና ዋና ነገሮች የሚከተሉት ነበሩ፦ የፋርስ መንግሥት (539 ዓ.ዓ. – 331 ዓ.ዓ.) የውይይት ጥያቄ፦ ዳንኤል ምዕራፍ 8ን አንብብ። የሜዶንና የፋርስ መንግሥታት ኃይልን ከማግኘታቸው ከ200 ዓመታት በፊት፥ እግዚአብሔር ቂሮስ (Cyrus) የተባለ ንጉሥ እንደሚያስነሣ ለነቢዩ ኢሳይያስ በስሙ ጠቅሶ ገልጦለት ነበር (ኢሳ. 44፡28)። ምንም እንኳ ቂሮስ እውነተኛውን አምላክ በግል ባያውቅም፥ እግዚአብሔር ግን ለአይሁድ ሕዝብ ሲል እርሱን ወደ መሪነት በማምጣት ባቢሎንን እንዲያሸንፍና ምርኮኞቹ ወደ አገራቸው ተመልሰው መቅደሱንና የኢየሩሳሌምን ቅጥር እንዲገነቡ ፈቀደ። ይህ ታላቅ ግዛት ጥምር የሜዶንና የፋርስ መንግሥት ነበር። የባቢሎን መንግሥት በሥልጣን ላይ የቆየው ለ70 ዓመታት ብቻ ሲሆን፥ የፋርስ መንግሥት ግን ለ200 ዓመታት ቆይቷል። ይህም የፋርስ መንግሥት በአይሁዶች ማኅበራዊ ሕይወትና ባህል ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ለማሳደር አስችሎታል። ፋርሳዊው ቂሮስ ሜዶንን ከፋርስ ጋር በማዋሃድ አነስተኛ የነበረችውን አገር በ550 ዓ.ዓ. ኃያል የዓለም አገር አደረጋት። ቂሮስ በ546 ዓ.ዓ. ታላቁን የሊዲያን መንግሥት ሲያሸንፍ፥ በ539 ዓ.ዓ. ደግሞ ባቢሎንን ወግቶ በማሸነፍ የፋርስ ግዛት አካል አደረጋት። ስለሆነም በአጭር ጊዜ ውስጥ ቂሮስ የፋርስን መንግሥት በምሥራቅ ከፋርስ ባሕረ ሰላጤ ጀምሮ ወደ ምዕራብ ቱርክና ወደ ደቡብ ግብጽ ድረስ ለማስፋፋት ቻለ። ይህም የፋርስን መንግሥት በዘመኑ ከነበሩት ግዛቶች ሁሉ ታላቅ አድርጎታል። የአይሁድ ታሪክ ትውፊት እንደሚለው፥ ቂሮስ ድል አድርጎ ወደ ባቢሎን በገባ ጊዜ የአይሁድ መሪዎች የእርሱ መምጣትና ስሙም እንኳ ሳይቀሩ ከ200 ዓመታት በፊት በነቢዩ ኢሳይያስ መጽሐፍ መተንበዩን በክብር አሳዩት። ቂሮስ ለአይሁዶች ልዩ አዋጅ እንዲያወጣና ወደ አገራቸው እንዲመልሳቸው እግዚአብሔር ልቡን ያነሳሳበት አንዱ ታሪካዊ ምክንያት ይህ ነበር። የቂሮስ አገዛዝ ስልት ሰዎችን በግፍ ካፈናቀሉት ከባቢሎናውያንና ከአሦራውያን ፍጹም የተለየና የለዘበ ነበር። ሰዎችን አስገድዶ ወደ ሌላ ምድር ከመስደድ ይልቅ፥ በአገራቸው በሰላም እየኖሩ ለፋርስ መንግሥት ታማኝ እንዲሆኑና ግብር እንዲከፍሉ ያበረታታ ነበር። በመሆኑም ቂሮስ በሕዝቦች ዘንድ ተወዳጅነት ያተረፉለትን ሁለት ታላላቅ ተግባራት አከናውኗል፦ በመጀመሪያው ዙር በዘሩባቤል አማካይነት 50,000 የሚሆኑ አይሁዶች ብቻ ነበሩ ወደ ኢየሩሳሌም የተመለሱት። ይህ የሚያሳየው አብዛኞቹ አይሁዶች በባቢሎን ምድር የተደላደለ የንግድ ሕይወት ይመሩ ስለነበር፥ ኋላቀርና በኢኮኖሚም ወደ ወደመችው የኢየሩሳሌም ምድር ለመመለስ ፈቃደኞች እንዳልነበሩ ነው። ይህ ሁኔታ ዛሬ በምዕራቡ ዓለም (ለምሳሌ በአሜሪካ) የሚኖሩ የብዙ አገሮች ስደተኞች ወደ ገጠሪቱና ወደ ደከመችው አገራቸው ተመልሰው ለመኖር ከማይፈልጉበት ምድራዊ ምቾት ጋር ይመሳሰላል። ይህ የዓለም ፍቅርና ምቾት አብዛኞቹ አይሁዶች እግዚአብሔር ለአብርሃምና ለዘሮቹ ተስፋ ወደ ገባላቸው የተቀደሰች ምድር እንዳይመለሱ ከለከላቸው። የውይይት ጥያቄ፦ የሳምራውያን መነሳትና የቤተ መቅደሱ ግንባታ ውጊያ አነስተኛው የአይሁድ ቅሬታ ወደ ይሁዳ ምድር ሲመለስ፥ ቀዳሚ ተግባራቸው የይሖዋ ቤተ መቅደስ ዳግም ግንባታ ነበር። ብዙም ሳይቆይ ግን ከባድ የፖለቲካ ተቃውሞ ተነሣባቸው። በአሦራውያን አስተዳደር ዘመን በነበረችው በሰሜኑ የእስራኤል ክፍል (ሰማርያ) ከአሦር ንጉሥ የመጡ አሕዛብና የቀሩት እስራኤላውያን ተጋብተው በመውለዳቸው ምክንያት ከፊል አይሁዳዊና ከፊል አሕዛብ የሆኑ ሕዝቦች ተፈጥረው ነበር። እነዚህ ሰዎች በአዲስ ኪዳን ዘመን ሳምራውያን (Samaritans) ተብለው ተጠርተዋል። ሳምራውያን አይሁዶች መቅደሱን መልሰው ለመገንባት መነሳታቸውን ሲያዩ፥ መጥተው በሥራው አብረው መሳተፍና መተባበር እንደሚፈልጉ አስታወቁ። ነገር ግን በዘሩባቤል የሚመሩት እነዚህ የተመለሱት አይሁዶች፥ ሳምራውያኑ በቁጥር በልጠው እንዳይቆጣጠሯቸውና ንጹሑ የእግዚአብሔር አምልኮ

በብሉይና በአዲስ ኪዳን መካከል የነበረው ዘመን Read More »

በብሉይና በአዲስ ኪዳን ውስጥ የሚገኙ ተመሳሳይ ጭብጦች

እግዚአብሔር ሁልጊዜ ሰዎች ከእርሱ ጋር ኅብረት የሚያደርጉበትን መንገድ ያዘጋጃል። ብዙውን ጊዜ ኃጢአትን ከሚንቁ (ቀልለው ከሚመለከቱ) ሰዎች በተቃራኒ፥ እግዚአብሔር ቅዱስና ጻድቅ ነው። ስለሆነም በሰዎች ኃጢአትና ዓመፃ ላይ በጽድቅ ይፈርዳል። እግዚአብሔር አዳምና ሔዋን ኃጢአት በሚሠሩበት ጊዜ እንደሚሞቱ ቀድሞ ነግሯቸው ነበር (ዘፍጥ. 2፡16-17)። ይህ ሞት ሁለት ታላላቅ ገጽታዎች ነበሩት፦ ደኅንነት (ድነት) ሙሉ በሙሉ ከእግዚአብሔር እንጂ ከሰው አይደለም። እኛ እግዚአብሔርን እንደመረጥነው ወይም የደኅንነትን መብት የሚያስጨብጥ አንድ ትክክለኛ የጽድቅ ሥራ እንዳደረግን በምናስብበት ጊዜ፥ በልባችን ውስጥ የመንፈሳዊ ኩራት ምልክት እናሳያለን። ለምሳሌ ለድሆች መመጽወት፥ በራስ ጥረት ጥሩ ክርስቲያን ለመሆን መሞከርና የመሳሰሉት በራሳቸው ሰውን ሊያድኑ አይችሉም። ስለሆነም ብዙውን ጊዜ «የዳንሁት በክርስቶስ ስላመንሁ ነው» እንላለን፤ ይህ ፍጹም እውነት የሆነ አባባል ነው። ነገር ግን እኛ ከማመናችንም በፊት የደኅንነትን መንገድ ቀድሞ ያዘጋጀልን እግዚአብሔር ነው። የደኅንነት ብቸኛ ምንጩ እግዚአብሔር እንጂ ሰው አይደለም። አዳምና ሔዋን ኃጢአትን ከፈጸሙ በኋላ ከእግዚአብሔር ጋር የነበራቸውን ግንኙነት በራሳቸው ጥረት ለማደስ የሚያስችል ምንም ዓይነት ሌላ መላ አልነበራቸውም። ስለዚህም ነው እግዚአብሔር ራሱ የግድ ለእነርሱ አንድን የማዳን ሥራ ማድረግ የነበረበት። በሰው ልጆች ታሪክ ሁሉ ውስጥ ሰዎች የራሳቸውን የደኅንነት መንገድ በተለያየ ሃይማኖት ለማግኘት ሲሞክሩ ኖረዋል። ነገር ግን ሰዎች ከእርሱ ጋር የሚታረቁበትን እውነተኛ መንገድ ሊያሳይ የሚችለው ፈጣሪ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ቡድሂስቶች፥ ሂንዱዎች፥ ሙስሊሞችና ሌሎችም የሃይማኖት ወገኖች ሕግን በመጠበቅና ጥሩ ሰዎች በመሆን የእግዚአብሔርን ይቅርታ ለማግኘት በሥጋዊ ኃይል ይጥራሉ። ብዙ ክርስቲያኖችም ሳያውቁ ይህንኑ የተሳሳተ የይቅርታ መንገድ ይከተላሉ። አንዳንድ ሰዎች ብዙ ስለጸለዩ፥ ሳያቋርጡ ወደ ቤተ ክርስቲያን ስለሄዱ ወይም አሥራታቸውን ስለሰጡ ብቻ እግዚአብሔር ኃጢአታቸውን እንዲሁ ይቅር የሚል ይመስላቸዋል። ይህ ግን የተሳሳተ ድርጊትና አመለካከት ነው። እኛ ሰዎች በፈጣሪያችን ላይ ስላመፅን፥ በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት ምን ማድረግ እንዳለብን ሊነግረን የሚገባው ፈጣሪያችን ራሱ ነው። እግዚአብሔር እኛን እንዴት ይቅር ብሎ እንደሚያድነን የመወሰን ሥልጣን ለሰው ልጅ አልተሰጠም። ብሉይ ኪዳንም ሆነ አዲስ ኪዳን፥ እግዚአብሔር ራሱ የይቅርታንና የዕርቅን በር በክርስቶስ በኩል ስለሚከፍትበት መለኮታዊ መንገድ ብቻ ይናገራሉ። የውይይት ጥያቄ፦ ክርስቲያኖችን ጨምሮ ብዙ ሰዎች ለእግዚአብሔር አንድ መልካም ነገር በማድረግ ብቻ ይቅርታን ሊያገኙ እንደሚችሉ የሚያስቡበትን ሁኔታ ግለጽ። ይህ አመለካከት በክርስቶስ መስቀል ፊት የተሳሳተ የሚሆነው ለምንድን ነው? መለኮታዊው የመሥዋዕት ሥርዓት (ሕይወት ለሕይወት) እግዚአብሔር በሕዝቡ መካከል ቅዱስ ኅብረትን ለመመሥረት የተጠቀመበት ብቸኛው መንገድ በመሥዋዕት ነው። በዕብራውያን 9፡22 ላይ፥ «ደም ሳይፈስ ስርየት የለም» የሚል ቃል እናነባለን። እግዚአብሔር ፍጹም ቅዱስና ጻድቅ አምላክ በመሆኑ፥ በኃጢአተኞች ላይ በጽድቅ ሳይፈርድ እንዲሁ በደፈናው (ያለ ደም) ይቅር አይላቸውም። ነገር ግን እግዚአብሔር በፍቅርና በምሕረት የተሞላ አምላክ በመሆኑ፥ ለይቅርታ የሚሆን መለኮታዊ ምትክ መንገድ ያዘጋጅላቸዋል። እግዚአብሔር እንስሳት ለኃጢአት መሥዋዕት ይሆኑ ዘንድ በብሉይ ኪዳን በመደንገግ፥ «ሕይወት ለሕይወት» የሚል ታላቅ መንፈሳዊ መርሕ መሥርቷል። ፩. የብሉይ ኪዳን ጊዜያዊ መሥዋዕቶች በመጀመሪያ እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ዘመን በኃጢአተኞች ምትክ የሚሰዉ ጊዜያዊ እንስሳትን ሥርዓት አዘጋጅቷል (ዕብ. 10፡1-14)። እግዚአብሔር ለአዳምና ለሔዋን የቆዳን ልብስ በማልበስ፥ ለኃጢአት መሸፈኛ የእንስሳት መሥዋዕት ማቅረብ እንዳለባቸው መጀመሪያ አስተምሯቸዋል። የአዳምና የሔዋን ልጆች የሆኑት ቃየንና አቤል ይህንን የአምልኮ ሥርዓት ያውቁ ነበር (አቤልም በመንፈስ የታዘዘው ለዚህ ነው)። በተቀረው የብሉይ ኪዳን ታሪክ ሁሉ ቅዱሳን ሰዎች እግዚአብሔርን ያመልኩ የነበረው የእንስሳትን መሥዋዕት በማቅረብ ነበር። ሰዎች በሕይወት ይኖሩ ዘንድ በነርሱ ምትክ የእንስሳቱ መሞት የግድ ነበር። ምንም እንኳን እንስሳት በራሳቸው ኃጢአት ባይሠሩም፥ በሰዎች ምትክ በመሞት የኃጢአትን ዋጋ በምሳሌነት ለመሸከም ተገደው ነበር። ይህንን የምትክ ሞት (Substitutionary death) ለማሳየት፥ መሥዋዕቱን የሚያቀርበው ሰው እጆቹን በሚሠዋው እንስሳ ራስ ላይ በመጫን ኃጢአቱን በግልጽ ይናዘዝ ነበር (ዘፀ. 29፡10፤ ዘሌዋ. 16፡21)። እግዚአብሔር በመገናኛው ድንኳንና በሰለሞን ቤተ መቅደስ የአምልኮን ሥርዓት በሙሴ በኩል ሲመሠረት፥ ሥርዓቱ ሁሉ እነዚህን ደማዊ መሥዋዕቶች እንዲያካትት አድርጓል (ዘሌዋ. ምዕ. 1-5)። ፪. የክርስቶስ ፍጹምና ዘላለማዊ መሥዋዕት ነገር ግን የእንስሳት ደም ለኃጢአት ችግርና ለዘላለም ይቅርታ ጊዜያዊ ጥላና መፍትሔዎች ብቻ ነበሩ። እግዚአብሔር አብ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ፍጹምና የመጨረሻው መሥዋዕት አድርጎ ለመላክ ከዘላለም ዓለም አቅዶ ነበር። ለዚህ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ክርስቶስ «ዓለም ሳይፈጠር ጀምሮ ቀድሞ እንደተመረጠ» የሚናገረው (1ኛ ጴጥ. 1:19-20)። የብሉይ ኪዳን መሥዋዕቶች ሁሉ ወደ ክርስቶስ ፍጹም መሥዋዕትነት የሚያመለክቱ ጥላዎች ነበሩ። ምንም ዓይነት ኃጢአት ፈጽሞ ባይገኝበትም፥ የእግዚአብሔር ዘላለማዊ ልጅ የሆነው ክርስቶስ በእኛ ምትክ በመስቀል ላይ ሞተ። በመስቀሉ ላይ ክርስቶስ የሰዎችን ሁሉ ኃጢአት በአንድነት ተሸከመ። ከአዳምና ከሔዋን ጀምሮ በታሪክ ውስጥ እስከሚኖሩት የመጨረሻዎቹ አማኞች ድረስ ይህን የማዳን ሥራ ፈጸመ (ዕብ. 9፡26-28)። ለዚህም ነው እርሱ «የእግዚአብሔር በግ» የተባለው (ዮሐ. 1፡29)፤ እንዲሁም «እኔ መንገድ፥ እውነትና ሕይወት ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም» ያለው (ዮሐ. 14፡6)። ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ለሰዎች ሁሉ የሚሆን መሥዋዕትን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አቀረበ (ዕብ. 9፡26)። ለሰው ልጆች የራሱን መለኮታዊ ሕይወት ሰጠ። ጳውሎስ እንዳለው፥ «እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።» (2ኛ ቆሮ. 5፡21)። የእውነተኛ ደኅንነት መለኮታዊ “ቅመሞች” እግዚአብሔር ሰዎች እንደገና ከእርሱ ጋር ቅዱስ ኅብረት እንዲመሠርቱ ዕድል ይሰጣቸዋል። እግዚአብሔር ሰዎች ከእርሱ ጋር የሚታረቁበትን መንገድ በጸጋ ቢያዘጋጅም፥ ማንንም በግድ አያስገድድም። ምርጫው የሰዎቹ ነው። በዓመፃችንና በኃጢአታችን ልንቀጥል ወይም ሰው ሠራሽ የሃይማኖት መንገዶቻችንን ልንከተል እንችላለን፤ ወይም ደግሞ እግዚአብሔር ያዘጋጀውን የክርስቶስን መሥዋዕት በእምነት ተቀብለን ከአምላካችን ጋር ልንታረቅ እንችላለን። እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ከሁለቱ አንዱን መንገድ የመምረጥ ነጻነት ቢሰጥም (ማቴ. 7፡13-14)፥ እነዚህ ሁለት መንገዶች ወዴት እንደሚወስዱን መለኮታዊውን ፍጻሜ ግን ልንቀይር አንችልም። ስለሆነም የዓመፀኝነትንና ሰውን ያማከለ የሃይማኖት አምልኮ ከመረጥን፥ የዘላለምን ፍርድ እንደምንቀበል እግዚአብሔር በቃሉ ያስጠነቅቀናል (ዮሐ. 8፡24፤ 12፡46-48)። ነገር ግን የእርሱን የደኅንነት መንገድ ከተቀበልን ልጆቹ እንደምንሆን (ዮሐ. 1፡12)፥ የዘላለምን ሕይወት እንደምናገኝና (ዮሐ. 3፡16)፥ ለዘላለም በበረከቶቹ ደስ እየተሰኘን ከእርሱ ጋር በክብር እንደምንኖር ይነግረናል (ራእይ 21-22)። ወንጌሉን በምንመሰክርበት ጊዜ በአብዛኛው ይህንን እንደ ቀላል ውሳኔ ብቻ እንመለከተዋለን፤ «በክርስቶስ እመንና ዳን» እንላለን። ምንም እንኳን ይህ ቀላል አሳብ እውነት ቢሆንም፥ እግዚአብሔርን ለመከተል በምንመረጥበት ጊዜ ልንገነዘባቸው የሚገቡንን ሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች አንዳንድ ጊዜ ይሰውርብናል። በመልካም ወጥ ውስጥ የተለያዩ ቅመሞች እንደሚጨመሩ ሁሉ፥ እምነታችንም እውነተኛና ፍሬያማ እንዲሆን ከተፈለገ አያሌ የተለያዩ መንፈሳዊ ልምምዶችን ማካተት አለበት። የሚከተሉት ለእውነተኛ ደኅንነት ኑሮ የሚያስፈልጉ ዋና ዋና መለኮታዊ “ቅመሞች” ናቸው፦ ሀ. ትሕትና የኃጢአት ሁሉ ማዕከል ትዕቢትና ዓመፅ ነው። ሔዋን ኃጢአትን በፈጸመች ጊዜ፥ ድርጊቷ «የራሴን መንገድ በመምረጥ የምፈልገውን አደርጋለሁ፤ ለእግዚአብሔርም አልገዛም» የሚል የትዕቢት መንፈስ ነበር። ኃጢአትን በምንሠራበት ጊዜ ሁሉ ለእግዚአብሔርና ለመንገዶቹ ከመገዛት ይልቅ፥ በራስ ወዳድነት እየተመላለስን የራሳችንን ሥጋዊ ክብርና ምቾት ለመጠበቅ እንሻለን። የውይይት ጥያቄ፦ ባለፈው ሳምንት በሕይወትህ የተገለጡትን ድካሞችና ኃጢአቶች በልብህ አስብ። ትዕቢት፥ ዓመፅና ራስ ወዳድነት የእነዚህ ድርጊቶች ስውር ምንጭ ሊሆኑ የቻሉት እንዴት ነው? መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ከፍ ከፍ የሚያደርገን ራሳችንን በፊቱ ስናዋርድ ብቻ እንደሆነ በተደጋጋሚ ይናገራል (ያዕ. 4፡6፥ 10፤ 1ኛ ጴጥ. 5፡5-6)። እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤ ትሑታንን ግን ጸጋን ይሰጣቸዋል (ኢሳ. 2፡12)። ስለሆነም ደኅንነትን ለማግኘት ወደ እግዚአብሔር በምንመጣበት ጊዜ ሊኖረን የሚገባው የመጀመሪያው “ቅመም”፥ ለራሳችን ሥጋዊ ጥቅም ሳይሆን ለእግዚአብሔር ክብር ለመኖር ቁርጥ ውሳኔ ማድረግ ነው። ፍጡር ለፈጣሪው ፍጹም የመገዛትን አመለካከት ሊያሳይ ይገባል። በልባችን ውስጥ የትዕቢትና የዓመፅ ጽናት ካለ እውነተኛ የደኅንነት ደስታ ሊኖረን አይችልም። ለ. ንስሐ መጥምቁ ዮሐንስ «ንስሐ ግቡ» በማለት እየሰበከ ነበር የመጣው (ማቴ. 3፡2)። ጌታ ክርስቶስም አገልግሎቱን በንስሐ ጀምሯል (ማቴ. 4፡17)። ጴጥሮስም በጰንጠቆስጤ ዕለት በነበረው መጀመሪያ ስብከቱ ሰዎች ንስሐ እንዲገቡ አሳስቧቸዋል (የሐዋ. 2:38)። ስለሆነም ከእግዚአብሔር ጋር ዕርቅ

በብሉይና በአዲስ ኪዳን ውስጥ የሚገኙ ተመሳሳይ ጭብጦች Read More »

የብሉይና አዲስ ኪዳናት ዐበይት ጭብጦች

አንድ የልቦለድ መጽሐፍ ለማንበብ ትፈልጋለህ እንበል። በዚህን ጊዜ የመጽሐፉን የመጀመሪያ ምዕራፍ ብቻ እንዳነበብህ የታሪኩን አጀማመር ልታውቅ ትችላለህ፤ ታሪኩ እንዴት እንደተጠናቀቀ ግን ልታውቅ አትችልም። ከእያንዳንዱ ምዕራፍ አንዳንድ ገጽ ብታነብ ደግሞ ስለ ታሪኩ አጠቃላይ አሳብ ይኖርሃል፤ ነገር ግን በመጽሐፉ ውስጥ የሚገኙትን ክንዋኔዎች በትክክል ልትረዳ አትችልም። ወይም ደግሞ የመጽሐፉን ሁለተኛ ክፍል ብቻ ብታነብ ደግሞ፥ አንዳንድ ነገሮች ለምን በዚያ መንገድ እንደተጻፉ ለማወቅ የተለያዩ ጥያቄዎችን ማንሣት ትጀምራለህ። የውይይት ጥያቄ፦ መጽሐፍ ቅዱስ «የእግዚአብሔር ታሪክ ነው»። ይህ ታሪክ እግዚአብሔር ስለ ራሱ፥ ስለ ሰው ልጆችና በሁለቱ መካከል ስላለው ግንኙነት የተናገረበት እውነተኛ ታሪክ ነው። የሚያሳዝነው ታዲያ የእግዚአብሔርን ታሪክ በአግባቡ የሚያነቡ ብዙ ክርስቲያኖች አለመኖራቸው ነው። መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል እንዲነበብ በሚፈልገው መንገድ በማንበብ ፈንታ፥ እነርሱ የሚወዷቸውን ክፍሎች ብቻ ያነባሉ። ከዚህም የተነሳ ብዙ ክርስቲያኖች እጅግ ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችን ገለል አድርገው ይተዋሉ። ይህም ስለ እግዚአብሔርና ከሰዎችም ጋር ስላለው ግንኙነት ግራ የተጋባ ግንዛቤ ውስጥ እንዲገቡ ያደርጋቸዋል። አዲስ ኪዳን እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር ስለሚያደርገው ግንኙነት መንፈስ ቅዱስ የሚሰጠን የመጨረሻው መለኮታዊ ትምህርት ነው። መደምደሚያ እንደ መሆኑ መጠን፥ እጅግ አስፈላጊ የሆነ የታሪኩ ክፍል ነው። እግዚአብሔር ከልጆቹ ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት ለማወቅ ከፈለግን በአዲስ ኪዳን ውስጥ የሚገኙትን 27 መጻሕፍት በሚገባ መረዳት አለብን። በዚህ ጥናታችን በአዲስ ኪዳን ውስጥ የሚገኙትን ዐበይት ትምህርቶች በሙሉ ለመረዳት እንሞክራለን። በተጨማሪም፥ መንፈስ ቅዱስ ለአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ሊያስተላልፍ የፈለገውን መልእክት እንዲገልጥልን እየተማጠንን እያንዳንዱን መጽሐፍ አጠር አጠር አድርገን እንመለከታለን። የእግዚአብሔርን ቃል ማጥናት ብቻ ሳይሆን ዛሬ በሕይወታችን ተግባራዊ ማድረግ ስላለብን፥ የአዲስ ኪዳንን እውነቶች ወስደን ከሕይወታችን ጋር ለማዛመድ እንጥራለን። እግዚአብሔር በሚፈልገው መንገድ ልባችን ከእርሱ ጋር እንዲዛመድ ሳናደርግ ዝም ብለን ስለ እግዚአብሔር ማጥናቱ ምንም ፋይዳ የለውም። ስለሆነም፥ ቃሉን በምናነብበት ጊዜ ሳሙኤል እንዳለው፥ «ባሪያህ ይሰማልና ተናገር» ልንል ይገባል (1ኛ ሳሙ. 3፡9-10)። ለጥናቱ የሚረዱ መመሪያዎች ቀጥለህ የጥያቄዎቹን መልስ በደብተር ላይ ጻፍ። የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ-ቃላት ከሌለህ ለጥናትህ ስለሚረዳህ መግዛት ይኖርብሃል። አዲሱ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉምና የእንግሊዝኛ መጽሐፍ ቅዱስ ካሉህ ለጥናትህ ተጠቀምባቸው። የእያንዳንዱን ዕለት ትምህርት በአንድ ቀን ለማጠናቀቅ ሞክር። አንዳንዱ ትምህርት ከሌሎቹ ስለሚረዝም፥ ከሳምንታዊ ስብሰባው በፊት ጥናትህን ለማጠናቀቅ በቂ ጊዜ መመደብ ይኖርብሃል። በትምህርቶቹ ውስጥ አያሌ የማጣቀሻ ምንባቦች አሉ። «አንብብ» ተብሎ የተጻፈባቸውን ጥቅሶች የግድ ማንበብ ይኖርብሃል። እንደዚህ የሚል ማሳሰቢያ የሌለባቸውን ግን ጊዜ ካለህ ብቻ ልታነባቸው ትችላለህ። የመግቢያ ትምህርቶቹ ስለ አዲስ ኪዳን አንዳንድ ጠቃሚ አሳቦችን ያስጨብጡሃል። ምንም እንኳ እነዚህ አሳቦች አዲስና አስቸጋሪ ቢሆኑብህም፥ ለመረዳት ግን የተቻለህን ጥረት አድርግ። ከዚህ ጥናት ዓላማዎች አንዱ ተማሪው አዲስ ኪዳንን ሙሉ በሙሉ እንዲያነብ መርዳት ነው። ስለሆነም፥ ተማሪው እንዲያነብ የተጠየቀውን ክፍል በሙሉ ማንበብ አለበት። ከእያንዳንዱ ጥናቶች ጋር ተያይዘው የቀረቡት ጥያቄዎች ምን ያህል ግንዛቤህን ለመመዘን የቀረቡ በመሆናቸው ጊዜ ሰጥተህ ሥሪያቸው። (ማስታወሻ፦ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የቀረቡት ታሪኮች ሁሉ መንፈሳዊ እውነቶችን ለማብራራት የተዘጋጁ እንጂ፥ እውነተኛ ገጠመኞች አይደሉም።) የብሉይና የአዲስ ኪዳናት ዐበይት ጭብጦች መጽሐፍ ቅዱስ በዓለም ውስጥ ከሚገኙ መጻሕፍት ሁሉ እጅግ ልዩ መጽሐፍ ነው። መጽሐፍ ቅዱስን ጽፎ ለመጨረስ 1500 ዓመታት ፈጅቷል። ከኦሪት ዘዘፍጥረት እስከ ኦሪት ዘዳግም ያሉት የመጀመሪያዎቹ መጻሕፍት የተጻፉት በ1400 ዓ.ዓ አካባቢ ነበር። የመጨረሻው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የሆነው የዮሐንስ ራእይ የተጻፈው በ100 ዓ.ም አካባቢ ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ የ66 ልዩ ልዩ መጻሕፍት ስብስብ ሲሆን፥ የደራስያኑም ቁጥር ቢያንስ 45 ይሆናል። ከእነዚህ መጻሕፍት መካከል አንዳንዶቹ የታሪክ መጻሕፍት ሲሆኑ፥ ሌሎቹ ደግሞ ግጥሞችን ያካተቱ ናቸው። ለግለሰቦችና ለአብያተ ክርስቲያናት የተጻፉ ደብዳቤዎችም ይገኙባቸዋል። መጽሐፍ ቅዱስ በረጅም ጊዜ ውስጥና በብዙ ደራስያን አማካይነት የተጻፈ በመሆኑ ብዙ የሚጋጩ አሳቦችና ስሕተቶች ይኖሩታል ብለን ልናስብ እንችላለን። ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስን በጥንቃቄ በምናጠናበት ጊዜ በውስጡ የሚገኙ መጻሕፍት ሁሉ የሚያስደንቅ የሃሳብ ስምምነት እንዳላቸው እንገነዘባለን። ምንም እንኳ እግዚአብሔር በሰዎች ተጠቅሞ መጽሐፍ ቅዱስን ቢጽፍም፥ ዋናው የመጽሐፍ ቅዱስ ደራሲ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ግልጽ ነው (2ኛ ጴጥ. 1፡20-21)። በ1500 ዓመታት ውስጥ በተጻፉት 66 መጻሕፍት መካከል ያለውን ፍጹም ስምምነት ሊያብራራ የሚችለው ይህ መለኮታዊ እውነት ብቻ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በጥሩ ሁኔታ እንደተሠራ የጋቢ ጥለት፥ በውስጡ ከዳር እስከ ዳር እየተጠላለፉ የእግዚአብሔርን ታሪክ የሚያስተሳስሩ ታላላቅ ጭብጦች አሉት። መጽሐፍ ቅዱስን በአግባቡ ለመረዳት እነዚህን ጭብጦች ማወቅ አለብን። የውይይት ጥያቄ፦ ስለ ብሉይና ስለ አዲስ ኪዳን ባለህ ዕውቀት መሠረት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙት እነዚህ ጭብጦች ምን ምን እንደሆኑ ግለጽ። ፩. እግዚአብሔር ሁሉን ነገር የሚቆጣጠር ልዑል ፈጣሪ ነው መጽሐፍ ቅዱስ የሚጀመረው፥ «በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ» በማለት ነው (ዘፍጥ. 1፡1)። የመጽሐፍ ቅዱስ ዐቢይ ጭብጥ፥ የእግዚአብሔር ባሕርይና የዓላማው መገለጥ ነው። እግዚአብሔር የአጽናፈ ዓለሙ (ዩኒቨርስ) ማዕከል፥ ሁሉንም ነገር ወደ ሉዓላዊ ዕቅዱ የሚመራ፥ ሁሉን አዋቂና ሁሉን ቻይ አምላክ ነው። ምንም እንኳ በአጽናፈ ዓለሙ አማካይነት ስለ እግዚአብሔር አንዳንድ ነገሮችን ማወቅ ብንችልም፥ እግዚአብሔር ማን እንደሆነ ትክክለኛውን ማረጋገጫ የምናገኘው ከዘፍጥረት እስከ ራእይ በሚገኙት ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ነው። እግዚአብሔር ልጁን ወደዚህ ምድር በላከው ጊዜ ራሱን ፍጹም አድርጎ እንደገለጠ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። ሰዎች ክርስቶስን በሚመለከቱበት ጊዜ እግዚአብሔር አብን በማየት፥ የእግዚአብሔርን ባሕርይ ይበልጥ ፍጹም በሆነ መንገድ ይረዱታል (ዮሐ. 14፡8-11፤ ዕብ. 1፡1-3)። ይህም ሆኖ፥ ብዙዎች ነገሩ አልገባቸውም ነበር። አንዳንድ ጊዜ ሰይጣን እግዚአብሔር እኛን ማገልገል ይገባዋል ብለን እንድናስብ ያደርገናል። ሰው ከምንም ነገር በላይ ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው ስለሚገባ፥ እግዚአብሔር ፍላጎታችንን ማሟላት አለበት ብለን እናስባለን። መጽሐፍ ቅዱስ ግን እግዚአብሔር የእውነት ሁሉ ማዕከል እንደሆነና ሰዎች እግዚአብሔርን ማገልገል እንደሚገባቸው በግልጽ ያስተምረናል። እርሱ ፈጣሪ፥ እኛ ደግሞ ፍጥረቱ ነን። ጳውሎስ እንዳለው፥ እኛ የተፈጠርነው እርሱን ለማክበር ነው (1ኛ ቆሮ. 10፡31፤ ኤፌ. 1፡11-12፤ 3፡20-21)። መጽሐፍ ቅዱስ አሁን ያለውን ነገር ሁሉ እግዚአብሔር እንደ ፈጠረና እርሱ ብቻ ያልተፈጠረ አምላክ እንደሆነ ያስረዳል። በዘፍጥረት 1-2 ላይ ስለ መጀመሪያው ፍጥረት እናነባለን። ዘፍጥረት 3 ስለ ሰው ልጅ ዓመፅ ቢገልጽም፥ እግዚአብሔር ግን የፈጠረውን ዓለም ለመቆጣጠር አልተሳነውም። ነገሮችን ከፍና ዝቅ እያደረገ ታሪክን በመቆጣጠር ላይ ይገኛል (ኢሳ. 5፡26፤ 40፡15-17)። እግዚአብሔር የነገሥታትን ልብ ያንቀሳቅሳል (ምሳሌ 21፡1)። እርሱ የታሪክን ፍጻሜ ወስኗል። እግዚአብሔር በእርሱ ላይ የሚያምፁትን ሁሉ እንዴት እንደሚያንበረክካቸው ከራእይ መጽሐፍ እንመለከታለን። ይህንን ዓለም ከፍጻሜ ካደረሰ በኋላ፥ ፈቃዱ ብቻ የሚከናወንበትን አዲስ ዓለም ፈጥሯል። እግዚአብሔር የሁሉም ተቆጣጣሪና የነገሮችንም ፍጻሜ የወሰነ አምላክ በመሆኑ፥ ወደፊት የሚከሰተውን መለኮታዊ ዕቅድ ልንለውጥ አንችልም። ነገር ግን የዘላለማዊ መንግሥቱ አካል እንሆን ዘንድ ፈቃዳችንን ከፈቃዱ ጋር እንድናስማማ ያሳስበናል። አሁን የምናደርገው ውሳኔ የዘላለም ዕጣ ፈንታችንን ይወስነዋል። የውይይት ጥያቄ፦ ምንም ያህል ሁኔታዎች ክፉ ቢመስሉም እንኳ፥ እግዚአብሔር ሁልጊዜ ነገሮችን እንደሚቆጣጠር ማስታወስ አስፈላጊ የሚሆነው ለምንድን ነው? ፪. እግዚአብሔር ከሰው ጋር ያለው ግንኙነትና የዓለም በኃጢአት መበከል የትም ብንሄድ ዓለም በኃጢአት ተበክላ እናገኛታለን። በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን የሚገድሉ በሽታዎች አሉ። እንደ ድርቅና ጎርፍ የመሳሰሉ የተፈጥሮ አደጋዎችም የእግዚአብሔርን ፍጥረት ሰላም በመንሳት ላይ ናቸው። በአገሮች፥ በሕዝቦችና በጎሳዎች መካከል መከፋፈልና ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት በሺህ የሚቆጠሩ ወገኖች ሕይወት እየተቀጠፈ ነው። እነዚህ ሁሉ ከየት መጡ? መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሁለተኛው የኃጢአት ጭብጥም ይነግረናል። በዘፍጥረት 3 ላይ እንደተናገረው፥ እነዚህ ሁሉ ችግሮች የተከሰቱት በአዳምና በሔዋን ኃጢአት ምክንያት ነው። ጳውሎስ በሮሜ 5፡12-13 ላይ እንደተናገረው፥ ከአንዱ ሰው ከአዳም የተነሳ ኃጢአትና ሞት በሰዎች ሁሉ ላይ ደረሰ። ይህ በአዳምና በሔዋን የተጀመረው የዓመፀኛነት መንፈስ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሁሉ ተንጸባርቋል። የአዳምና የሔዋን ልጆችም የኃጢአትን መንገድ ተከተሉ፤ ከዚያም ቃየን አቤልን ገደለ። ከጥፋት ውኃ በፊት ዓለም ሁሉ በዓመፅ ስለተበላሸች የጥፋት ውኃ ጠርጎ ወሰዳቸው። የተመረጡት

የብሉይና አዲስ ኪዳናት ዐበይት ጭብጦች Read More »

ኦሪት ዘፍጥረት

የኦሪት ዘፍጥረት መግቢያ ጥያቄ፥ «ዘፍጥረት» የሚለውን ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ውስጥ ተመልከት። ስለ ጸሐፊው፥ ስለ ተጻፈበት ዓላማና ስለ መጽሐፉ አስተዋጽኦ ያገኘኸው ነገር ምንድን ነው? ከብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ ልናጠናቸውና ልንረዳቸው ከሚገቡን እጅግ ጠቃሚ መጻሕፍት አንዱ ዘፍጥረት ነው። ብዙ ክርስቲያኖች በዘፍጥረት ውስጥ የሚገኙትን ታሪኮች ቢያውቁም እንኳ አብዛኛዎቹን ጥልቅ ትምህርቶች ግን አያጠኗቸውም። የዚህ መጽሐፍ ዓላማ ዘፍጥረትን በጥልቀት ማጥናት ባይሆንም፥ በመጽሐፉ ውስጥ የምናገኛቸውንና የተተኮረባቸውን ዋና ዋና የሥነ- መለኮት ትምህርቶች ለመመልከት እንሞክራለን። የኦሪት ዘፍጥረት ስያሜ ለኦሪት ዘፍጥረት የተሰጠው ስም የመጣው ከግሪኩ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ ዘፍጥረት የሚለው ቃል በመጽሐፉ የመጀመሪያ ሁለት ምዕራፎች ላይ እግዚአብሔር ነገሮችን ሁሉ ስለ መፍጠሩ በሚናገረው መሠረተ አሳብ ላይ ያተኩራል። እንደግሪኩ ስያሜ መጽሐፉ የሚያተኩረው በተለያዩ ነገሮች «አጀማመር» ላይ ነው። ጥያቄ፥ ከዚህ ቀደም ኦሪት ዘፍጥረትን በግል ካነበብከው በመነሣት አጀማመራቸው በመጽሐፉ የሆነ የተለያዩ ነገሮችን ዘርዝር። በዘፍጥረት ውስጥ የቀረውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍላችንን ለመረዳት በጣም ጠቃሚ የሆኑ የብዙ ነገሮችን አጀማመር እንመለከታለን። ለምሳሌ፡- የፍጥረታትን አጀማመር እንመለከታለን። እግዚአብሔር ፈጣሪ ስለሆነ እርሱ የፍጥረታት ሁሉ ባለቤትና ተቆጣጣሪ ነው። በዘፍጥረት ውስጥ የወንድና የሴትን፥ የጋብቻን፥ የኃጢአትን፥ ስለ ኃጢአት የሚቀርብ መሥዋዕት፥ የተለያዩ ከተሞችን፥ የነፍስ ግድያን፥ የሥልጣኔ፥ የነገድና የጎሣዎችን፥ የተለያዩ ቋንቋዎችን አጀማመር፥ ወዘተ እናያለን። አብዛኛዎቹም በኦሪት ዘፍጥረት በመጀመሪያዎቹ 11 ምዕራፎች ውስጥ ይገኛሉ። ከብሉይ ኪዳን ታሪክ አንጻር ስናየው ግን በጣም አስፈላጊ ክስተት የሆነው የእስራኤል ሕዝብ አጀማመር ነው። የኦሪት ዘፍጥረት አብዛኛው ክፍል (ምዕራፍ 12-50) ስለ እስራኤል ሕዝብ አጀማመር የሚናገር ነው። ይህም ሕዝብ እግዚአብሔር የመረጠው ነው። የኦሪት ዘፍጥረት ጸሓፊ ጥያቄ፡ሀ) የኦሪት ዘፍጥረት ጸሐፊ እንደሆነ በይበልጥ የሚገመተው ማን ነው? ለ) እንደ አንዳንድ ምሁራን አስተሳሰብ ዘፍጥረት የተጻፈው እንዴት ነው? ። ሐ) ሙሴ የሚለውን ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ተመልክተህ ስለ ሕይወቱ በአጭሩ ጻፍ። መ) ኦሪት ዘፍጥረትን ለመጻፍ ሙሴ የተለየ ብቃት ያገኘው እንዴት ነው? በዘመናት ሁሉ ሙሴ ዘፍጥረትን ጨምሮ የፔንታቱክ ጸሐፊ መሆኑ ይገመት እንደነበር ቀደም ሲል ተመልክተናል። ጸሐፊው ሙሴ እንደሆነ በዘፍጥረት ባይጠቀስም እንኳ የቀሩቱ የፔንታቱክ መጻሕፍት ግን ሙሴ እንደጻፈው ያሳያሉ። አምስቱ የሙሴ መጻሕፍት በሙሉ እንደ አንድ ክፍል ስለሚቆጠሩ፥ ዘፍጥረትንም የጻፈው ሙሴ መሆን አለበት። ሙሴ ዘፍጥረትን አልጻፈውም ብለን የምናምንበት አንዳችም ምክንያት የለም። ይልቁንም ሙሴ በዘፍጥረት ውስጥ የምናገኘውን ነገር ለመጻፍ በተለየ ሁኔታ ተዘጋጅቶ ነበር። ለአይሁድ በብሉይ ኪዳን ዘመን ከነበሩ እጅግ ታላላቅ ሰዎች አንዱ ሙሴ ነበር። ከግብፅ ባርነት አውጥቶ ወደ ተስፋይቱ ምድር የመራቸው ሙሴ ነበር። ለእስራኤል ሕዝብ ሕግን ለመስጠት እግዚአብሔር የተጠቀመበት ሰው ሙሴ ነበር። አይሁድ የመጀመሪያዎቹን አምስት የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ዘወትር «የሙሴ ሕግ» ብለው የሚጠሩት ስለዚህ ነበር። ሙሴ ነቢይ፥ ካህን፥ ሕግ ሰጭ፥ ፈራጅ፥ አማላጅ፡ እረኛ፥ ተአምራት አድራጊና የአይሁድ ሕዝብ የፖለቲካ መሥራች ነበር። ሙሴ የተወለደው ሌዊ ከተባለው የእስራኤል ነገድ እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ወላጆች ነበር። ነገር ግን የተወለደው እጅግ አስቸጋሪ በሆነ ጊዜ ነበር። የእስራኤል ሕዝብ በግብፃውያን ባርነት ሥር ወድቆ፥ ግብፃውያንም እስራኤላውያን የሆኑ ወንዶች ልጆች ሁሉ በሚወለዱበት ጊዜ እንዲገደሉ ሕግ ያወጡበት ጊዜ ነበር። ግብፃውያን ይህንን ያደረጉበት ምክንያት እስራኤላውያን በቁጥር እጅግ ብዙ ይሆኑና ከዚህ ቀደም ሐይክሶሳውያን እንዳደረጉት ሊገለብጡን ይሆናል ብለው ፈርተው ስለ ነበር ነው። በእምነታቸው ጽናት የሙሴ ወላጆች ሊደብቁት እስከሚችሉበት ጊዜ ድረስ አሳደጉት። ሊደብቁት ከማይችሉበት ጊዜ ላይ ሲደርሱ ግን እግዚአብሔር እንደሚታደገው በመተማመን በዓባይ ወንዝ ዳር አስቀመጡት። የግብፅ መሪ የነበረው የፈርዖን ሴት ልጅ ባገኘችው ጊዜ ወደ ቤቷ ወስዳ እንደ ግብፃዊ አሳደገችው። የሙሴ ሕይወት እያንዳንዳቸው 40 ዓመታት በሆኑ ሦስት ክፍሎች ሊከፈል ይችላል። 40 ዓመታት በግብፅ – በፈርዖን ቤት ውስጥ፡- በእነዚህ 40 ዓመታት ውስጥ ሙሴ በሁለት የተለያዩ ባሕሎች ትምህርት አደገ። በመጀመሪያ፥ በአይሁድ ሃይማኖትና ከአባቶች በተወረሰ ትምህርት አደገ። ይህ የሆነው ለጊዜውም ቢሆን ያሳድጉት ዘንድ ኃላፊነቱ በተሰጣቸው በእኅቱ ማርያምና በእናቱ ነበር (ዘጸ. 2፡7-10)። ሁለተኛ፥ ሙሴ እንደፈርዖን ልጅ ሆኖ የማደግ ዕድል በማግኘቱ በዚያ ዘመን ሊኖር የሚችለውን ትምህርት ሁሉ ቀስሞ ነበር (የሐዋ. 7:22 ተመልከት)። ግብፅ በዚያን ዘመን እጅግ የሠለጠነች አገር ስለነበረች፥ ሙሴ እጅግ የተማረ ሰው ነበር ማለት ነው። እስጢፋኖስ ሙሴ «በቃልና በሥራው ሁሉ የበረታ ሆነ» ይላል። ሙሴ ይህንን ሁሉ ትምህርት በመቅሰሙ፥እግዚአብሔር በኋላ ዘፍጥረትን ጨምሮ የመጀመሪያዎቹን አምስት የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት እንዲጽፍ ተጠቀመበት። አይሁዳውያን ከነበሩት ወላጆች ስለ ወገኖቹ እንደሰማ ጥርጥር የለውም። ወደ ኋላ ተመልሶ እስከ አዳምና ሔዋን፥ ኖኅ፥ በተለይም አብርሃም፥ ይስሐቅ፥ ያዕቆብና ዮሴፍ ያለውን የሕዝቡን አፈ ታሪኮችን ያውቅ ነበር። በግብፅ ታላላቅ ቤተ መጻሕፍት ስለአለፈው ጊዜ የሚናገሩ ታሪኮችን የማየት ዕድልም ገጥሞት ነበር። ይህ ታሪክ የዓለምን አፈጣጠር፥ በኖኅ ዘመን የነበረውን የጥፋት ውኃ፥ የዓለምን መከፋፈል ወዘተ የሚጨምር ነው። ሙሴ ዘፍጥረትን ለመጻፍ በጣም ብቁ ሰው ነበር። በእነዚህ 40 ዓመታት ሙሴ እስራኤላዊ እንጂ ግብፃዊ እንዳልሆነ አልዘነጋም ነበር። ካደገ በኋላ ኣንድ ውሳኔ ለማድረግ ተገደደ። ውሳኔውስ ዓለማዊ የሆነ ዕድል ባለበት በፈርዖን ቤት ለመቆየት? ወይስ እግዚአብሔር የተለዩ የቃል ኪዳን ሕዝቡ አድርጎ ከመረጣቸውና አሁን ባሮች ከሆኑት ሕዝብ ጋር ማበር ይሆን? ጥያቄ፥ ዕብ. 11፡24-26 አንብብ። ሀ) ሙሴ ያደረገው ምርጫ ምን ነበር? ለ) ዛሬ ይህንን ምርጫ ማድረግ ያለብን እንዴት ነው? ምሳሌ ስጥ። ሙሴ እስራኤልን ከግብፅ ባርነት ነፃ ለማውጣት የተመረጠ መሪ እንደነበር ተረድቶ ነበር (የሐዋ. 7፡25)። ነገር ግን የእግዚአብሔርን ጊዜ ከመጠበቅ ይልቅ በራሱ ኃይል ነፃ ሊያወጣቸው ሞከረ። ስለዚህ አንድን ሰው ከገደለ በኋላ የፈርዖንን ቤት ትቶ ከግብፅ መሸሽ ግድ ሆነበት። 40 ዓመታት በምድያም ምድረ በዳ፡- በሰው አመለካከት የሚቀጥሉት 40 ዓመታት የባከኑ ይመስላሉ። ሙሴ በጣም የተማረ ሰው ቢሆንም በግ ማገድ ጀመረ። በእግዚአብሔር አመለካከት ግን በሙሴ ሕይወት ይህ በጣም አስፈላጊ ጊዜ ነበር። ምድረ በዳውና በግ ማገዱ እግዚኣብሔር ሙሴን የእስራኤል ሕዝብ መሪ ወይም እረኛ ለማድረግ የሚያስተምርበት ቦታና ሥራ ነበር። በምድረ በዳው እግዚአብሔር በትምህርቱና በችሎታው የነበረውን ትምክሕት በማስወገድ ሙሴን ትሑት አደረገው። ሙሴ ትሑት ከሆነና እግዚአብሔር በሕይወቱ እንዲሠራ በእርሱ ብቻ ከታመነ፥ ታላቅ ሥራን ይሠራ ዘንድ የእግዚአብሔር መገልገያ ለመሆን ተዘጋጅቷል ማለት ነው። ጥያቄ፥ ሀ) እግዚአብሔር ሙሴን በኃይል ይገለገልበት ዘንድ ትሑት ሊያደርገው ያስፈለገበት ምክንያት ምንድን ነው ብለህ ታስባለህ? ለ) የእግዚአብሔርን ሕዝብ በምንመራበት ጊዜ በችሎታችንና በእውቀታችን ስለ መመካት ይህ ምን ያስተምረናል? ሐ) ከሙሴ ለ40 ዓመታት በምድረ በዳ መኖር ስለ ቤተ ክርስቲያን አመራር ምን ለመማር ትችላለህ? 40 ዓመታት የእግዚአብሔርን ሕዝብ ከግብፅ ወደ ከነዓን መምራት፡ አንድ ቀን እግዚአብሔር ሙሴን በሚቃጠል ቁጥቋጦ ውስጥ ተገናኘውና ወደ ግብፅ ተመልሶ እስራኤላውያንን ከግብፅ ነፃ በማውጣት እንዲመራቸው ጠራው። ሙሴ ወደ ግብፅ ለመመለስ ቢፈራም፥ በመጨረሻ ከእግዚአብሔር ጋር ተስማማ። እግዚአብሔር ሙሴን በፈርዖን ፊት ስለ እርሱ ሆኖ ይናገር ዘንድ ተገለገለበት። ሙሴ ያደረገው በፈርዖን ቤተ መንግሥት በመሆኑ በፈርዖን ዘንድ እውቅናን ማትረፉ አያጠራጥርም። አሥር ታላላቅ ተአምራዊ መቅሠፍቶችን በግብፅ ላይ በማምጣት እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ነፃ አውጥቶ በሙሴ አማካይነት 40 ዓመታት በምድረ በዳ መራቸው። በእነዚህ 40 ዓመታት ውስጥ እግዚአብሔር ሙሴን ፊት ለፊት ተገናኘው። እግዚአብሔር ለሙሴ ከዘጸአት እስከ ዘዳግም ድረስ የተጻፈውን ሕግ ሰጠው። ሙሴን ኦሪት ዘፍጥረትን፥ ዘጸአትን፥ ዘሌዋውያንን፥ ዘኁልቁንና ዘዳግምን እንዲጽፍ እግዚአብሔር ተጠቅሞበታል። ይህ ሁሉ ቢሆንም እንኳ ሙሴ ለእግዚአብሔር ስላልታዘዘ ወደ ተስፋይቱ ምድር እንዳይገባ ታገደ (ዘኍ. 20፡1-13)። ሕዝቡን እስከ ከነዓን ድንበር ድረስ አደረሳቸው። የተስፋይቱን ምድር በተራራ ጫፍ ላይ ሆኖ ከተመለከታት በኋላ ሞተ። ጥያቄ በቤተ ክርስቲያን መሪዎች ሕይወት ውስጥ እግዚአብሔር እንዴት ኃጢአትን አክብዶ እንደሚያየው ይህ ምን ያስተምረናል? የኦሪት ዘፍጥረት ታሪክ ቅደም ተከተልና አስተዋጽኦ ጥያቄ፥ የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት ዘፍ. 2፡4፤ 5፡1፤ 6፡9፣ 10፡1፤ 11፡10፤ 11፡27፤

ኦሪት ዘፍጥረት Read More »