አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ የመረጣቸውን አበክሮ ይጠራቸዋል። 

This entry is part 75 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ባለፉት ሁለት ቀናት እግዚአብሔር ለደኅንነቱ የጥሪ ቃል ይመልሱ ዘንድ ሰዎችን እንደሚጠራ ተገንዝበናል። ነገር ቀን ሰዎች ከኃጢአታቸው የተነሣ በራሳቸው ፈቃድ የእግዚአብሔርን ጥሪ ሳይቀበሉ ቀሩ። ነገር ቀን እግዚአብሔር አንዳንድ ሰዎች ጥሪውን ሳይቀበሉ ቢቀሩም ለሌሎች ደግሞ ምሕረቱን ይሰጣል። እግዚአብሔር በሉዓላዊ ምርጫው ምሕረትን ለመስጠት ወንዶችንም ሴቶችንም ወደ ራሱ ይጠራቸዋል። ጥሪውም እርሱን ሰምተው ንስሐ ገብተው በማመን ለጥሪው ቃል መልስ እንዲሰጡ ነው። ይህ ጥሪ በዚህ ሳምንት በትምህርት አንድ ላይ ካጠናነው አጠቃላይ ጥሪ የተለየ ነው። ሰዎች ደኅንነቱን እንዲቀበሉ እግዚአብሔር ለሰዎች የሚያስተላልፈው አጠቃላይ ጥሪ የእግዚአብሔር የወንጌል ጥሪ ወይም አጠቃላይ ጥሪ ተብሎ ይታወቃል። ነገር ገን እግዚአብሔር በሉዓላዊ ሥልጣኑ የሚመርጣቸውና ምሕረቱን የሚሰጣቸው ሌላ ጥሪ ይቀበላሉ። ይህ ጥሪ ከአጠቃላይ ጥሪ ይለያል። ይህኛው ጥሪ ኃይለኛ ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ ሰዎች ለእግዚአብሔር የወንጌል ጥሪ መልእክት መልስ እንዲሰጡ የሚያደርገና በልባቸው ውስጥ የሚሠራ ጥሪ ነው። አንዳንድ ጊዜ ይህ ኃይለኛ ጥሪ የእግዚአብሔር «ውጤታማ ጥሪ» ለደኅንነት ይባላል። ምክንያቱም ሰዎች ከልባቸው የእግዚአብሔርን ጥሪ እንዲቀበሉ ስለሚያደርግ ነው።  1. ለደኅንነት «ውጤታማ ጥሪ» አለ።  1.1 እውነተኛና ዳግም የተወለዱ ክርስቲያኖች «ተጠሩ» ይባላል።  ጥያቄ፡- ሮሜ 1፡6-7 አንብቡ። የሮማ ክርስቲያኖች እንዴት ላሉ ሁለት ጉዳዮች ተጠሩ?  ጥያቄ፡- 1ኛ ቆሮንቶስ 1፡2፥9 አንብቡ። በቆሮንተስ የምትገኝ ቤተ ክርስቲያን እንዴት ላሉ ሁለት ጉዳዮች ተጠራች?  ጥያቄ፡- ገላትያ 1፡15-16 አንብቡ። ሀ) ጳውሎስ ወደ ምን ተጠራ? ለ) ፊልጵስዩስ 3፡14 እንብቡ። ጳውሎስ ወደ ምን ተጠራ?  ጥያቄ፡– ኤፌሶን 1:8 አንብቡ። የኤፌሶን ክርስቲያኖች ወደ ምን ተጠሩ?  ጥያቄ፡- 1ኛ ተሰሎንቄ 2፡12 አንቡ። የተሰሎንቄ ምእመናን ወደ ምን ተጠሩ?  ጥያቄ፡- 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡12 አንብቡ። ጢሞቴዎስ ወደ ምን ተጠራ?  ጥያቄ፡- ዕብራውያን 3፡1 አንብቡ። ቅዱሳን ወንድሞች ምንን ተካፈሉ?  ጥያቄ፡- 1ኛ ጴጥሮስ 2፡9 አንብቡ። ሀ) እኛ የማን ነን? ለ) እኛ ከምን ተጠራን? ሐ) ወደ ምን ተጠርተን ነበር?  በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደምንመለከተው እግዚአብሔር ሰዎችን ውጤታማ በሆነና ሰዎችን ወደ ደኅንነት ሊያመጣ በሚችል መንገድ ይጠራቸዋል። በመጀመሪያ፥ በእውነት ዳግመኛ የተወለዱ ክርስቲያኖች ወደ ደኅንነቱ በረከት «የተጠሩ» ተብለው ይታወቃሉ። ጳውሎስ በሮሜ 1፡6-7 ውስጥ ሲናገር፥ የሮማ ክርስቲያኖች ቅዱሳን እንዲሆኑና ወዲያውም የክርስቶለ እንዲሆኑ መጠራታቸውን ይገልጻል። ይህ ጥሪ ተራ ጥሪ አይደለም። ነገር ግን ጥሪው የሮሜን ክርስቲያኖች ቅዱሳን የሚያደርግ ውጤታማ ጥሪ ነበር። በዚህም የኢየሱስ ክርስቶስ እንዲሆኑ ያደረጋቸው ጥሪ ነው፡ እንደዚሁም ሐዋርያው በ1ኛ ቆሮንቶስ 12፥ 9 ውስጥ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ቅዱሳን እንዲሆኑ የተጠሩ መሆናቸውንና እንዲሁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ኅብረት እንዲኖራቸው ጥሪ መቀበላቸውን ይገልጻል። ይህ ጥሪ ለርማ ክርስቲያኖች ተራ ጥሪ አልነበረም። ጥሪው በእግዚአብሔር ፊት ቅዱሳን ያደረገና ከኢየሱስም ጋር ኅብረት እንዲኖራቸው ያስቻለ ጥሪ ነው። እንዲሁም በኤፈሶን 1፡18 ጳውሎስ ስለ ኤፌሶን አማኞች ሲናገር፥ ለወደፊቱ ተስፋና ውርስ የተጠሩ መሆናቸውን ያሳስባል። ይህ ለኤፌሶን ምእመናን የቀረብ ጥሪ ወደ ፊት የሚያገኙትን ሰማያዊ ውርስ የሚያበስር ውጤታማ ጥሪ ነበር። በ1ኛ ተሰሎንቄ 2፡12 ጳውሎስ፥ የተሰሎንቄ አማኞች ወደ እግዚአብሔር መንግሥትና ክብር የተጠሩ መሆናቸውን ይናገራል። ለእነዚህ ለተሰሎንቄ ምእመናን የቀረበ ጥሪ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት አመጣቸው። እንደዚሁም ጳውሎስ በ1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡12 ውስጥ ጢሞቴዎስ ለዘላለም ሕይወት መጠራቱን ነግሮታል። ይህ ለጢሞቴዎስ የቀረበ ጥሪ፥ የዘላለምን ሕይወት የሰጠው የእግዚአብሔር ሥራ ነው። ቀጥሎም በገላትያ 1፡15-16 ጳውሎስ፥ ኢየሱስ እንደ ገለጠለት የተጠራ መሆኑን ያስረዳል። በፊልጵስዩስ 3፡14 ላይ ጳውሎስ ከሰማይ የሚሰጠውን ሽልማት ለመቀበል የተጠራ መሆኑን ይናገራል። ለጳውሎስ የቀረበለት ጥሪ ኢየሱስን እንዲያውቀው ከማድረጉም በላይ የሰማይንም ስጦታ አረጋገጠለት፡ በዕብራውያን 3፡1 ቅዱሳን ወንድሞች የሰማይን ጥሪ መቀበላቸውንና ይህም ጥሪ ከሰማይ የመጣና ወደ ሰማይ የሚያደርሳቸው መሆኑን ያስገነዝባል። ደሞም በ1ኛ ጴጥሮስ 2፡12 ውስጥ ጰጥርስ ሲናገር አማኞች የእግዚአብሔር ሰዎች ናቸው፥ እነርሱም ከመንፈሳዊ ጨለማ ወደ እግዚአብሔር ብርሃን ተጠርተዋል ይላል። በእነዚህ የተለያዩ ማስረጃዎች አማካይነት ግልጽ ሆኖ ከቀረበው ሁኔታ እንደምንገነዘበው፥ የእግዚአብሔር ጥሪ በእያንዳንዱ ሰው ሕይወት ውስጥ የመዳንን በረከት የሚያመጣ ውጤታማ ጥሪ ነው።  1.2 የእግዚአብሔር ጥሪ ከእግዚአብሔር ጋር ወደአለው የጽድቅ ስፍራ ይመራል።  ጥያቄ፡- ሮሜ 8:30 አንብቡ። ሀ) አስቀድሞ ስለተወሰኑ ሰዎች እውነቱ ምንድን ነው? ለ) ለለተጠሩት ሁሉ ያለው እውነት ምንድን ነው?  ሁለተኛው መንገድ ሰዎችን ወደ ደኅንነት የሚጠራ ውጤታማ ጥሪ ሲኖር እንደዚሁም ሁልጊዜ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ አድርጎ ለሚያቆም ወደዚያ የሚመራ ጥሪ አለ። ሮሜ 8፡28 እግዚአብሔር አስቀድሞ የመረጣቸውን የልጁን መልክ እንዲላሉ ወሰነ ይላል። ሮሜ 8፡29 በተጨማሪ አስቀድ የመሰናቸውን ጠራቸው፤ የጠራቸውንም አልደታቸው፥ ያጸደቃቸውንም አከበራቸው ይላል። እግዚአብሔር ምሕረቱን ሊሰጣቸው የመረጣቸው ሁሉ . የእግዚአብሔርን ውጤታማ ጥሪ ይቀበላሉ፥ ለእግዚአብሔር በፈቃዳቸውና በችሎታቸው በእምነት መልስ እንዲሰጡ ያደርጋቸዋል። የተጠሩት ሁሉ ስለ ከበሩና በእግዚአብሔር ፊትም ጻድቃን ስለሆኑ፥ የእግዚአብሔር ጥሪ ውጤታማ መሆኑን እንገዘባለን። በሮማ 8፡29 ውስጥ እግዚአብሔር ያቀረበው ጥሪ ሰምተው የሚቀበሉት በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ሆነው እንዲገኙ ዋስትና የሚሰጥ ጥሪ ነው። 1.3 አንዳንዶች የዳኑት ብቻ የሚቀበሉት የእግዚአብሔር ጥሪ አለ።  ጥያቄ፡ 1ኛ ቆሮንቶስ 1፡23-24፥ 26-28 አንብቡ። ሀ) የእግዚአብሔር ጥሪ ወደየት ይመራል? ለህ ይህንን ጥሪ የተቀበሉ ብዙዎች ናቸው ወይስ ጥቂቶች?  ሦስተኛው መንገድ የምንመለከተው ጥሪ ሰዎችን ወደ እግዚአብሔር የሚያመጣ ጥሪ አለ፡፡ ይህም እግዚአብሔር ለሰዎች ሁሉ ከሚያቀርበው ጥሪ ጋር ሲመዛዘን ጥቂቶች ብቻ የሚቀበሉት ጥሪ ነው። በ1ኛ ቆሮንቶስ 1፡23 28 ውስጥ እግዚአብሔር የጠራቸው የቆሮንቶስ አማኞች ብቻ የእግዚአብሔርን ኃይልና ጥበብ የተቀበሉ መሆናቸውን ጳውሎስ ይነግረናል። ይህ ጥሪ የተላለፈው ለሰዎች ሁሉ ሳይሆን፣ በኅብረተሰቡ ዘንድ ደካሞችና ሞኞች ተብለው ለተመደቡት ለጥቂቶች ብቻ ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር ኃይሉንና ጥበቡን ለማሳወቅ በእነዚህ ጥቂቶቹ ውስጥ ይሠራል። ስለዚህ የእግዚአብሔር ጥሪ፥ ስለ ኢየሱስ ሞትና፥ ትንሣኤ፥ ማለትም አብዛኛው የዓለም ክፍል የሞኝነትና የደካማነት መልእክት አድርጎ የቆጠረውን ለተቀበሉት ነው።  1.4 የእግዚአብሔርን ውጤታማ ጥሪ የሚቀበሉ ሁሉ ወደ ክርስቶስ ይመጣሉ።  ጥያቄ፡– ዮሐንስ 6፡44 አንብቡ። ሀ) ማንኛውም ሰው ወደ ክርስቶስ እንዲመጣ ምን መደረግ አለበት? ለ) ዮሐንስ 6፡37 አንብቡ። በእዚአብሐር ለኢየሱስ ከተሰውት መካከል ስንቶቹ ወደ ክርስቶስ ይመጣሉ? ደግሞስ እርሱ ስንቶቹን ይቀበላል?  ጥያቄ፡- ሉቃስ 14:16-23 ያለውን ምሳሌ አንብቡ። በእውነት ወደ ግብዣው እነማን መጡ (ቁጥር 21-23)?  አራተኛው መንገድ፥ እግዚአብሔር ሰዎች ወደ እርሱ እንዲመጡ ለማድረግ የሚያቀርበው ውጤታማ ጥሪ ብቻ ሰዎችን ወደ ክርስቶስ ያመጣል። ስለሆነም ጥሪውን የሚቀበሉ ሁሉ ወደ እርሱ ይመጣሉ። ኢየሱስ በዮሐንስ 6 ውስጥ ሲናገር፥ ማንም ቢሆን በእግዚአብሔር በኩል ወደ ክርስቶስ ይመጣል ይላል፡ አብ የሳበው ብቻ ወደ ክርስቶስ መምጣት ይችላል። ሰዎች በአብ ወደ ክርስቶስ ሊሳቡ የሚችሉት በእርሱ ውጤታማ ጥሪ አካይነት ነው። ይህን ጥሪ የተቀበሉ ሁሉ ጥሪውን ተቀብለው ሊመልሱና ወደ ክርስቶስ ዘንድ ሊመጡ፥ እርሱም ሊቀበላቸው ይችላል።  ሰዎች ለክርስተስ ጥሪ ምላሽ እንዲሰጡ የእግዚአብሔር ጥሪ ይሠራል፥ እንደዚሁም ሰዎች ክርስቶስን እንዲቀበሉ ያደርጋል። ኢየሱስ ይህንን በሉቃስ 14 ምሳሌ ውስጥ ጠቅሶታል። አንድ ሰው ብዙ ሰዎች ወደ ቀብዣው እንዲመጡ ጠራ። ነገር ግን ከተጠሩት ሰዎች አብዛኛዎቹ ሳይመጡ ቀሩ። ከዚህ የተ የግብዣው ባለቤት ሌሎች ሰዎችን ለመጥራት ተገደደ። ቁጥር 23 ላይ እንደሚለው የግብዣው ጌታ በጎዳና ላይ የነበሩ ሰዎች መጥተው እንዲጋበዙ አስገደዳቸው ይላል። በመጀመሪያ ወደ ግብዣው የተጠሩ ሁሉም አልመጡም ነበር። ነገር ግን በመጨረሻው ላይ ወደ ቀብዣው የመጡት ሁሉ ወደ የብዣው ለመምጣት ፍላጎት እንደነበራቸው ተደርገው እንዲገቡ ሆኑ።  እዚህ ላይ ማስታወስ ያለብን የእግዚአብሔር ጥሪ ብቻ በራሱ ሰዎችን ሊያድን የማይችል መሆኑን ነው። ስለዚህ የእግዚአብሔር ጥሪ የሚመጣው በወንጌሉ አማካይነት ነው። ይህን የወንጌል ቃል የሰሙ መስማታቸውን በንስሐና በእምነት ማረጋገጥ አለባቸው። ወንጌልን ተቀብሎ ይህን በመሰለ መንገድ ስማት ስለ መግለጥ ወይም ስለ ማረጋገጥ በሚቀጥለው ሳምንት ዘርዘር አድርገን እናጠናለን። በመሠረቱ ግን ሰዎች ጥሪውን መቀበላቸው ጥሪውን ተገንዝበው የደረሳቸው ጥሪ ልባቸውን የነካ ለመሆኑ ስሜታቸውን በነፃ እንዲገልጹና የእግዚአብሔርን የማዳን በረከቶች እንዲያገኙ ያደርጋቸዋል።  ጥያቄ፦ 2ኛ ተሰሎንቄ

እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ የመረጣቸውን አበክሮ ይጠራቸዋል።  Read More »

እግዚአብሔር ለጥቂቶች ምሕረቱን ሊሰጥ ይመርጣል 

This entry is part 74 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

በትናንትናው ትምህርታችን እግዚአብሔር በዓለም ያሉ ሰዎች ሁሉ ደኅንነቱን እንዲቀበሉ አጠቃላይ ጥሪ እንደሚያቀርብ አጥንተናል። ነገር ን በዓለም ያሉ ሰዎች ኃጢአት ስለ ሠሩ፣ በኃጢአት ስለ ታወሩ፣ የኃጢአት ባሪያዎች ስለሆኑ፣ በኃጢአታቸው ስለ ሞቱና እንዳሻቸው ስለሆኑ እግዚአብሔር የሰጣቸውን የደኅንነት መብት እንደ ናቁ ተመልክተናል። ነገር ግን የእግዚአብሔርን የደኅንነት ስጦታ ቸል ከሚሉት መካከል ለጥሪው ጆሮአቸውን የመስጠት ዝንባሌ ያላቸውን እግዚአብሔር እንደሚመርጥም አስተውለናል። በሮሜ 9 ውስጥ እግዚአብሔር የመረጣቸውን፣ «የተስፋ ልጆች» ሲል እንደ ጠራቸውም ልብ ብለናል። ከሌሎች የአብርሃም ልጆች መካከል ይስሐቅ እንደ ተመረጠ ሁሉ፥ እንደዚሁም ያዕቆብ ከዔሳው ይልቅ ምርማን እንዳገኘ፥ እንዲሁም እግዚአብሔር የመረጣቸውና እርሱንም የተቀበሉ ብቻ እርሱ የሚሰጠውን ደኅንነት ይቀበላሉ። በአንጻሩ እግዚአብሔር ያልመረጣቸውን እርሱም ችላ ስለሚላቸው እነርሱ ወደ ፈቀዱት ወደ ራሳቸው መንገድ ይሄዳሉ።  ነገር ግን ይህ ፍትሐዊ ነው? እግዚአብሔር ያዕቆብን መርጦ ዔሳውን ሲነጋው ፍትሐዊ ያልሆነ ተግባር መፈጸሙ ነው? እንደዚሁም እግዚአብሔር አንዳንዶቹን ሰዎች በመምረጡና እነርሱም የደኅንነት ጥሪውን እንዲሰሙ ሲያደርግና በአንጻሩ ደግሞ ሌሎችን ወደ እርሱ ሳያመጣ ችላ በሚላቸው ጊዜ አድልዎ ማድረጉ ነውን? ጳውሎስ ለእነዚህ ከባድ ጥያቄዎች በሮሜ 9 ውስጥ መልስ ሲሰጥ፥ እግዚአብሔር የደኅንነትን ሉዐላዊ ቁጥጥር በመዘንጋት አልነበረም። በዚህ ፈንታ ሲገልጽም፥ እግዚአብሔር በደኅንነት ላይ ሥልጣን ቢኖረውም ሥልጣኑን የተወሰኑ ሰዎችን ለመምረጥና ሌሎችን በመተው ሥልጣኑን በነሲብ እንዳልተጠቀመበት ይናገራል። በአንጻሩ እግዚአብሔር ብዙ ጊዜ ምሥጢራዊና አስደናቂ በሆነ መንገድ የቁጥጥር ሥልጣኑን ምሕረትን ለማዳረስ ይጠቀምበታል። እንዲሁም እርሱ ብዙ ጊዜ የቁጥጥር ሥልጣኑን ደኅንነቱን ሌሎች ብዙ ሰዎች ለማዳረስ ይጠቀምበታል። የእግዚአብሔር ሥልጣን እንዴት እኛ ስለ ደኅንነት ካለን ኃላፊነት ጋር እንደሚስማማ ለሚኖሩት ጥያቄዎች ሐዋርያው ጳውሎስ መልስ የሚሰጠው ትኩረቱን በእግዚአብሔር ታላቅነት ላይ በማድረግና እኛን ስላዳነን እርሱን  እንድናመልክ ጥሪ በማድረግ ነው።  ጥያቄ፡- ሮሜ 9፡14-16 አንብቡ፡፡ ሀ) ደኅንነት በምን ላይ አይመረኮዝም? ለ) ደኅንነት በምን ላይ ይመረኮዛል?  ጳውሎስ፥ በሮሜ 9፡14-29 ባለው ክፍል እግዚአብሔር በደኅንነት ላይ ስላለው ሥልጣንና አስቸጋሪ ስለሆነው ነገር በመጥቀስ ማብራሪያውን ይጀምራል። ታዲያ እግዚአብሔር የተወሰኑ ሰዎችን መርጦ ሊያድን ሳለ ሌሎችን ደግሞ አለማዳኑ ፍትሐዊ አይደለም ያለኘዋል? እግዚአብሔር በሥልጣኑ ሰዎችን ለማዳን የሚሠራባቸውን ሁኔታዎች በሦስት ጠቃሚ መንገዶች አማካይነት መልስ ይሰጥበታል።  1. ለጥያቄዎቹ የጳውሎስ የመጀመሪያው መልስ፡- የእግዚአብሔር ሉዓላዊ ምሕረት ማንኛውም ሰው ሊድንበት የሚችል ብቸኛው መንገድ ስለ መሆኑ ነው።  በመሠረቱ ማንም ሰው ለምሕረቱ ስጦታ ብቁ ስላልሆነ እግዚአብሔር ምሕረቱን ለጥቂቶች መስጠቱ ፍትሐዊ አይደለም አያሰኘውም። ለዚህ ማስረጃ ጳውሎስ በቁጥር 5 ውስጥ ከዘጸአት 33፡19 በመጥቀስ ያቀርባል። ይህ የእግዚአብሔር ቃል የመጣው የእስራኤል ልጆች በሲና ተራራ የወርቅ ጥጃ በማምለክ ኃጢአት በሠሩ ጊዜ ነበር። ሙሴ እስራኤላውያን ለዚህ የወርቅ ጥጃ መስገዳቸውን እንዳወቀ የጥጃ ውን ምስል ደምስሶ የእግዚአብሔርን ምሕረት ለመለመን ወደ ሲና ተራራ ሄደ። በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር መላ እስራኤልን ለማጥፋት ሥልጣን እንደ ነበረው ሙሴ ያውቅ ነበር። ስለዚህ እግዚአብሔር በምሕረቱ ሕዝቡን እንዲታደገው እንጂ እንዳያጠፋው ለመነው።  ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ለሙሴ የመለሰለት እንዴት ነበር እግዚአብሔር መልሱን የሰጠው እርሱ የምሕረት አምላክ መሆኑን በማሳወቅ ነበር፡ ለእርሱ ምሕረት መሠረታዊ ባሕርይው ስለሆነ ለሕዝቡ ራራለት ለጣዖታት እንዳይሰግዱ ሕግ ሰጥቶአቸው ነበር። እስራኤል ግን ያንን ሕግ ትእዛዝ ሻረ። ምንም እንኳን ሕዝቡ ጥፋት የሚገባው ቢሆንም፥ እግዚአብሔ በዚህ ምክንያት ሕዝቡን በሙሉ አልደመሰሰም። ይልቅለ መሐሪ አምላ በመሆኑና ርኅራኄ ባሕርይው ስለሆነ ምሕረቱን ሰጥቶ አብዛኛዎቹን ከጥፋት ተቤዣቸው።  ጳውሎስ ይህን ክፍል ካዘጸአት ውስጥ በመጥቀስ ማንም ሰዉ ለእግዚአብሔር ደኅንነት በራሱ ብቁ አለመሆኑን አመልክቷል። እንዲህ ሮሜ 9፡16 ማንም ሰው የእግዚአብሔርን ምሕረት ስለፈለገ ወይም ጠንክ በመሥራቱ እንደማያገኝ በግልጽ አስቀምጦታል። ይህ እንግዲህ ሁሉም ወ የመንገዳቸው እንዲሄዱ ስለተተዉ የእግዚአብሔርን ምሕረት የሚሻ ወይና ለማግኘት የሚጥር አልነበረም! ማንም ቢሆን ምሕረትን ሊያገኝ የሚችለዉ እግዚአብሔር በሥልጣኑ ምሕረትን ሊሰጥ ሊፈቅድ ብቻ ነው። እንደ እስራኤል ሕዝብ ሁሉ ማንኛውም ሰው በደለኛ ስለሆነ የእግዚአብሔርን ቅጣት መቀበል ይኖርበታል። እግዚአብሔር እንደ ሰዎች ክፋት አፀፋውን ፍርድ ሊሰጥ ቢወስን ኖሮ ሰዎች ሁሉ ወደ ሲኦል በወረዱ ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር የምሕረት አባት ስለሆነ፥ ቸርነትን ለማድረግ የዘወትር ፈቃዱ ከመሆኑ የተነሣ አዛኝና ርኅሩኅ ነው። ስለዚህ በሥልጣኑና በሁሉን ቻይነቱ ለጥቂቶች ደኅንነትን ለመስጠት መረጠ።  አንድ ጊዜ አንድ ወታደር የጦር ሠራዊቱን ደንብ በመተላለፉ ምክንያት የሞት ቅጣት ተፈረደበት። የወታደሩም እናት ይህን ጊዜ ወደ ጄኔራሉ ዘንድ መጥታ ልጅዋን ምሕረት ሰጥቶ ከሞት እንዲያተርፍላት ተማጠነችው። ጄኔራሉ ግን መልሶ፥ ወታደሩ ደንብ የተላለፈ ወንጀለኛ በመሆኑ ፍትሕ የእርሱን ሞት እንደሚጠብቅ ነገራት። የልጁም እናት፥ «እኔ ስለ ፍትሕ እልጠየቅሁህም፥ የእኔ ልመና ምሕረት ነው» አለችው። ጄኔራሉም መልሶ፣ «ግን እኮ ምሕረት የማይገባው ሰው ነው» አላት። ከዚህ በኋላ የወታደሩ እናት ጥበባዊ መልስ ሰጠችው፣ «ክቡር ጄኔራል፣ ምሕረት የሚገባ ነገር ከሆነማ ምሕረት ሊባል አይችልም፥ እኔ ግን የምጠይቀው ስለ ምሕረት ነው» አለች። ጄኔራሉ በዚህች ሴት መልስ ተደነቀ። ከዚያም በሰጠው ምሕረት ወታደሩ ልጅዋ ከሞት ሊድን ቻለ።  በተመሳሳይ መንገድ የሰው ልጆች ሁሉ በኃጢአታቸው ምክንያት በድለዋል። የፍትሕ ጥያቄም በደለኛች ሁሉ ለሠሩት ኃጢአት ቅጣት የእግዚአብሔርን ቁጣ እንዲቀበሉ ነው። ማንም ምሕረት አይገባውም። ልክ እንደዚህ ጄኔራል፥ ሰዎች ምሕረትን ስለ ተመኙ ወይም ለማግኘት በጎ ሥራ ስለ ሠሩ እግዚአብሔር ምሕረትን አይሰጣቸውም። ደግሞም እግዚአብሔር ባለብዙ ምሕረት የሚሆነው ሰዎች ምሕረትን ለማግኘት ብቁዎች ስለሆኑ አይደለም፡፡ ሰዎች ምሕረትን ለማግኘት ብቃት ካላቸውማ ምሕረትም ምሕረት አይሆንም። ልክ እንደዚህ ጄኔራል፤ እግዚአብሔር ምሕረቱን የሚሰጠው ምሕረትን ለመስጠት በሥልጣኑና በሉዓላዊነቱ ስለሚፈቅድና ስለሚመርጥ ነው። ምሕረት ምሕረት ሊሆን እንዲችል ሁልጊዜ ሥልጣናዊ የምርጫ ስጦታ መሆን አለበት። ምሕረት ምሕረት ይሁን ከተባለ በራስ ብቃት ወይም በመልካም ሥራ የሚገኝ መሆን የለበትም። እንዲሁም ምሕረት ምሕረት ይሁን ከተባለ በምሕረት ሰጪው በጎ ፈቃድ የሚሰጥ ሊሆን ይገባል። ምንም እንኳን ሰዎች ሁሉ ቅጣት የሚገባቸው ቢሆኑም፣ እርሱ የምሕረት አምላክ በመሆኑ በሥልጣኑ ጥቂቶችን ለማዳን ምሕረቱን ይሰጣቸዋል።  ጥያቄ፡- ሀ) ይህ የእግዚአብሔር ምሕረት ሰለ እርሱ ይሰማችሁ ዘንድ እንዴት ያደርጋል? ለ) ስለ ደኅንነታችሁላ እንዴት እንድታስቡ ያደርጋል?  አንዳንድ ጊዜ ክርስቲያኖች በደኅንነት ጉዳይ ላይ ስለሚኖራቸው ድርሻ ከፍ ያለ አስተሳሰብና ምት አላቸው። ስለሆነም አንዳንድ ጊዜ እነርሱ የጻኑ ሲሆኑ ሌሎች ባለመዳናቸው ስለ ራሳቸው በመጠኑ ኩራት ይሰማቸዋል። እንዲሁም አንዳንድ ጊዜ ትንሽ ብልጥነት፥ ትንሽ ታዛዥነትና ትሕትና ደግሞም ክርስቶስን ካልተቀበሉት ሰዎች ይልቅ መንፈሳዊ ነገሮችን የመገንዘብ ችሎታ ያላቸው መስሎ ይሰማቸዋል። በተጨማሪም በአካባቢአችው ከሚገኙ አማኝ ካልሆኑ ሰዎች ይልቅ መድኃኒት እንደሚያስፈልጋቸው በማወቃቸው የተሻሉ የመሆን ስሜት ይከሠትባቸዋል። ስለዚህ ይህ ክፍል እግዚአብሔር ለእኛ ራርቶ ምሕረቱን እንዲሰጠን ያደረገው ግንዛቤአችን ወይም ለመዳን የምናደርገው ጥረት አይደለም። ሁላችንም እንደ ሌሎች ሁሉ በኃጢአታችን ምክንያት በድለናል። እንደ ማንኛውም ሰው የእግዚአብሔር ቅጣት የሚገባን ነን። እኛ ሁልጊዜ ማስተዋል የሚገባን ደኅንነትን ልናገኝ የቻልነው እግዚአብሔር የምሕረት አባት በመሆኑና እኛንም ለማዳን ስለ ጠራን ነው።  ጥያቄ፡- ስለ ደኅንነታችሁ በልባችሁ ውስጥ ስለተሰማችሁ የኩራት ሁኔታ በማስታወሻ ደብተራችሁ ውስጥ ጻፉ። ይህን አጉል ስሜታችሁን እየተናዘዛችሁ አጭር ጊዜ በጸሎት እሳልፉ። እግዚአብሔር እናንተን ለማዳን የምሕረትና የርኅራኄ አሳት ስለሆነ አመስግኑት።  ጥያቄ፡- ሮሜ 9፡17-29 አንብቡ። ሀ እግዚአብሔር በምን ምክንያት ፈርዖንን አስነሣው (ቈ 17)? ለ) ሐዋርያው ጳውሎስ በሸክላ ሠሪውና በሸክላው ምላሱ ስለ እግዚአብሔር ባሕርይ ምንን እስተማረ፧ በአሳባችሁ ውስጥ የሚመጡትን ነገሮች በሙሉ ጻፉ። ሐ) እግዚአብሔር ሊቀበሉት ያልፈለጉትን በምን ምክንያት ይታሣቸዋል?  ጥያቄ፡- በሮሜ 9፡25-26 ላይ ጳውሎስ ሆሴዕ 2፡23ና እንዲሁም ምዕራፍ 1፡10 ይጠቅሳል። በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ የእግዚአብሔር ሕዝብ ባልሆኑት ላይ ምን ይደርሳል?  ጥያቄ፡- በሮሜ 9፡27-29 ባለው ክፍል ጳውሎስ ኢሳይያስ 10፡22-23 ና ምዕራፍ 1፡9ን ይጠቅሳል። ሀ) በእነዚህ ጥቅሶች መሠረት፥ ከእስራኤል ሕዝብ ስንቱ ይድናሉ? ለ) እግዚአብሔር እስራኤልን ለማዳን ጣልቃ ባይገባ ኖር በእስራኤል ላይ ምን ይደርስ ነበር?  2. ሁለተኛው ትምህርት ሰዎችን ለማዳን የእግዚአብሔር ምሕረት

እግዚአብሔር ለጥቂቶች ምሕረቱን ሊሰጥ ይመርጣል  Read More »

ወደ ደኅንነት መድረሻው መንገድ – የእግዚአብሔር ምርጫና የእግዚአብሔር ጥሪ 

This entry is part 73 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ኢየሱስ ክርስቶስ ደኅንነትን ሊሰጠን ብሎ ስለፈጸመው ተግባር ተምረናል። ኢየሱስ ኃጢአት በሌለበት ሕይወቱ፥ መሥዋዕትነትን በከፈለበት ሞቱና ድልን በተጎናጸፈበት ትንሣኤው፥ የኃጢአታችንን ቅጣት በመቀበል ከኃጢአትና ከሰይጣን ቁጥጥር ነፃ አወጣን። የኢየሱስ ሕይወት፥ ሞትና ትንሣኤ የደኅንነታችን መሠረቶች ናቸው። ነገር ግን እያንዳንዱ ሰው እንዴት ይህን ደኅንነት ሊቀበል ይችላል? የክርስቶስ ተግባር በእውነት ወደ እያንዳንዳችን ደኅንነትን ያመጣልን ዘንድ፥ እግዚአብሔር ምን ያደርጋል? እኛስ የክርስቶስን ደኅንነት ለማግኘት ምን ማድረግ ይጠበቅብናል? በዚህ ሳምንት እግዚአብሔር ሰዎችን ለመምረጥና ለመጥራት ስለሚፈጽመው ተግባር እናጠናለን። በሚመጣው ሳምንት ደግሞ የክርስቶስን ደኅንነት ለመቀበል ምን ማድረግ እንደሚገባን እንማራለን፡  እግዚአብሔር ወደ ደኅንነቱ እንዲመጡ ብዙዎችን ይጠራል፤ በአንጻሩ ግን ጥቂቶችን ይመርጣል የእግዚአብሔር የወንጌል ጥሪ ለሁሉ  ሰዎች ከኃጢአታቸው የሚድኑበትን ደኅንነት ሊሰጣቸው እግዚአብሔር ወደ እርሱ ዘንድ ይመጡ ዘንድ ጥሪውን ያቀርባል። ይህ ጥሪ የእግዚአብሔር የወንጌል ጥሪ ወይም የእግዚአብሔር አጠቃላይ ጥሪ ተብሎ የሚጠራበት ጊዜ አለ። ሰዎች ሁሉ ወንጌልን ማለት የምሥራቹን ይቀበሉ ዘንድ እግዚአብሔር ለሁሉም የሚያቀርበው ጥሪ ነው።  ጥያቄ፡- ኢሳይያስ 45፡22 አንብቡ፡ ሀ) እግዚአብሔር ወደ እርሱ ይመለሱ ዘንድ እነማንን ጠራ? ለ) ወደ እግዚአብሔር የሚመለሱት ምን ያገኛሉ?  ጥያቄ፡- ኢሳይያስ 55፡1 አንቡ። ሀ) እግዚአብሔር ማን ወደ እርሱ ይመጣ ዘንድ ጠራ? ለ) ወይንና ወተት ለመዛት የሚመጡ ምን ያህል ዋጋ ይጠየቃሉ?  3ኛ ጥያቄ፡- ማቴዎስ 11፥28-30 ንቡ። ሀ) ኢየሱስ ወደ እርሱ ይወጡ ዘንድ እነማንን ጠራ? ለ) ኢየሱስ ወደ እርሱ ዘንድ ለሚመጡት ምን ተስፋ ሰጣቸው?  4ኛ ጥያቄ፡- ማቴዎስ 22፡44 አንብቡ። ሀ) የተጠሩት ምን ያህሉ ናቸው? ለ) ምን ያህሉን ተመረጡ?  5ኛ ጥያቄ፡- ራእይ 22፡17 አንብቡ። የሕይወትን ውኃ መጥተው በነፃ ይወለዱ ዘንድ የተጠሩት እነማን ናቸው?  የእግዚአብሔር የወንጌል ጥሪ፥ ሰዎች ሁሉ በኃጢአታቸው ከበደሉት በደል ሁሉ ነፃ ወጥተው ደኅንነትን እንዲያገኙ ነው። በኢሳይያስ 45፡22 ውስጥ በምድር ዙሪያ ያሉ የሰው ልጆች ሁሉ ወደ እርሱ ይመለሱ ዘንድ እግዚአብሔር ጥሪ ያቀርብላቸዋል። ቃሉን ሰምተው ቢታዘዙ ደኅንነትን ለማግኘት እንደሚችሉ ተስፋ ይሰጣቸዋል። በሚቀጥሉት የጥቅስ ቁጥሮች ውስጥ፥ ጠላቶቹ እንደሚቀጡ እግዚአብሔር በራሱ ይምላል። ዳሩ ግን ወደ እርሱ ዘንድ የሚመጡ ጻድቃን ተብለው እንደሚጠሩ ይናገራል። እንዲሁም በኢሳይያስ 55፡1 የመንፈስ ጥማት ያለባቸው ሁሉ ወደ እርሱ ዘንድ መጥተው መንፈሳዊ ወይንና ወተት በነፃ ጠጥተው ከጥማቸው እንዲረኩ ሰዎችን ሁሉ ይጋብዛል። ኢየሱስም ወደዚህ ምድር በመጣበት ጊዜ እርሱ የእነዚህ የብሉይ ኪዳን ተስፋዎች ፍጻሜ መሆኑን ግልጽ አድርጎ ተናግሮ ነበር። ሰዎች ሁሉ ወደ እርሱ ዘንድ መጥተው የደኅንነቱ ቡራኬ ተሳታፊዎች ይሆኑ ዘንድ ነፃ ጥሪ አቅርቧል። በማቴዎስ 11፡28–30 ደግሞ የተጨነቁትና ሸክምም የከበደባቸው ወደ እርሱ ዘንድ ይመጡ ዘንድ ኢየሱስ ጥሪ አቅርቦላቸዋል። እረፍትን በተለይም የነፍስ ዕረፍትን ሊሰጣቸው ፈቅዷል። ኢየሱስ በማቴዎስ 22 ላይ ስለ አንድ ሠርግ ዝግጅት ተርኮ ነበር። ሠርጉን ያዘጋጀው ንጉሥ ብዙ እድምተኞችን ጠራ። ነገር ግን ከተጠሩት ብዙዎቹ ለመምጣት ባለመፈለጋቸው እንዲሁም ጥሪውን እክብረው ከመጡት መካከል አንዳንዶቹ ንጉሡ በፈለገው አኳኋንና ሥነ ሥርዓት በመምጣት ፈንታ በራሳቸው መንገድ ስለ መጡ፥ እነዚያ ጥሪውን አክብረው የንጉሡን ሥነ ሥርዓት ጠብቀው የመጡት ጥቂቶቹ ብቻ የሠርጉን ደስታ ሊካፈሉ ቻሉ። ኢየሱስ ይህን ታሪክ ተናገር በቁጥር 14 ላይ እንዲህ ብሎ ትረካውን ደመደመ፤ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የተጠሩት ብዙዎች ሲሆኑ፥ ወደ መንግሥቱ ገብተው የደስታው ተካፋይ ለመሆኑ የተመረጡ ጥቂቶች ናቸው። በእግዚአብሔር ጋባዥነት ወደ መንግሥቱ ለመግባትና የደኅንነቱን ደስታ ማግኘት ማለት ሰፊ ግብዣ ወይም ጥሪ ነው። ጥሪው ለዓለም ሁሉ የተላለፈ ጥሪ ነው። ነገር ግን ብዙዎቹ የእግዚአብሔርን ጥሪ ችላ በማለታቸው፥ እንዲሁም ወደ ግብዣው እንዳሻቸው ስለ መጡና እግዚአብሔር በፈቀደው መንገድ ባለመምጣታቸው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የሚገቡት ጥቂቶቹ ናቸው። ራእይ 22፡17 የኢሳይያስ 5፡1ን ጥሪ የሚያስተጋባ ሲሆን፥ ማንኛውም የተጠማ ሰው መጥቶ የዘላለምን ሕይወት ነፃ ስጦታ ይቀበል ዘንድ ጥሪ ያቀርባል።  እያንዳንዱ ሰው በራሱ ለእግዚአብሔር ጥሪ ምላሽ መስጠት አለበት  እግዚአብሔር በዓለም ላሉ ሰዎች ሁሉ ደኅንነቱን ይሰጣል። እንዲህ ሲባል ደሞ ማንኛውም ሰው ይድናል ማለትም አይደለም። ይህን ደኅንነት ለማግኘት ሰዎች ይህን መልእክት አድምጠው ለጥሪው መልስ ሲሰጡ፥ ያን ጊዜ ይህን የተዘጋጀላቸውን ደኅንነት ሊያገኙ እንደሚችሉ ቅዱስ መጽሐፍ ያስገነዝባል።  ጥያቄ፡- ዮሐንስ 1፡11-12 አንብቡ፡ ሀ) ኢየሱስ ለእነማን መጣ? ለ የእግዚአብሔር ልጅነትን መብት እነማን አገኙ?  ጥያቄ፡- ሮሜ 10፡12-15 አንብቡ። ሀ) እግዚአብሐር የደኅንነትን በረከ፡ ለእነማን ሰጠ? (ቁ 12) ለ) እንድ ሰው ይህን ደኅንነት ለማግኘት ምን ማድረግ ይኖርበታል? (ቁጥር 13-14) አንድ ሰው እነዚህን ነገሮች ከመፈጸሙ በፊት ምን መደረግ ይኖርበታል? (ቁጥር 14-)  ጥያቄ፡- ራእይ 3፡20 አንብቡ፡ ኢየሱስ ወደ ሰው ሕይወት መጥቱ ከእርሱ ጋር አንድነት እንዲኖረው ምን መደረግ ይኖርበታል?  እግዚአብሔር ደኅንነቱን ለሰዎች ሁሉ ይሰጣል። ቢሆንም ሰዎች ይህን የደኅንነት ስጦታ ለማግኘት በግላቸው ለዚህ የእግዚአብሔር ስጦታ የሚጠበቅባቸውን ምላሽ መስጠት አለባቸው። በዮሐንስ 1፡11-12 ያለው ክፍል ኢየሱስ ወደ ወገኖቹ ወደ አይሁድ ቢመጣም እነርሱ ገን እንዳልተቀበሉት ይገልጻል። ታዲያ እነዚያ ጥቂቶቹ የተቀበሉትና ያመኑበት ብቻ የእግዚአብሔር ልጅነትን መብት አግኙ። እንዲሁም በሮሜ 10፡12 አይሁድም ሆነ አሕዛብ ሁሉም የእግዚአብሔርን የደኅንነት ስጦታ ሊቀበሉ መጠራታቸውን ያብራራል። ነገር ግን ቁጥር 13-14 ባለው ክፍል ታክሎ እንደምንመለከተው የጌታን ስም የሚጠሩና በእርሱ የሚያምኑ ብቻ ‘ እንደሚድኑ ይናገራል። ስለሆነም ሰዎች የጌታን ስም ለመጥራትና በእርሱም ለማመን እንዲችሉ የተሰበከላቸውን የክርስቶስን መልእክት ማዳመጥ ይኖርባቸዋል። ምንም እንኳን ደኅንነት ለሁሉም ቢሆንም፥ እያንዳንዱ ሰው በግሉ ደኅንነትን ተቀብሎ ለመዳን የክርስቶስን ጥሪ አድምጦ የሚፈለግበትን መፈጸምና ለጥሪውም ቃል ምላሽ መስጠት አለበት። በራእይ 3፡20 ውስጥ ኢየሱስ፡- በእያንዳንዱ ሰው ልብ መዝጊያ አጠገብ ቆሞ እንደሚያንኳኳና ለመግባትም እንደሚፈልግ ይናገራል። ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው የልቡን ስር ለመክፈት ፈቃደኛ መሆን አለበት። በመሆኑም፥ ሰዎች ኢየሱስ ወደ እነርሱ እንዲገባና ከእነርሱ ጋር አንድነት እንዲኖረው ካላደረጉ በስተቀር አይገባም። እግዚአብሔር የደኅንነት ስጦታውን ለሰዎች ሁሉ ያቀርባል። ይህን ጊዜ ሰዎች ይህን ስጦታ ለመቀበል በግላቸው ዝግጁዎች መሆን አለባቸው። ያለበለዚያ ይህን የእግዚአብሔር ደኅንነት ማግኘት አይችሉም።  ከኃጢአት የተነሣ ቢተዉ፥ ሰዎች ሁሉ ስለ እግዚአብሔር ጥሪ ግድም አይኖራቸውም ጥያቄ፦ ሮሜ 3፡11 እንብቡ። ስንት ሰዎች መንፈሳዊ ነገርችን ተገንዝበው እግዚአብሔርን ይፈልጉታል?  ጥያቄ፡- ዮሐንስ 6፡44 አንብቡ፡ አንድ ሰው ወደ ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት ምን መደረግ ይኖርበታል?  ጥያቄ፡- 2ኛ ቆሮንቶስ 4፡3-4 አንብቡ። ሰይጣን የሚያምኑትን ዓይን ምን አደረገ?  ጥያቄ፡- ሮሜ 1፡18-19 አንብቡ። ሀ) የእግዚአብሔር ቁጣ በሰዎች ላይ በምን ምክንያት ተገለጠ? ለ) እዚህ ላዎች ስለ እግዚአብሔር አንዳች እውቀት ነበራቸው? (ቁ 19) ሐ) ሮሜ 1፡21፣25 አንብቡ። እግዚአብሔርን ሳወቁት መጠን እዚህ ሰዎች ምን አደረጉ?  ጥያቄ፡- ማቴዎስ 23፡37 አንብቡ። ሀ) ኢየሱስ ለሰዎቹ ምን ሊያደርግላቸው ፈለገ? ለ) መልሳቸው ወይም አስተሳሰባቸው ምን ነበር?   ጥያቄ፡- ዮሐንስ 5፡40 አንብቡ። ሰዎች ለኢየሱስ ምላሽ የሰጡት እንዴት ነበር?  15ኛ ጥያቄ፦ ዮሐንስ 8፡44 አንብቡ። አይሁዳውያን የማንን ፈቃድ መፈጸም ይፈልጉ ነበር?  በ12ኛው ትምህርት ውስጥ፣ ሰዎች በተፈጥሮ ኃጢአተኛች ሆነው እንደሚመለፉ፥ እንዲሁም ሁሉም ሰዎች ኃጢአት እንደሚሠሩ ተምረናል። እንደዚሁም ከዚህ ኃጢአት የተነሣ ማንም ሰው የእግዚአብሔርን ጥሪ ተቀብሎ ወደ እርሱ ሊመጣ እንደማይችል ተመልክተናል። የማያምኑ ሰዎች እውነተኛ የሆነ መንፈሳዊ ንዛቤ የላቸውም (ኤፌሶን 4፡18፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 2፡13)፥ በኃጢአታቸውም የሞቱ ናቸው (ኤፌሶን 2፡1)፥ የኃጢአትም ባሪያዎች ናቸው (ዮሐንስ 8፡34)። ኃጢአት ሰዎች የእግዚአብሔርን የደኅንነት ጥሪ ተቀብለው ወደ እርሱ እንዳይመጡ ያደርጋቸዋል። የማያምኑ ሰዎች የእግዚአብሔርን ሥራ እንዳይመለከቱ ዓይናቸውን ስለሚያሳውርሳቸው፥ እግዚአብሔር ጣልቃ ካልገባ በስተቀር፥ የወንጌልን ብርሃን ሊያዩ አይችሉም (2ኛ ቆሮንቶስ 4፡3-4)። እግዚአብሔር ወደ ሕይወታቸው ከመግባቱ በፊት ማንኛቸውም ስለ እግዚአብሔር ሊነዘቡና እግዚአብሔርንም ሊፈልጉት አይችሉም (ሮሜ 3፡1ህ። ስለዚህ ያላመኑ ሰዎች ባሉበት ሁኔታ ቢተዉ ወደ እግዚአብሔር ለመምጣት አይችሉም። እግዚአብሔር ራሱ ሰዎችን ወደ ክርስቶስ ካልሳበ በስተቀር ወይም እርሱ ሥራውን ካልሠራ ሊመጡ አይችሉም (ዮሐንስ 6፡44)።  እግዚአብሔር ለሰዎች ሁሉ

ወደ ደኅንነት መድረሻው መንገድ – የእግዚአብሔር ምርጫና የእግዚአብሔር ጥሪ  Read More »

ኢየሱስ በሞቱ በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን ተቀዳጅቷል – ክፍል ሁለት 

This entry is part 72 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

በትናንትናው ቀን ክርስቶስ በሰይጣን ላይ ስለተቀዳጀው ድል ማጥናት ጀምረን ነበር። የዚህ የድል ትንቢት የተነገረው በኤድን ገነት ውስጥ እንደ ነበረና ይህም ቀደም ብሎ በኢየሱስ አገልግሎት ውስጥ እንደ ተጀመረ እና ኋላም ክርስቶስ በመስቀል ላይ በሞተ ጊዜ ግቡን እንደ መታ ተገንዝበናል። በእርሱ ለሚያምኑት የክርስቶስ ድል ተጨባጭ ውጤት ምንድን ነው? በዛሬው ዕለት ኢየሱስ በሰይጣን ላይ ስለ ተቀዳጀው ድል ስለ ማሳወቅ፥ ስለ ማስፋፋትና ስለ ድሉ ፍጻሜ እናጠናለን።  በክርስቶስ ትንሣኤ የተገኘና የተነገረ ድል  የኢየሱስ ከሞት መነሣት በመስቀሉ በሰይጣን ላይ የተገኘውን ድል ያረጋገጠ ከመሆኑም በላይ የድሉን ውጤት ለዓለም ሁሉ አስተጋብቷል።  ጥያቄ፡- የሐዋ. 13፡37-39 አንብቡ። የትንሣኤው ውጤት ምንድን ነው?  ጥያቄ፡- የሐዋ. 17፡31 እንብቡ። ትንሣኤው ምንን አረጋገጠ? ጥያቄ፡- 1ኛ ቆሮ. 15፡20፥ 23-26 አንብቡ። የኢየሱስ ትንሣኤ የሚሰጠው ዋስትና ምንድን ነው? በእነዚህ ምንባቦች ውስጥ ቢያንስ ሦስት መልሶችን ፈልጉ።  ጥያቄ፡– ኤፌ. 1:20-21 እንብቡ። እግዚአብሔር ኢየሱስን ከሞት ባስነሣው ጊዜ ምን ተፈጸመ?  ጥያቄ፡– ኤፌ 4፡8 አንብቡ። ኢየሱስ ወደ ሰማይ ባረገ ጊዜ ምን አደረገ?  የክርስቶስ ትንሣኤ ለሚያምኑበት ምን ጥቅም አስገኘላቸው? በአዲስ ኪዳን ውስጥ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ያስገኘውን ድል ትንሣኤው በዋስትና አረጋገጠልን። ድሉም በዓለም ሁሉ ላይ ታወቀ። የሐዋ. 13፡37-39 እንደሚለው ኢየሱስ ከሞት በመነሣቱ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የኃጢአትን ይቅርታ ያገኛል። ይህ ይቅርታም በሙሴ ሕግ አማካይነት የሚገኝ አይደለም ይላል። ትንሣኤው እንዳረጋገጠው በኃጢአታቸው ምክንያት በሰይጣን ባርነት ሥር ያሉና ስለ ኃጢአታቸውም ቅጣትን የሚጠባበቁ በኢየሱስ ክርስቶስ በሚሆን እምነት የኃጢአታቸውን ይቅርታ አግኝተዋል።  የሐዋ. ሥራ 17፡31 እንደሚለው ኢየሱስ አንድ ቀን በዓለም ላይ እንደሚፈርድ ትንሣኤው አረጋግጦአል። ኢየሱስ በፍጥረቱ ላይ ያለው የገዢነት ሥልጣን በሰይጣንና በአጋንንቱ ላይ ያለውንም ሥልጣን የሚጨምር መሆኑን በአዲስ ኪዳን የሚገኙ ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ይናገራሉ። ኢየሱስ በፍጥረት ሁሉ ላይ ፈራጅ እንደሚሆን በትንሣኤው ተረጋግጦአል። ኤፌ። 1፡20-21 እንደሚናገረው ክርስቶስ ከሙታን ተነሥቶ ወደ ሰማይ በወጣ ጊዜ፥ እግዚአብሔር ከግዛትና ከሥልጣን፥ ከኃይልና ከጌትነት በላይ አድርጎ አስቀመጠው ይላል። ሐዋርያው ጳውሎስ «ስለ ግዛት ሥልጣን፥ ኃይልና ጌትነት» በሚናገርበት ጊዜ በተለይ ስለ ሰይጣንና ስለ ሠራዊቱ መናገሩ ነው (ኤፌ. 6፡12፤ 1ኛ ቆሮ. 15፡25 ይመልከቱ)። የኢየሱስ ትንሣኤ ገዢአቸው ለመሆኑ፥ ትክክለኛ መብት ያለው ለመሆኑ ማረጋገጥ ነው። ጳውሎስ ኢየሱስ በሰይጣን ላይ ስለተቀዳጀው ድል የበለጠ ጉልህ ማብራሪያ በኤፌ. 4፡8 ውስጥ ስለ ትንሣኤና ስለ ዕርገት በተናገረው ላይ ገልጾአል። እንደሚለውም «ወደ ላይ በወጣ ጊዜ ምርኮን ማረከ፤ ለሰዎችም ስጦታን ሰጠ» ይላል። ኢየሱስ ከሞት ተነሥተ ወደ ሰማይ ባረገበት ጊዜ ሁኔታው ልክ አንድ ጄኔራል ድል አድርጎ በወታደሮቹ ታጅቦ በጦርነት የያዘውን ምርቱ እስከትሉ ከጦር ሜዳ እንደሚመለስ ዓይነት ነበር። ይህ ድል ያደረገ ጀኔራል በሚኖርበት ከተማ የድል ሰልፍ ካደረገ በኋላ ለሠራዊቱ ስጦታ ያድላል። በጳጳውሎስ አጻጻፍ «ምርኮዎች» የተባሉት ሰይጣንና መናፍስቱ ናቸው። የኢየሱስ ሠራዊት ደግሞ ቤተ ክርስቲያን ናት። የጳውሎስ አባባል አንድ) ጄኔራል ድል አድርጎ ሲመለስ ያገኘውን ምርኮ ይዞ እንደሚገባ ሁሉ፥ ኢየሱስም በመስቀል ላይ በሰይጣንና በሠራዊቱ ላይ የተቀዳጀው ድል በትንሣኤውና በዕርገቱ ተረጋግጦአል።  ምናልባት የክርስቶስ ትንሣኤ በሰይጣንና በሞት ላይ የተቀዳጀው ድል ማረጋገጫና ለዓለም ሁሉ ማወጂያ መሆኑን በይበልጥ የሚገልጸው ክፍል 1ኛ ቆር. 15፤ 1ኛ ቆሮ. 5፡20፥ 23-26 ይሆናል። ቃሉም፥ «የክርስቶስ ትንሣኤ ከሙታን ለሚነሡ ሁሉ በኩር ነው» ይላል። በአሥረኛው ትምህርት ውስጥ እንደተመለከትነው የክርስቶስ ትንሣኤ በእምነት የክርስቶስ ለሆኑት ሁሉ ከሙታን የሚነሡ ለመሆናቸው ዋስትና ነው። እንደዚሁም የክርስቶል ትንሣኤ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ አንድ ቀን ሙሉ በሙሉ ሰይጣንና ሠራዊቱን ድል እንደሚመታ ማረጋገጥ ነው። ማናቸውም («ግዛት፥ ሥልጣንና ኃይልን»፥ ቁጥር 24) ክዚያም ክርስቶስ የአጽናፈ-ዓለም ፍጹም ገዥ ይሆናል። እንደዚሁም በመጨረሻው ላይ ሞት ራሱ ጨርሶ እንደሚሸነፍ የክርስቶስ ትንሣኤ ማረጋገጫ ነው። ክርስቶስ ከመስቀል ላይ በሰው ልጅ ጠላቶች ላይ ያገኘው ድል በትንሣኤው ተረጋግጦ ድሉንም አሳውቆአል። ጠላቶች የተባሉት ሰይጣንና ሠራዊቱ፥ ወይም ክፉ መናፍስቱ፥ ኃጢአትና ሞት ናቸው።  ድሉ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ውስጥ ተስፋፋ  ኢየሱስ በሰይጣንና በክፉ መናፍስት (ሠራዊት) ላይ የተቀዳጀው ድል፥ በዛሬዋ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ውስጥ እየተስፋፋ ነው። የኤፌሶን መልእክት ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሞቶ በሰይጣን ላይ የተቀዳጀው ድል በትንሣኤው አማካይነት እንዴት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ተስፋፋ የሚገልጽ በመሆኑ በጣም ጠቃሚ ነው።  ጥያቄ፡– ኤፌ 1፡22–23 አንብቡ። እግዚአብሔር ኢየሱስን የሁሉ ራስ አድርጎ የሾመው ለምንድን ነው? 46ኛ ጥያቄ፡– ኤፌ 2፡6 አንብቡ። ሀ) እግዚአብሔር በክርስቶስ ያስቀመጠን የት ነው? ለ) ኤፌ 2፡10 አንብቡ። በክርስቶስ ኢየሱስ የተፈጠርነው ምን እንድንሠራ ነው?  ጥያቄ፡– ኤፌ 4፡11 አንብቡ። ሀ) እግዚአብሔር ለቤተ ክርስቲያን ምን ስጦታዎችን ሰጠ? ለ) ኤፌ. 4፡12-13 አንብቡ።  ጥያቄ፡– ኤፌ 6፡10-13 አንብቡ። ሀ) አማኞች የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ከለበሱ ምን ማድረግ ይችላሉ? ለ) ኤፌ 6፡14-17 አንብቡ። አማኞች የሰይጣንን ተቃውሞ ሊከላከሉ የሚችሉት በምን ዘዴ ነው?  ክርስቶስ በሰይጣን ላይ ያገኘው ድል በመስቀልና በትንሣኤ ብቻ ተወስኖ አልቀረም። የዚህ ድል ውጤት በዛሬይቱ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተስፋፍቷል። ኤፌ 1፡22-23፥ እግዚአብሔር ኢየሱስን የሁሉ ራስ አድርጎ በሰይጣንና በሠራዊቱም ላይ፥ ቁጥር 21) ለቤተ ክርስቲያን ሾመው። የኢየሱስ ሥልጣን በሰይጣን ላይ መኖሩ ለቤተ ክርስቲያንም ይጠቅማታል። ከኢየሱስ ሥልጣን የተነሣ ቤተ ክርስቲያን የምታገኘው ጥቅም ምንድን ነው? በተቀረው የኤፌሶን ክፍል ውስጥ ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ከክርስቶስ ድል ጥቅም የምታገኝባቸውን ሦስት መንገዶች ያስቀምጣል። ክርስቶስ በሰይጣንና በርኩሳን መናፍስቱ ላይ ካለው ሥልጣን ቤተ ክርስቲያን የምታገኘው የመጀመሪያው ጥቅም በኤፌ 2፡6 ውስሮ ይገኛል። ጳውሎስ እንደሚነግረን እርሱ ባዳነን ጊዜ እግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር በሰማያዊ ስፍራ አስቀመጠን፡ ዳግም በኃጢአታችን ሙታን አንሆንም፥ ለኃጢአተኛ ተፈጥሮአችንም ባሪያዎች አንሆንም። እንደዚሁም የሰይጣን ተከታይነታችን ይቀራል (ኤፌ. 2፡1-3)። በዚህ ፈንታ በሰይጣንና በመናፍስቱ ላይ ያለው የክርስቶስ የድል አድራጊነቱ ሥልጣን ተካፋዮች እንሆናለን። ስለ ዳንና በዚህ አዲስ ቦታ ላይ ስላለን አዲስ ሕይወትን በመኖር እግዚአብሔር የፈቀደልንን መልካም ሥራ እናከናውናለን (ኤፌ 2፡10)።  ክርስቶስ በሰይጣን ላይ ከተቀዳጀው ድል ቤተ ክርስቲያን የምታገኘው ሁለተኛው ጥቅም በኤፌ 4፡8 ውስጥ ይገኛል። ቀደም ብለን እንዳየነው ሁሉ ሐዋርያው ጳውሎስ ክርስቶስ በሰይጣን ላይ የተቀዳጀውን ድል በትንሣኤውና በእርገቱ እውን ካደረገ በኋላ ለተከታዮቹ ስጦታዎችን አደለ ይለናል። ለቤተ ክርስቲያን ክርስቶስ ያደላቸው ስጦታዎች በኤፌ. 4፡11 ውስጥ ተዘርዝረዋል። እነዚህም፥ ሐዋርያት፥ ነቢያት፥ ወንጌል ሰባኪዎች፥ እረኞችና አስተማሪዎች ናቸው። እነዚህ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ሰዎች አገልግሎቱን ሁሉ ራሳቸው እንዲያከናውኑ ለቤተ ክርስቲያን አልተሰጡም። በአኳያው ኤፌ 4፡12-13 ያለው ክፍል እንደሚነግረን የእነዚህ ተሰጥኦ ያላቸው ሰዎች ተግባር እርስ በርስ አንዱ ሌላውን እንዲያገለግል ማዘጋጀት፥ ማሠልጠንና ማስታጠቅ ነው። ስለዚህ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሰዎች የተዘጋጁና የታጠቁ ሊሆኑና አንዱ ሌላውን ለማገልገል ሲችል ብቻ ቤተ ክርስቲያን ኅብረትን አግኝታ በብስለት ታድጋለች። ክርስቶስ በሰይጣን ላይ ከተቀዳጀው ድል የተገኘችው የተባበረችና የደረጀች ቤተ ክርስቲያን ከክርስቶስ ቀጥላ በጠቃሚነትዋ በሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትቀመጥ ናት።  ሦስተኛው ጥቅም በኤፌ. 6፡10-18 ውስጥ ይገኛል። አማኞች የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር በሚለብሱበት ጊዜ፥ የሰይጣንና የሠራዊቱን ጥቃት ፊት ለፊት ሊቋቋሙ ይችላሉ። እንዴት ያለውን ጥቃት ነው ሊቋቋሙ የሚችሉት? ከቁጥር 14-20 በግልጽ እንደተብራራው አማኛች የሰይጣንን ፈተና ሁሉ ለመቋቋም ይችላሉ።  ጥያቄ፦ በኤፌ 6፡14-17 የተጻፈውን የጦር ዕቃ ብትለብሱ፥ የሰይጣንን ጥቃት ልትን፡ሙ የምትችሉባቸውን የተለያዩ ዘዴዎች ጻፉ?  በኤፈሶን 6፡14-17 የተጠቀሰውን ዕቃ ጦር የለበሱ አማኞች ልባቸውንና አእምሮአቸውን በእግዚአብሔር እውነት፥ በቃሉና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከሞሉ፥ ኃጢአት እንዲሠሩ ለመገፋፋት ሰይጣን የሚያመጣባቸውን ፈተና ሁሉ ሊቋቋሙ ይችላሉ። ሰይጣን እንዲዋሹና እውነትን እንዲደብቁ በሚፈትናቸው ጊዜ፥ እውነተኞች ለመሆንና የእግዚአብሔርንም እውነት ሊያስተጋቡ ይችላሉ። እንደዚሁም ሰይጣን እንዲረክሱ ሲፈትናቸው፥ እነርሱ ን ይህን ተቃውመው የጽድቅ ሕይወትን ሊኖሩ ይችላሉ። ሰይጣን እምነታቸውን ለሌሎች ለማካፈል እንዲፈሩም ሆነ በሌሎች ላይ እንዲቆጡ በሚፈትናቸው ጊዜ፥ ይህን ተቋቁመው ወንጌሉን ያስፋፋሉ። ደግሞም ከሌሎችም ጋር በሰላም ይኖራሉ። ሰይጣን እንዲጠራጠሩ ሲፈትናቸው፥ እነርሱ

ኢየሱስ በሞቱ በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን ተቀዳጅቷል – ክፍል ሁለት  Read More »

የኢየሱስ ሞት በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን አስገኝቷል- ክፍል አንድ 

This entry is part 71 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ባለፉት በርካታ የትምህርታችን ክፍለ ጊዜያት ላይ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ስለፈጸማቸው አብዛኛዎቹ ሥራዎች ተመልክተናል። ኢየሱስ በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ በእኛ ፈንታ መሥዋዕት ሆኖ ስለ ኃጢአታችን ሞተ። እግዚአብሔር በኃጢአታችን ላይ የነበረውን የጽድቅ ቁጣ አስታሠልን፡ ከእግዚአብሔርም ጋር አስታርቆ ከኃጢአታችን ተቤዠን፥ ከኃጢአታችን ቅጣትና ከክፉ ውጤቶቹም አዳነን። ነገር ግን የኢየሱስ ሞት በመስቀል ላይ በሰይጣንና በመናፍስቱ ላይ ድልን ለመቀዳጀት ይረዳል? ስኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ብዙ ሰዎች ሰይጣንና ክፉ መናፍስትን ይፈራሉ። ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሞቶ የሰጣቸው ደኅንነት ሊከላካላቸው ይችላል? ደግሞስ አንድ ክርስቲያን ሰይጣንን የሚፈራበት ምክንያት አለው?  ጥያቄ፡- በአካባቢአችሁ የሚኖሩ ሰዎች ስለ ሰይጣንና ስለ መናፍስቱ ምን ያስባሉ? ይፈሯቸዋል? ከሆነ ሰዎች ከክፉ መናፍስት ለመከላከል የሚያደርጓቸውን ድርጊቶች በማስታወሻ ደብተራችሁ ላይ ጻፉ።  በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ብዙ ሰዎች ራሳቸውን ከሰይጣንና ከክፉ መናፍስቶቹ ለመከላከል የተለያዩ ነገሮችን ያደርጋሉ። የማያምኑ ሰዎች ራሳቸውን ከጠንቋዮችና ከቃልቻዎች ከሚላኩ መናፍስቶች ለመከላከል ይጥራሉ። ሙስሊሞች የሙስሊም ቅዱስ ሰው መምሕር (አሊም) ከሚያደርገው ምትሐት ለመከላከል ይሞክራሉ። እንደዚሁም ራሳቸውን ክርስቲያን አድርገው የሚቆጥሩ ሰዎች ቄስ ወይም ደብተራ ቤታቸው መጥቶ በመድገም በመስቀል ወይም ጠበል በመርጨት ካልተከላከለላቸው በስተቀር ሰይጣንና መናፍስትን ይፈራሉ፥ ሥጋትም ያድርባቸዋል። ሌሎች እንዲህ ያሉ ሰዎች ደግሞ ወንጌላዊ ወይም መጋቢው ከቤታቸው ሕንጻ ውስጥ አለ የሚሉትን ሰይጣን ካላባረረላቸው ፍርሃት ያድርባቸዋል። ራሳቸውን ክርስቲያን ብለው የሚጠሩ ሰዎች ክርስቶስ ሰይጣንን ስለ ማሸነፉ መጠነኛ ግንዛቤ ሊኖራቸው ይችላል። አብዛኛውን ጊዜ የሚፈጽሙት ድርጊት ግን ፡ የክርስቶስ ድል ዛሬም ከሰይጣንና ከዲያብሎስ ሊጠብቃቸው እንደሚችል እንደማያምኑ ሰዎች ዓይነት ነው።  ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያረጋግጥልን፥ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሞቱና በትንሣኤው በሰይጣን ላይ ድልን ስለ ተቀዳጀ አማኛች ሰይጣንን ከቶ ሊፈሩት አይገባቸውም። እግዚአብሔር ለበጎ ከሚፈቅደው በስተቀር፥ ሰይጣን ማንኛውንም አማኝ የማስፈራራት ወይም የመጉዳት ኃይል የለውም። መጽሐፍ ቅዱስ ክርስቶስ በሰይጣን ላይ ስለተቀዳጀው ድል ምን ያስተምረናል? (በዛሬውና በነገው ዕለት የምናጠናው የክርስቶስ ድል በሰይጣን ላይ የሚለው ማውጫ የተወሰደው ጆን ስቶት «The Cross of Christ» [«የክርስቶስ መስቀል»] ብለው ከጻፉት መጽሐፍ ላይ ነው።)  1. በኤድን ትንቢት የተነገረው ድል  ጥያቄ፡- ዘፍጥረት 3፡14-15 አንብቡ። ሀ) እንግዚእብሔር እባቡን በሴቲቱ ዘር ላይ ምን ታደርጋለህ አለው? ለ) የሴቲቱ ዘር በእባቡ ላይ ምን ያደርጋል አለ?  ስለ አዳምና ሔዋን ኃጢአት በዘፍጥረት 3 ውስጥ በተጻፈው መሠረት አጥንተናል። በዚህ ታሪክ ውስጥ እንደተመለከትነው ሰይጣን በእባብ ተመስሎ መጥቶ ሔዋን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ጥሳ ኃጢአት እንድትሠራ ፈተናት። በዘፍጥረት 3፡15 ውስጥ ሰይጣን በዓለም ላይ ኃጢአትን በማምጣቱ እግዚአብሔር በሰይጣን ላይ የፍርድን ትንቢት ተናገረ። እግዚአብሔርም ወደፊት ሰይጣን የሴቲቱን ዘር ሰኮና ይቀጠቅጣል። የሴቲቱ ዘር ግን በተራው የሰይጣንን ራስ ይቀጠቅጣል ሲል ተናግሮአል። እግዚአብሔር በሰዎችና በእባብ መካከል ያለውን ጠላትነት ከሰይጣን ጋር ለሚያካሂደው ጦርነት ምሳሌ አድርጎ አቅርቦታል። አንድ ቀን እግዚአብሔር ከሴቲቱ ዘር ፍጹም የሆነን ሰው አዳኝ አድርጎ ያስነሣል። እግዚአብሔር ሰይጣን የሰውን ሰኮና ይቀጠቅጣል ሲል፥ አንድ ዓይነት ጉዳትን ያደርስበታል ማለቱ ነው። ነገር ግን ሰውዬው የሰይጣንን ራስ ይቀጠቅጣል ሲል፥ ሰውዬው ሰይጣንን ጨርሶ ድል በማድረግ ይደመስሰዋል ማለቱ ነው። ያለጥርጥር ትንቢቱ የተነገረለት ሰውም አምላክም የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፥ እርሱም ከድንግል ማርያም የተወለደው የሔዋን ዘር ነው። ስለ እርሱ ጉዳት የተነገረው ትንቢት የሚያመለክተው ስቅለቱን ነው፥ ሰይጣን ሥራውን በአይሁድ መሪዎች በጲላጦስና በሮማውያን ወታደሮች አማካይነት በመሥራት ኢየሱስን ለማስገደል ቻለ። ነገር ግን በዘፍጥረት 3 ውስጥ እግዚአብሔር ስለ ወደፊቱ የሰይጣን መሸነፍ ይተነብያል። እርሱ እንዴት ተሸነፈ?  2. በኢየሱስ አገልግሎት ድሉ ተጀመረ  ጥያቄ፡- ሉቃስ 10፡1-2፥9፥17-19 አንብቡ። ሀ) ኢየሱስ 72ቱን ም እንዲያደርጉ ላካቸው? ለ) ውጤታቸውስ ምን ነበር? ሐ) ኢየሱስ እነዚህን ውጤቶት እንዴት ተቀበላቸው?  ጥያቄ፡- ሉቃስ 11፡20 አንብቡ። ኢየሱስ አጋንንትን ሲያስወጣ፥ ምን ያረጋግጥ ነበር?  ኢየሱስ በምድር ላይ ያገለግል በነበረበት ጊዜ ከተከታዮቹ መካከል ለ ሁለቱን መርጦ እንዲሰብኩ፥ እንዲፈውሱና አጋንንትን እንዲያወጡ ላካቸው ይህን በሚያደርጉበት ጊዜ የእግዚአብሔርን መንግሥትና እዚአብቁ! በምድር ሁሉ ላይ ገዥ መሆኑን ያሳዩ ነበር። ከተልዕኮአቸው በተመለሰ ጊዜም ትልቅ ስኬት እንዳገኙ ሪፖርት አቀረቡለት። እነርሱም በኢየሱ ስምና ሥልጣን አጋንንትን አስወጡ። ኢየሱስም ይህ ድርጊት የሰይጣን ሽንፈት እንደሚያመለክት ተረዳ። ኢየሱስም በእርሱ ሥልጣን ሥር ሰይጣ ከሚያደርሰው ጉዳት ሁሉ እንደሚጠበቁ ቃል ገባላቸው። ለእነዚህ ሰባ ሁለቱ ኢየሱስ የሰጣቸው ሥልጣን ኢየሱስ በዚህ ምድር ላይ በነበረ ጊዜ ይፈጽማቸው የነበሩትን ተግባራት የሚያመለክት አንድ ምሳሌ ነው። ኢየሱስ አጋንንትን በሚያስወጣበትም ጊዜ ወይም በሰይጣን ኃይል የታመመ ሰውን በሚፈውስበት ጊዜ ሰይጣንን ማሸነፉን የሚያመለክት ነበር። እርሱም የእግዚአብሔር መንግሥት እዚሁ በምድር ላይ በእርሱ ውስጥ መሆንዋን ያረጋግጥ ነበር። የሰይጣንንም መሸነፍ መጀመሩ ነበር። የኢየሱስ አገልግሎት በምድር ላይ መጀመር በሰይጣን ላይ ድል የመቀዳጀቱ መጀመሪያ ነበር። እውነተኛው ድል ቀን የተገኘውና የተፈጸመው ሽንፈት በመሰለው በኢየሱስ ስቅለት ነው።  3. በኢየሱስ ስቅላት የተገኘ ድል  ጥያቄ፡- ዮሐንስ 12፡31 አንብቡ። ኢየሱስ በተሰቀለ ጊዜ በሰይጣን ላይ ምን ይደርስ ነበር?  ከስቅለቱ አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ተሰብስበው ለነበሩ ሰዎች ንግግር አደረገ። በመናገርም ላይ ሳለ ድምፅ ከሰማይ መጣ። አብዛኛዎቹ ሰዎች ስለ ድምጹ በግልጽ አልተረዱም ነበር። በዚህን ጊዜ ኢየሱስ ሊያውቁት በሚገባ ቃል እግዚአብሔርን በእርሱ ላይ በሚፈጸመው ነገር እንደሚከብር መናገሩን ገለጸላቸው። ሊሆን ያለው ነገር ምን ነበር? ኢየሱስ የሚሰቀልበት ጊዜ ቀርቧል። ኢየሱስም ቀጥሉ እርሱ በሚሰቀልበት ጊዜ ሰይጣን ወደ ውጭ እንደሚጣል ገለጸላቸው። በተመሳሳይ መንገድ ከግለሰቦች ሕይወት ውስጥ አጋንንትን ባስወጣበት ጊዜ ሁሉ ሰይጣንን ሲያሸንፍ ቆይቷል። አሁን ግን በበለጠ መንገድ ሰይጣንን ሊያሸንፈው ነው። ሰይጣን በዓለም ያለውን የቁጥጥር መረብ ሊበጣጥስበት ነው። በየትም ስፍራ ያሉ ሰዎች ሁሉ ከሰይጣን ቁጥጥር ነፃ እንዲወጡ መንገድ ሊያመቻች ነው። መስቀል ሰይጣን የሚሸነፍበት ታላቁ ነገር ሊሆን ነው። የኢየሱስ በመስቀል ላይ መሞት እንዴት የሰይጣን መሸነፊያ ሊሆን ይችላል?  ጥያቄ፡- ቆላ. 2፡13-15 አንብቡ፡ ሀ) እግዚአብሔር በሕይወት እንድንኖር ከማድረጉ በፊት ሁኔታችን እንዴት ነበር? ለ) እግዚአብሔር በዕዳው ጽሕፈት ላይ ምን አደረገ? ሐ) ይህ ምን ማለት ይመስላችኋል? መ) እግዚአብሔር ስእለቀችና በሥልጣናት ላይ ምን አደረገ?  በሦስተኛው ክፍለ ትምህርት ውስጥ ስለ ተሠገዎ ምሥጢር ለመረዳት ቆላ. 2፡13-15 በአጭሩ ማጥናታችን የሚታወስ ነው። ነገር ግን ክርስቶስ በተሰቀለ ጊዜ እንዴት አድርጎ ሰይጣንን እንዳሸነፈ ለመገንዘብ ይህንን ጥቅስ አሁን በዝርዝር ማጥናት ይኖርብናል። ቆላ. 2፡13-15 ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ እግዚአብሔር አዲስ መንፈሳዊ ሕይወትን እንደ ሰጠን ይናገራል። በበደላችንና ሥጋችንን ባለመገረዛችን ሞተን እንደ ነበርን ያሳስበናል። ይህም ከመዳናችን በፊት መንፈሳዊ ሕይወት እንዳልነበረንና ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት እንደማናደርግ ያስረዳል። ስለዚህ ከእግዚአብሔር የተለየንና እርሱንም የምንቃወም ነበርን። እኛ በዚህ መንፈሳዊ ሞትና በእግዚአብሔር ላይ መንፈሳዊ ተቃውሞ ላለን እግዚአብሔር ግን መንፈሳዊ ሕይወትን ሰጥቶ ኃጢአታችንን ይቅር አለን። እግዚአብሔር እንዴት ይህን አደረገ? ይህን ያደረገው ክርስቶስ በመስቀል ላይ በፈጸመው ተግባር ነው።  ጳውሎስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ የፈጸመው ተግባር ሁለት ደረጃ ዎች እንደ ነበሩት ይናገራል። አንደኛው ደረጃ፥ «በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዝ የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው» የሚለው ነው። በመጀመሪያው የግሪኩ ጽሑፍ «ደመሰሰው» የሚለው ቃል በጥቅም ላይ የዋለው ከቁራጭ ወረቀት ላይ ቀለምን ማጠብ ወይም አንዱ ሰው ለሌላው ያበደረውን የዕዳ ገንዘብ መሰረዝና መተው በሚለው የአነጋገር ዘይቤ ነበር። «የተጻፈ ዕዳ» የሚለው በመጀመሪያው ግሪክ የተመለከተው አገላለጽ የሳለዕዳነትን የምስክር ወረቀት የሚያሳይ ነበር። አንድ ሰው ብድር በሚወስድበት ጊዜ ዕዳ ያለበት መሆኑን የሚያሳይ ወረቀት ይፈርም ነበር። አበዳሪው ያለውን የብድር ገንዘብ አገልጋዮቹ ይህን ወረቀት በማሳየት ይሰበስቡ ነበር። ጳውሎለም ማለት የፈለገው ሁላችንም ባለዕዳዎች ነን ለማለት ነው። ዕዳው ምንድን ነው? ዕዳው ትእዛዝ አለው ይላል። ጳውሎስ የሚናገረው ስለ ሕጉ ነው። እርሱ የሚለው እግዚአብሔር ሕጉን የሰጠው ሰዎች እንደ መስፈርት አድርገው እንዲጠብቁት ነው። ሁላችንም ሕጉን የምጠበቅ ዕዳ አለብን። ነገር ግን ሕጉን አልጠበቅንም። የሰው ልጅ

የኢየሱስ ሞት በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን አስገኝቷል- ክፍል አንድ  Read More »

ኢየሱስ የራሱ ሰዎች እንድንሆን ከኃጢአት ዋጀን

This entry is part 70 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ትናንትና በተከታተልነው ትምህርት ክርስቶስ በመስቀል ላይ በፈጸመው ተግባር እግዚአብሔር መልሶ ከራሱ ጋር እንዳስታረቀን አስተውለናል። እኛ ጠላቶቹ ሳለን እግዚአብሔር ራሱ በእኛና በእርሱ መካከል ሰላምን ለመመሥረት የሚያስፈልገውን ሁሉ አደረገ። ነገር ግን እግዚአብሔር በራሱና በእኛ መካከል በክርስቶስ ሞት ሰላምን ብቻ አላመጣም። እኛን ነፃ አውጥቶ ደግሞም ወደ ራሱ ዋጅቶ መልሶ አመጣን። ይህ እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን ነፃ አውጥቶ የመቤዥትና መልሶ ወደ ራሱ የማምጣት ሁኔታ «መዋጀት» ይባላል።  ጥያቄ፡- ሮሜ 3፡24 አንብቡ። ኃጢአተኞች ሰማን አማካይነት እንደሚጸድቁ ተነገረ?  በሮሜ 3፡24 ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ በኢየሱስ ክርስቶስ በተገኘው ቤዛነት በኩል ኃጢአተኞች እንደሚጸድቁ መረጋገጡን ተናግሮአል። «ቤዛነት» ማለት ዋጋ ከፍሎ አንድን ሰው ነፃ ማውጣት ማለት ነው። ይህ ቃል የሚጠቅመውም ባሪያን በገበያ ሊሸጡና ነፃ ሲለቅቁ ካለው ሁኔታ ነው። እንደዚሁም በጦርነት ጊዜ ተይዘው ምርኮኛ የሆኑ እስረኞችን ዋጋ ከፍሎ ቤዛ ሰጥቶ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ የሚደረገውን ተግባር ለመግለጽ በጥቅም ላይ ይውላል።  ብሉይ ኪዳን የመቤዠትን አሳብ እንድንረዳው ጠቃሚ የግንዛቤ መሠረተ አሳብን ይሰጣል።  ጥያቄ፡- ዘፀአት 21፡28–30 አንብብ። አንድ በሬ ሰውን ወግቶ ቢገድል፥ የበሬው ባለቤት እንዴት ከሞት ይተርፋል?  ጥያቄ፡- ዘዳግም 7፡8 አንብብ። እግዚአብሔር እስራኤልን ከምን ዋጀው?  ጥያቄ፡– ሩት 4፡1-10 አንብቡ። ሀ) ቦዔዝ የሩትን የመጀመሪያ ባል የመሐሎንን የቤተሰብ ስም ለማስጠበቅ ብሎ የኑኃሚን ንብረት ለመቤዠትና ሩትን ለማግባት ምን አደረገ? ለ) ሩት 2፡20 እንብቡ። ኑኃሚን ቦዔዝን ምን ብላ ጠራችው?  ስለ መዋጀት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ያለው አሳብ ቢያንስ ሦስት ክፍሎች አሉት። የመጀመሪያው በዘፀአት 21፡28–30 ተገልጾአል። እግዚአብሔር ሕጉን በሰጠ ጊዜ አንድ በሬ ሰውን ወግቶ ቢገድል፤ በሬውና የበሬው ባለቤት፣ እንደሚገደሉ አዝዟል። ነገር ግን የበሬው ባለቤት ሕይወቱን ለመዋጀት ጉማ (ዋጋ ከፍሎ) ከሞት ሊያተርፍ ይችላል። ስለዚህ የበሬው ባለቤት ጉማ ቢከፍል ወይም የገንዘብ ቤዛ ቢከፍል ከሞት ይድናል። እንግዲህ በዚህ ክፍል እንደምንመለከተው፥ መዋጀት ማለት ዋጋ ከፍሎ ሕይወትን ማትረፍ ወይም መግዛት ማለት ነው።  ሁለተኛው «ስለ መዋጀት» የተሰጠው አሳብ በዘዳግም 7፡8 ውስጥ ይገኛል። እግዚአብሔር እስራኤልን ከግብፅ በኃይሉ ነፃ እንዳወጣቸው ማለትም እንደ ተቤዣቸው ይነግራቸዋል። ስለዚህ እግዚአብሔር እስራኤልን ከጠላት ኃይል ነፃ አወጣ፥ አዳነ። ነጻነቱ ስዋጋ ሲተመን እጅግ ውድ ነበር። ነገር ግን ዋጋው ለጠላቱ አልተከፈለም። እግዚአብሔር እስራኤልን ከፈርዖን አልገዛም። የተከፈለው እጅግ ውድ የነበረው ዋጋ የእስራኤልን በኩራት ለማትረፍ በእነርሱ ፈንታ በፋሲካ ዕለት የተሠዉት የበጎች ሕይወት ነበር። ሆኖም ዋጋው ለእስራኤል ጠላት ለፈርዖን አልተከፈለም። በዚህ ክፍል መዋጀት ማለት ዋጋ በመክፈል ከጠላት እጅ ነፃ ማውጣት ማለት ነው። ነገር ግን ዋጋው የተከፈለው ለጠላት አይደለም።  ሦስተኛው «የመዋጀት» አሳብ የሚገኘው በሩት 4፡1-10 ውስጥ ነው። ሩት ምዕራፍ 4 የሩት፥ የቦዔዝና የኑኃሚን ታሪክ ማሳረጊያ ምዕራፍ ነው። የሩት የመጀመሪያው ባል መሐሎን ሩት ልጅ ሳትወልድ ሞተ። ይህም የሚያሳየው ሩትና ኑኃሚን ለቤተሰባቸው ንብረት ወራሽ አልነበራቸውም ማለት ነው። የቤተሰቡን መሥመር ጠብቆ የሚወርስ አልነበረም። ሆኖም ቦዔዝ የኑኃሚን የመጀመሪያው ባልዋ የነበረው የአቤሜሌክ የሥጋ ዘመድ ነበር። በሩት 2፡20 ውስጥ ኑኃሚን ቦዔዝን «ይህ ሰው የቅርብ ዘመዳችን ነው እርሱም ሊቤዠን ከሚችሉት አንዱ ነው» አለች። ምክንያቱም ቦዔዝ የቅርብ ዘመድ በመሆኑ ሊቤዥ ስለሚችል የአቤሜሌክንና የመሐሎንን ንብረት በስማቸው ሊገዛ የተገባ ሰው ነበር። በዚህ ጊዜ ደግሞ ሩትን ያገባታል። እንግዲህ ከቦዔዝና ከሩት ጋብቻ የሚወለዱ ልጆች በሕግ ከአቤሜሌክና ከመሐሎን ዘር እንደ ተገኙ ተደርገው ይቆጠራሉ። እነርሱም የአቤሜሌክንና የመሐሎንን ስም ይዘው፥ የአቤሜሌክንና የመሐሎንን ንብረት ይወርሳሉ፡ ስለዚህ ንብረቱ ከቤተሰብ ውጭ ተሽጦ እንዳይተላለፍ ቦዔዝ ንብረቱን ገዛ፡ ንብረቱን በቤተሰቡ ውስጥ ለማስቀረት ብሎ ገዛው። እዚህ ላይ እንደምንረዳው የመቤዥት ወይም ከፍሎ የማስቀረት ተግባር መፈጸም ያለበት በቤተሰብ አባል ነው። በዚህ ምንባብ መሠረት መቤዥት ማለት የቤተሰብ አባል የሆነ ሰው ዋጋ ከፍሉ የቤተሰብ የሆነው ንብረት ከእጅ እንዳይወጣና ለውርስ እንዲበቃ ማዳን ነው።  ከእነዚህ ክፍለ ምንባቦች እንደምናጤነው፥ በብሉይ ኪዳን ውስጥ መቤዠት ማዳን ወይም መታደግ ይሆናል። ብዙ ጊዜ ግን ነፃ ማውጣት ወይም ማስለቀቅ የሚፈጸመው ዋጋን በመክፈል ነው። አንደኛው ጊዜ ግን ይህ የመቤዥት፥ ነፃ የማውጣትና የመታደግ ነገር በቤተሰብ አባል ይፈጸማል። እነዚህ በብሉይ ኪዳን ውስጥ የነበሩ አላቦች በአዲስ ኪዳን ውስጥ ለሚገኘው የክርስቶስ ኃጢአተኞችን የመዋጀት ትምህርት መሠረቱን የሚጥሉ ናቸው፡፡  ጥያቄ፡- ሉቃስ 24፡21 አንብቡ ሀ) ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ ምን ይፈጽማል ብለው ተስፋ አደረጉ? ለህ ይህንን ባሉ ጊዜ ምን ማለታቸው ይመስላችኋል?  ጥያቄ፡- ገላ 3፡13-14 አንብቡ። ደግሞም ገላ. 4፡4-5 ተመልከቱ። ) ክርስቶስ ከምን ተቤዠን? ለ) ክርስቶስ እንዴት ተቤዥን? ሐህ ክርስቶስ ስለ ተቤዥን ምን ጥቅም እናገኛለን?  ጥያቄ፡– ኤፈሶን 1፡7 አንብቡ። ሀ) በምን በኩል መቤዠትን እናገኛለን? ለህ ይህን መቤዥት በማግኘታችን ምን እናገኛለን?  ጥያቄ። ቲቶ 2፡13-14 አንብቡ። ሀ) ኢየሱስ እኛን ለመዋጀት ምንን ለጠ? ለ) ኢየሱስ ከምን ዋጀን? ሐ) መዋጀት ለእኛ ምን ጠቀመን?  ጥያቄ፡- ዕብራውያን 9፡12 አንብቡ። ክርስቶስ መዋጀትን በምን አገኘ?  ጥያቄ፡- 1ኛ ጴጥሮስ 18-19 አንብቡ። ሀ) በምንድን ነው ያልተዋጀነው? ለ) በምን ተዋጀን?  ጥያቄ፡- ማርቆስ 10፡45 አንብቡ። የሰው ልጅ ሕይወቱን የሰጠው ለምንድን ነው?  ጥያቄ፡- 1ኛ ጢሞ. 2፡6 አንብቡ። ክርስቶስ ለሰው ሁሉ ምን አደረገ?  ጥያቄ፡- ራእይ 5፡9-10 አንብቡ። ሀ) ክርስቶስ የፍርዱን መጽሐፍ የመክፈት ሥልጣን እንዴት ተሰጠው (ቁጥር 9)? ለ) የክርስቶስ ድርጊት ውጤት ምን ይሆናል (ቁጥር 10)?  ኢየሱስ ከመምጣቱ በፊት የአይሁድ ሕዝብ ከሮማውያን እጅ ነፃ የሚያወጣቸው ይሹ ነበር። በሉቃስ 24፡21 የምናገኛቸው ሁለት ደቀ መዛሙርት ወደ ኤማኡስ ይጓዙ በነበሩበት ጊዜ፥ ኢየሱስ እስራኤልን ነፃ እንዲያወጣ ተስፋ እንደ ነበራቸው ይወያዩ ነበር። በዚህም የእስራኤልን ሕዝብ ከርማውያን ጭቆና ነፃ እንዲያወጣና እስራኤልን ነነ መንግሥት አድርጎ እንዲያቋቁም አስበው ነበር። ምናልባትም ዘካርያስና ሐና ስለ ሕፃኑ ኢየሱስ የተነበዩት ትንቢት ተመሳሳይ አሳብን ያዘለ ሳይሆን አይቀርም (ሉቃስ 1፡68፤ 2፡38)፡፡ እነዚህ አይሁዶች ነፃ አውጪው የሚያመጣው ነጻነት በሞቱ አማካይነት መሆኑን አልገመቱም ነበር። ዳሩ ግን ኢየሱስ ያመጣው መቤዠት አይሁዶቹ ከገመቱት ነጻነት የላቀ ነበር። አዲስ ኪዳን በኢየሱስ ስለ ተገኘው መዋጀት የሚሰጠው ትምህርት ምንድን ነው?  አዲስ ኪዳን በመጀመሪያ ደረጃ ስለ ኢየሱስ መቤዠት የሚያቀርበው ትምህርት ክኃጢአት፥ ከኃጢአት ቅጣትና ከክፉ ውጤቶቹ እንዳዳነን ነው። ገላ. 45 ኢየሱስ ከሕግ በታች ያሉትን ዋጀ ይላል። እንደዚሁም ገላ. 3፡13 ከሕግ እርግማን ዋጀን ይላል። የእግዚአብሔርን ሕግ ካለመጠበቃችን የተነሣ የሕግ እርግማን ለእያንዳንዳችን የሚገባ ቅጣት ነበር። የእግዚአብሔርን ሕግ ባለሞጠበቃችን ምክንያት ይደርስብን ከነበረው ቅጣት ኢየሱስ ዋጀን። ኤፌ. 1፡7 በደሙ በተደረገ ቤዛነት የበደላችንን ስርየት የኃጢአታችንን ይቅርታ አገኘን ይላል። (እንዲሁም ቆላ. 1፡14 ይመልከቱ፡፡) ቲቶ 2፡14 ደግሞ፥ እኛን ከዐመፅ ሁሉ ሊቤዠን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን ሰጠ ይላል። ስለዚህ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ በሞተ ጊዜ በእርሱ የሚያምኑትን ሁሉ ከኃጢአት ቅጣትና ከኃጢአት ክፉ መዘዞች ሁሉ ዋጀ፡፡  ግን ኢየሱስ ክርስቶስ ከኃጢአት ብቻ ነፃ አላወጣንም። አዲስ ኪዳን እንደሚያስተምረን ከሆነ የክርስቶስ የመቤዠቱ ሥራ በተጨማሪ እኛን ነፃ አውጥቶ ከበለጸገ ውርስ ጋር የእግዚአብሔር የራሱ ሕዝብ ለመሆን አብቅተናል።  በገላ. 3፡14 የክርስቶስ የመቤዥት አንዱ ጥቅም፥ አሕዛብ ለአብርሃም የተሰጠውን የበረከት ተስፋ ተካፋዮች መሆናቸውን ነው ይላል። በተለይም የመንፈስ ቅዱስ ተስፋ ተካፋይ መሆናቸው ላይ ነው። እንዲሁም በገላ. 4፡5፣ «ከክርስቶስ መዋጀት ወይም መቤዠት የተነሣ የልጅነትን ሙሉ መብት ሰጠን» ይላል። በኢየሱስ ለሚያምኑት ሁሉ እግዚአብሔር የእርሱ የሆነው ሁሉ ወራሾች የመሆንን መብት ሰጣቸው በማለት ጽፎአል። በቲቶ 2፡14 ክርስቶስ ከዐመፃ አንጽቶ የራሱ ሕዝብ ሊያደርገን የተቤዠንና የዋጀን መሆኑን ያረጋግጣል። በራእይ 5፡19 ከነገድ ሁሉ፥ ከቋንቋም ሁሉ፥ ከወገንም ሁሉ፥ ከአሕዛብ ሁሉ መንግሥትና ካህናት ሆነው በምድር ላይ ይነግሥ ዘንድ በጉ ዋጃቸው ይላል። በክርስቶስ የሚያምኑ ሁሉ ዛሬም ሆነ ለዘላለም የበለጸገ ውርስ ባለቤቶች ይሆኑ ዘንድ የክርስቶስ ቤዛነት ሁሉንም ዋጀ ይላል።  አዲስ ኪዳን ስለ ክርስቶስ መቤዠት የሚያስተምረን ሦስተኛው

ኢየሱስ የራሱ ሰዎች እንድንሆን ከኃጢአት ዋጀን Read More »

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀን 

This entry is part 69 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

በማስታረቅ ሥነ ሥርዓት (በሽምግልና) ላይ ተሳትፋችሁ ታውቃላችሁ? ምናልባትም በሁለት ሰዎች መካከል ያለ ግንኙነት ወደ ቀድሞው ስፍራዉ ተመልሶ እንዲታደስ ሸምግላችሁ ይሆናል። ወይም እናንተው ራሳችሁ ከሰዎች ጋር ተጣልታችሁ ይሆናል። ከዚህ የተነሣ በእርቅ ምክንያት በተለያዩ ሽማግሌዎች ፊት ቀርባችሁ ይሆናል።  ጥያቄ፡– ስለተሳተፋችሁበት የእርቅ ሥነ ሥርዓት ዓይነት አስቡ። ሀ) ሁለት ጸበኞች ሰአስታራቂ ሽማግሌዎች ፊት ሲቀርቡ ከእርቁ በፊት አንዳቸው ስለሌላዉ ምን ዓይነት ስሜት ይኖራቸዋል? ለ) ከእርቅ ሥነ ሥርዓት በኋላስ እርስ በር አንዳቸው ለሌላው የሚኖራቸው ስሜት ምን ይሆናል? ሐ) በእርቅ ሥነ ሥርዓ ምን እንዲፈጸም ይፈለጋል?  የማስታረቅ ሥነ ሥርዓት የሚካሄደው ሁለት የተጣሉ ሰዎች ታርቀa የቀድሞ ሰላምና ወዳጅነት ወደ ቦታው እንዲመለስ ለማድረግ ነው። ሁለ፡ ጸበኞች መራር ጠላትነት ቢኖራቸውም፥ ከእርቁ ሥነ ሥርዓት በኋ በመካከላቸው ሰላም ይሰፍናል። መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረ ከኃጢአታችን የተነሣ እኛ ራሳችንን የእግዚአብሔር ጠላቶች አድርገን ነበ (ሮሜ 5፡10፤ ቆላ. 1፡21፤ ያዕ. 4፡4)። ደኅንነትን ለማግኘት ዳግማ የእግዚአብሔር ወዳጆች መሆን ይገባናል። እንዲሁም ደኅንነትን ለማግኘ፡ ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖረን ሰላም መታደስ ይኖርበታል። ስለዚህ ደኅንነ ኃጢአተኞች በሆኑ ሰዎችና በቅዱሱ እግዚአብሔር መካከል ያለውን እር ማጠቃለል አለበት።  ጥያቄ፡ ሮሜ 5፡1 አንብቡ። በኢየሱስ በእምነት ስለ ጸደቅን ምን እናገኛለን ለዚህ መልስ ለማግኘት አዲሱ መደበኛ ትርጉም ሊረዳችሁ ይችላል።  ጥያቄ፡- ሮሜ 5፡10-11 አንብቡ። ሀ) ጠላቶቹ ሆነን ሳለን እግዚአብሔር ለእኛ ምን አደረገለን (ቁጥር 10)? ለ) በማን አማካይነት እርቅን አገኘን (ቁጥር 11)?  ጥያቄ፡- 2ኛ ቆሮ. 5፡18 አንብቡ። ሀ) እግዚአብሔር ምን አደረገልን (ቁጥር 18)? ለ) እግዚአብሔር ምን ሰጠን?  ጥያቄ፡- 2ኛ ቆሮ. 5፡19 አንብቡ። ሀ) እግዚአብሔር በክርስቶስ አማካይነት ለዓለም ምን አደረገ? ለ) የዚህ የእግዚአብሔር ሥራ ውጤትስ ምንድን ነው? ሐ) ከዚህ የተነሣ እግዚአብሔር የጣለብን ኅላፊነት ወይም ሥራ ምንድን ነው?  ጥያቄ፡- 2ኛ ቆሮ. 5፡20-21 አንብቡ። እኛ የእግዚአብሔር አምባሳደር እንደ መሆናችን መጠን መልእክታችን ምን መሆን አለበት? 7ኛ ጥያቄ፡- ቆላ. 1፡21-22 አንብቡ። ሀ) ከክፉ ባሕሪያችን የተነሣ ቀድሞ ምን ነበርን? ለ) እግዚአብሔር እንዴት አስታረቀን? ሐህ የዚህ እርቅስ ውጤት ምንድን ነው?  በሮሜ 3፡21–4፡25 ድረስ ሐዋርያው ጳውሎስ ሰው በእምነት እንደሚጸድቅ ይገልጻል። ከእግዚአብሔር ጋር የመታረቅ ውጤት ምንድን ነው? ጳውሎስ በምዕራፍ 5 የመጀመሪያ ውጤት አድርጎ ያቀረበው ሰላምን ነው። አሮጌው የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም «ሰላምን እንያዝ» ይላል። አዲሱ ትርጉም ግን፥ «ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም አለን» ነው የሚለው፥ ይህም የበለጠ የጳውሎስን አሳብ ያብራራዋል። ከሰዎች ኃጢአት የተነሣ፥ በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል ጠላትነትና ጦርነት ነበር። በሮሜ 5፡10 ውስጥ እኛ የእግዚአብሔር ጠላቶች ነን ይላል። በቆላ. 1፡21 ደግሞ ከክፉ ሥራችን የተነሣ ከእግዚአብሔር የተለየን ጠላቶቹ እንደ ነበርን ይገልጻል። በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአት በመሥራት ቅድስናውን ጥለናል። ነገር ግን ጳውሎስ በሮሜ 5 ውስጥ አሁን የእግዚአብሔር ወዳጆች መሆናችንን ይናገራል። ስለዚህ አሁን ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም አለን። እንዴት የእግዚአብሔር ወዳጆች ለመሆን በቃን? ይህ ሰላም እንዴትስ ሊታደስ ቻለ? በሮሜ 5፡10-11 እኛ ጠላቶቹ ሳለን እግዚአብሔር «እርቅ» በተባለው በክርስቶስ ሞት ሥራ አማካይነት፥ ሰላምን በራሱና በእኛ መካከል አመጣ ይላል። እርቅ ምንድን ነው? እርቅ ሁለት ጠላት የነበሩ ሰዎች ወደ ሰላምና ወዳጅነት ሲመጡ የሚፈጸመው ተግባር ነው። እዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ጊዜ እርቅ፥ ለዚህ ክንዋኔ በሚዘጋጅ ሥነ ሥርዓት ሲከናወን እንመለከታለን።  ጥያቄ፡- በ1ኛው ጥያቄ ውስጥ ስለ ገለጻችሁት የእርቅ ሥነ ሥርዓት አስቡ። ሀ) በዚያ የእርቅ ሥነ ሥርዓት ላይ ማን በማን ተቆጥቶ ነበር? ለ) በሁለቱም በኩል ስሕተት ነበር? ወይስ ስሕተቱ የአንዱ ሰው ነበር? ሐህ በሁለቱ መካከል ሰላም እንዲሆን፥ ሁለቱም ምን እንዲያደርጉ ሽማግሌዎቹ ወሰኑ? ሁለቱም አንድ ነገር እንዲያደርጉ ታዘዙ ወይስ አንዱ ሰው ብቻ አንዳች እንዲያደርግ በየኑበት? መ) እርቁ በሁለቱም መካከል ፍጹም ሰላም መመሥረት ቻለ? ወይስ የምትጠረጥሩት ድብቅ የሆነ ቂም በቀል ለእርስ በርስ አስከተለ?  መልካም ምሳሌ የሚሆን የእርቅ ተግባር አንድ ጊዜ በራሴው ግቢ ውስጥ አጋጥሞኛል። የራሴ ግቢ ጠባቂዎች የነበሩ ሁለት ዘበኞች እርስ በርስ ተጣሉ። ጥሉ እንደ ተጀመረ ሦስተኛው ዘበኛ ጥሉን አበረደ። ነገር ግን ሲጣሉ በነበሩት በሁለቱ ዘበኞች መካከል የነበረው ቅራኔ ቀጥሏል። የእነዚህን ሰዎች ቅራኔ ለማስቀረትና ለማስታረቅ በርከት ያሉ የአካባቢአችን ሽማግሌዎች ተጠሩ። ሁሉም ቁጭ ብለው ስለተከሰተው ችግር ተወያዩ። ሽማግሌዎቹም ችግሩን ከሁለቱም አቅጣግ ከመረመሩ በኋላ፥ ሁለቱም ሰዎች ለተከሰተው ጥል በከፊል ኃላፊዎች መሆናቸውን ገለጹ። ሁለቱም ጸበኞች ጥሉን ለማብረድና ቁጣቸውንም ለማስታገስ አንድ ነገር እንዲናገሩ ወይም እንዲያደርጉ ታዘዙ። ሁለቱም ሰዎች ይህንን ውሳኔ በመቀበላቸው ምክንያት በመካከላቸው ሰላም ሰፈነ። ሁለቱም ታረቁ። ከጥቂት ሳምንታት በኋላ አብረው እየተሳሳቁ ሲቀላለዱ ተመለከትኩ። ከእርቅ የተነሣ ጠላቶች የነበሩት ወዳጆች ሊሆኑ ቻሉ።  በርሜ 5፡10 እና በቆላ. 1፡21 እንደተጻፈው በተመሳሳይ ሁኔታ እነዚህ ሁለት ዘበኞች ይጣሉ እንደ ነበረ ሁሉ፥ እኛም በእግዚአብሔር ላይ ኃጢአት ስለ ሠራን ጠላቶቹ ሆነን ነበር። በጥንቃቄ ልታስቡት የሚገባው ነገር፡ የእግዚአብሔር ጠላቶች በሆንን ጊዜ፥ ስሕተቱ ሁሉ በእኛ ላይ ተጣለ። እኛ በእግዚአብሔር ላይ ኃጢአት ሠራን እንጂ እግዚአብሔር እኛን በምንም ነገር አልበደለንም። ብዙ ጊዜ ሁለት ሰዎች ተጣልተው ወደ ሽምግልና መድረክ በሚመጡበት ጊዜ በሁለቱም ባላንጣዎች ላይ ስሕተት ይገኛል፡ ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ በአንዱ ሰው ላይ ትልቅ ስሕተት ሲገኝ፡ በሌላው ላይ ያነሰ ሊሆን ይችላል። ቢሆንም አንዱ ሰው ሌላውን የበደለበት ሁኔታ ይኖራል። ከጠቀስናቸው ዘበኞች መካከል አንደኛው ጥል ጀምሮ ትል ስሕተት አድርጎአል። ሽማግሌዎቹ (አስታራቂዎቹ) ሌላውም ዘበኛ ቢሆ’ ትንሽ ስሕተት መፈጸሙን አልሸሸጉም። ስለዚህ በሁለቱም በኩል ሰላማ እንዲሰፍን፥ ሁለቱም አንድ ነገር መናገር ወይም ማድረግ ነበረባቸው። ነገ ግን እግዚአብሔር ምንም ዓይነት ስሕተት ወይም በደል በእኛ ላይ በፍጹ አድርጎ አያውቅም። ይልቅስ ስሕተትና፥ በደለን ሁሉ የፈጸምነው እኛ ራሳች ነን። ስለዚህ በስሕተታችንና በበደላችን ልንገሠጽ የሚገባን እኛ ነን።  በሠራነው ስሕተትና በዴል የምንወቀስ ብንሆንም፥ በእኛና በእግዚአብሔ መካከል ሰላም እንዲሆን የጣረ ማን ነው? እግዚአብሔር ሥራውን ሁ ሠርቷል። በሮሜ 5፡10 የተጻፈው ቃል በእግዚአብሔር ልጅ አማካይነ ታርቀናል ይላል። በሮሜ 5፡11 ደግሞ፥ እርቅን ያገኘነው በጌታችን በኢየሱ ክርስቶስ አማካይነት ነው ይላል። በ2ኛ ቆሮ. 5፡18 እግዚአብሔር በክርስቶ አማካይነት ከራሱ ጋር አስታረቀን በማለት ይገልጻል። በ2ኛ ቆሮ. 5፡19 እግዚአብሔር ዓለምን በሞላ በክርስቶስ አማካይነት ከራሱ ጋር አስታረ ሲል ይናገራል። የዚህ ሁሉ ውጤት የሚያመለክተው እግዚአብሔ ኃጢአታችንን በእኛ ላይ አለመቁጠሩን ነው። በቆላ. 1፡22 በሥጋው ሰውነ በሞቱ እግዚአብሔር እኛን ከራሱ ጋር አስታረቀ ሲል ጽፎአል። ምን እንኳን በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአትን በመሥራት በእግዚአብሔር ላ ስሕተትን ሁሉ ብንፈጽምና ራሳችንን ጠላቶቹ ብናደርግም፥ እግዚአብሐ ሰላምን ሊያመጣልንና ግንኙነታችንን ለማደስ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶ አማካይነት ሥራውን ሁሉ ሠርቷል።  እዚህ ላይ በኢትዮጵያ ውስጥ የምንመለከተው እርቅን የማምጣት ተግባርና ሥነ ሥርዓት እግዚአብሔር እርቅን ለማምጣት በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ለሠራው ተግባር መልካም ምሳሌ ነው። ይሁን እንጂ፣ አንዳንድ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገባ ልዩነቶችም አሉ። በአንዳንድ የእርቅ ሥነ ሥርዓት ላይ፥ ሁለቱም የተጣሉ ሰዎች የሆነ ስሕተት የተሳሳቱ በመሆናቸው፥ ሁለቱም ሰላም ለማምጣት የሚያደርጉት ተግባር አለ። ነገር ግን በእግዚአብሔር የማስታረቅ ተግባር፥ በኃጢአታችን ውስጥ ስሕተቶችን ሁሉ ፈጽመናል። ይህ ሆኖ ሳለ ሰላምን ሊያድስልን እግዚአብሔር በክርስቶስ ሞት አማካይነት ሁሉን ፈጽሞልናል።  በእግዚአብሔር ማስታረቅና እንደተመለከትነው ባለ የሰብአዊ የማስታረቅ ሥነ ሥርዓት መካከል ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ልዩነት አለ። የማስታረቅ ሥነ ሥርዓት ተደርጎ እንኳን ሲያበቃ፥ አንዳቸው በሌላው ላይ በልባቸው ውስጥ ቁጣና መራርነት ያለው ስሜት ሊኖር ይችላል። በሚታረቁበት ጊዜ ሁለቱ ሰዎች እርስ በርስ ይቅር የተባባሉና ግንኙነታቸውም በሙሉ እንደ ታደሰ ሊያስመስሉ ይችላሉ። በውስጣቸው ግን አንዱ ለሌላው ጠላቱ እንደሆነ ሊሰማቸው ይችላል። በእግዚአብሔር ዘንድ በሚደረገው እርቅ መሠረት ግን እርሱ በሚያስታርቃቸው ላይ የቁጡነትም ሆነ የመራርነት ሰማት አያድርበትም። እግዚአብሔር ከራሱ ጋር ካስታረቀን በኋላ፥ ፈጽሞ ይቅር ይለናል፥ ኃጢአታችንንም ጨርሶ አያስበውም። በቆላ. 1፡22፣ «ነውርና ነቀፋ

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀን  Read More »

የኢየሱስ ሞት የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቁጣ ለማርካት (ለማብረድ) የቀረበ መሥዋዕት ነው። 

This entry is part 68 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

በትናንትናው ትምህርታችን ኢየሱስ በደላችንንና የኃጢአታችንን ቅጣት የተሸከመ ፍጹም ቤዛ መሥዋዕት መሆኑን ተገንዝበናል። አዲስ ኪዳን የኢየሱስ መሥዋዕትነት ኃጢአታችንንና የከፋ ውጤቶቹን እንዴት እንዳስወገደ ለመግለጽ በሌሎች ሥዕሎችና አሳቦች ይጠቀማል። ዛሬና በሚቀጥለው ሳምንት ከእነዚህ ምስሎችና አሳቦች አራቱን እናጠናለን። ለዛሬው የኢየሱስ መሥዋዕትነት እግዚአብሔር በኃጢአት ላይ የነበረውን ቅዱስ ቁጣ እንዴት እንዳበረደው እንመለከታለን።  ጥያቄ፡– ኤር. 2፡12 አንብቡ። እግዚአብሔር ፍትሕ በማይኖርበት ጊዜ ምን አደርጋለሁ አለ?  ጥያቄ፡ ሕዝ. 24፡13 አንብቡ። እስራኤላውያን ራሳቸውን ከርኩሰታቸው ባለማንጻታቸው ምክንያት ምን ደረሰባቸው? ጥያቄ፡– 2ኛ ነገ 23፡26 እንብቡ። ከምናሴ ኃጢአት የተነሣ የእግዚአብሔር ምላሽ ላይሁዳ ምን ነበር?  ጥያቄ፡ ሰአ. ኤር. 3፡42-43፡- እግዚአብሔር እስራኤልን ለምን ወደ ምርኮኝነት ላካቸው?  የሰዎች ኃጢአት የእግዚአብሔርን የጽድቅ ቁጣ እንደሚቀሰቅስ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል። በኤር. 21፡12 ውስጥ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ሲያስጠነቅቅ ክፋት ከቀጠለ፥ ለተበዘበዙትም ፍትሕ ካልሰፈነ ቁጣው እንደ እሳት እንደሚቀጣጠል ይነግራቸዋል። በሕዝቅኤል 24፡18 ውስጥ በርኩሰታቸው ስለ ቀጠሉ መዓቱን እንደሚያመጣ እግዚአብሔር ለእስራኤል ተናግሯል። ምንም እንኳን ንጉሥ ኢዮስያስ የይሁዳ መልካም ንጉሥ ቢሆንም፥ በ2ኛ ነገ. 23፡26 ውስጥ በቀድሞው ንጉሥ በምናሴ ኃጢአት ሳቢያ እግዚአብሔር ሕዝቡን በጽድቅ ቁጣው የተቆጣው መሆኑን ለእስራኤል ተናግሮ ነበር። በሰቆ. ኤር. 3፡42-43 እንደተገለጸው እግዚአብሔር እስራኤልን ወደ ምርኮ የላከው በኃጢአታቸው ላይ የጽድቅ ቁጣ ስለ ነሐደ ነበር። ትናንትና በሮሜ 1፡18 በክፉዎችና በዐመፀኞች፥ ነገር ። የእግዚአብሔርን እውነት እያወቁ ቸል በሚሉትና በማይታዘዙት ላይ የእግዚአብሔር ቅዱስ ቁጣ እንደሚወርድ ተገንዝበናል። ሰዎች ኃጢአትን በሚሠሩበት ጊዜ፥ እግዚአብሔር በቅዱስ ቁጣው በኃጢአታቸው ላይ ይቆጣል።  የእግዚአብሔር ቁጣ ሲባል እግዚአብሔር ራሱን ስቶ ወይም ግንፍል ብሎት ይቆጣል ማለት አይደለም። የእግዚአብሔር ቁጣ፥ እግዚአብሔር ኃጢአትን የሚሠሩ ሰዎችን ስለ ጠላ ይወርድባቸዋል ማለትም አይደለም። የእግዚአብሔር ቁጣ፥ እግዚአብሔር በኃጢአት ላይ የሚሰጠው የጽድቅ ምላሽ ነው። ይህን የሚያደርገው ኃጢአት የከፋና አጥፊ መሆኑን ስለሚነዘብ ነው። ብዙ ጊዜ ግን እኛ የሰው ልጆች የምንቆጣው ሰዎች ወይም ሁኔታዎች የሚያደርሱብንን ድርጊት በራስ ወዳድነትና በክፉ አስተሳሰብ ስለምንመለከተው ነው። ሰዎች የእኛ ሊሆን የሚገባውን ዕቃ በሚወለዱብን ጊዜ እንቆጣለን። እንዲሁም ሰዎች የምንፈልገውን ነገር ስላልሰጡን፥ ወይም የምንሻውን ስላላደረጉልን እንቆጣለን። እግዚአብሔር ግን ራሱን ወዳድ ስላልሆነ እንዲህ ባሉት ነገሮች አይቆጣም። እግዚአብሔር የሚቆጣው ለእኛ እጅግ የሚጠቅመንን ነገር ኃጢአት ሲያበላሽብን ሲያይ ነው። እግዚአብሔር ስለሚወደን የእኛ ኃጢአት ሌሎች ሰዎችን፥ ካሌሎችና ከእርሱ ጋር ያለንን ግንኙነት፥ ፍጥረትንና ራሳችንን ሲጎዳ ያዝናል። ስለሆነም እግዚአብሔር በኃጢአትና ኃጢአት በሚያስከትለው ጥፋትና ውጤቶቹ ላይ ይቆጣል።  አንዳንድ ጊዜ እኛም ብንሆን እግዚአብሔር የጽድቅ ቁጣውን እንደሚቆጣ ሁሉ፥ እኛም ትንሽ ትንሽ የእርሱን የመሰለ ቅዱስ ቁጣ የምንቆጣበት ጊዜ አለ። እኔም አንድ ጎልማሳ ታዳጊዋን ልጃ ገረድ አስገድዶ ሕግዋን መግሰሱን በሰማሁ ጊዜ ይህን የመሰለ ቁጣ ተሰምቶኛል። ሰውዬውን ወይም ልጃገረዲቱን አላውቃቸውም ነበር። ነገር ግን በጣም ተናድጄ ነበር። የተቆጣሁበትም ምክንያት ይህ ሰው የታዳጊዋን ልጃገረድ ሕይወት ስላበላሸባት ነው። በዚህም ሰውዬው ንጽሕናዋን አጉድፎታል። በቀረው ዕድሜዋ በአካልና በስሜት ጎድቷታል። ስለዚህ የሰውዬው ኃጢአት አናደደኝ። ይህ ሰው በወንጀሉ ተከሶ ወደ ፍርድ ቤት ቢቀርብና ዳኛው፥ «ይህን ወንጀል በይቅርታ ስላለፍኩት ሰውዬው ያለቅጣት ነፃ ይለቀቅ» ብሎ ቢለቀው ኖሮ ምን ይሰማኝ ነበር? በጣም ይነደኝና ፍትሕም መጓደሉን አስብ ነበር። የከፋ ኃጢአት መቀጣት ይኖርበታል። አንድ ወንጀለኛ ኃጢአቱ ከመቀጣቱ በፊት፡ ነፃ ሊለቀቅ አይገባም። የጽድቅ ቁጣን ለማስታገስ ኃጢአትን መቅጣት ያሻል። በዚሁ መንገድ እግዚአብሔር በኃጢአታችን ላይ የጽድቅ ቁጣን ይቆጣል። ይህ ከመፈጸሙ በፊት እንዲህ በቀላሉ ይቅር አይለንም። ስለዚህ የእግዚአብሔርን ቁጣ ለማብረድ ኃጢአት መቀጣት አለበት።  ጥያቄ፡- ዕብራውያን 9፡5 አንብቡ። በብሉይ ኪዳን የማደሪያው ድንኳን ውስጥ ካታቦቱ በላይ የነበሩ መላእክት ምንን ሸፍነው ነበር?  ጥያቄ፡- ሉቃስ 18፡18 አንብቡ። ቀራጩ በጸሎት ላይ ምን አለ?  በብሉይ ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር ይቅርታ እንደ ሰጣቸው፥ እግዚአብሔር በኃጢአት ምክንያት የሚያወርደው ቅዱስ ቁጣ መታገስ እንዳለበት ያውቁ ነበር። በድንኳኑ ውስጥ በነበረው ቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ይገኝ በነበረው በኪዳኑ ታቦት ላይ መክደኛ ነበር። ከኪዳኑ ታቦት በላይ የነበሩ መላእክት ይህንን መክደኛ ይጋርዱ ነበር። የዚህ መክደኛ ስም «የስርየት መክደኛ» (ማስተላለፊያ) ነው። ስፍራው የስርየት መክደኛ ቃል በቃል ሊተረጎም፥ ምሕረት የሚሰጥበት ቦታ ማለት ነው። ይህም የእግዚአብሔር ቁጣ የሚበርድበት ቦታ ነው። በየዓመቱ በስርየት ቀን (ዘሌዋ. 16)፥ ሊቀ ካህናቱ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ገብቶ በዚህ «በስርየት መክደኛ» ላይ ደም ይረጫል። ከዚህ ከመሥዋዕቱ ደም የተነሣ በሕዝቡ ኃጢአት ላይ የነበረው የእግዚአብሔር የጽድቅ ቁጣ ለአንድ ሌላ ዓመት ይበርዳል። በዚህ ምክንያት ሕዝቡም የእግዚአብሔርን ምሕረት ያገኝ ነበር። የስርየቱ መክደኛ የምሕረቱ መቀመጫ ነው። ምክንያቱም የእግዚአብሔር የጽድቅ ቁጣ ማስታገሻ ስፍራ ስለነበረ ነው። በሉቃስ 18፡13 ውስጥ ኢየሱስ ስለ ፈሪሳዊውና ስለ ቀራጩ ታሪክ ተናግሮ ነበር። ቀራጩ በጸለየ ጊዜ ኃጢአቱ ይሰማው ስለ ነበረ በትሕትና መንፈስ ጸለየ። እንዲህ አለ፥ «እግዚአብሔር እኔን ኃጢአተኛውን ይቅር በለኝ።» ይህ ቃል በአማርኛው ለየት ያለ ቢሆንም በመጀመሪያው ግሪክ «ይቅር በለኝ» የሚለው ቃል «የምሕረት መክደኛ» ከሚለው ጋር ተመሳሳይ ነው። ቀረጥ ሰብሳቢው የጸለየው «በምሕረት መቀመጫው ላይ ያለው ደም በኃጢአቴ ላይ የተቃጣውን የጽድቅ ቁጣህን ያስታግስልኝ» በማለት ነበር። ቀራጩ እግዚአብሔር በእርሰ ኃጢአት ላይ የጽድቅ ቁጣ እንደሚቆጣ ገብቶታል። እግዚአብሔር የራሱን ቁጣ ለማስታገስ በምሕረት መቀመጫው ላይ ባለው ራሱ ባዘጋጀው ደም አማካይነት የኃጢአት ይቅርታ እንደሚያገኝ ያምን ነበር።  ነገር ግን፥ በብሉይ ኪዳን ጊዜ በሚደረገው መሥዋዕት በመሠዊያው ላይ ይፈስ የነበረው ደም ኃጢአትን በጊዜያዊነት የሚሸፍን ብቻ ነበር እግዚአብሔር በኃጢአት ላይ ያለው የጽድቅ ቁጣ እስከ መጨረሻው ድረ በእንስሳ ደም ረክቶ ሊበርድ አይችልም ነበር። ስለዚህ እግዚአብሔt በኃጢአት ላይ ያለውን ቁጣ ለመጨረሻው ለማቆም፥ ፍጹምና ዘላቂ የሆ መሥዋዕት ይሻ ነበር።  ጥያቄ፡- 1ኛ ዮሐ 2፡2 አንብቡ። ) ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ም ሆነ? ለ) 1ኛ ዮሐ 4፡10 አንብቡ። እግዚአብሔር ልጁ ስለ እኛ ኃጢአት ም እንዲሆን ላከው?  ጥያቄ፦ ዕብ 2፡17 አንብቡ። በምን ምክንያት ኢየሱስ ምሕረት የተሞላ ታማኝ ሊቀ ካህን ሆነ?  ጥያቄ፡- ሮሜ 3፡25-26 አንብቡ። ሀ) እግዚአብሔር ምን አድርጎ አቆመው ለ) ይህ ምንን ፈጸመ?  ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔርን በኃጢአት ሁሉ ላይ ለሁልጊዜ፡ የነበረውን የጽድቅ ቁጣ በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ያበረደ የእግዚአብሖ ፍጹም መሥዋዕት ነው። በ1ኛ ዮሐ. 2፡2 ውስጥ ኢየሱስ ክርስቶ የኃጢአታችን ማስተሰሪያ ነው ይላል። 1ኛ ዮሐ 4፡10 ውስጥ እግዚአብሖ ልጁን የላከው የኃጢአታችን ማስተሰሪያ እንዲሆን ነው ይላል። ቀደም ሲ እንደተመለከትነው ይህ «የስርየት መሥዋዕት» የሚለው አገላለ የሚያስገነዝበው፥ የመሥዋዕቶቹ ደም የእግዚአብሔርን የጽድቅ ቁ የሚመልሰውን የታቦቱን የምሕረት ማስቀመጫ ያመለክታል። እዚህ ላይ ዮሐንስ የሚነግረን አሁን ኢየሱስ የእግዚአብሔርን ቁጣ የሚመልስ ፍጹምና የመጨረሻው መሥዋዕት መሆኑን ነው። ዕብራውያን 2፡17 ደግሞ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ሊቀ ካህናቱ በዓመት አንድ ጊዜ የመሥዋዕቱን ደም ይዘው ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ መቅደስ እንደሚገቡ መለስ ብሎ ያስታውሳል። አሁን ኢየሱስ የእግዚአብሔር ፍጹም ምሕረት የተሞላና ታማኝ ሊቀ ካህን ነው።  የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔርን ቁጣ ለማስታገሥ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን በዓመት አንድ ጊዜ ይገሱ በነበረበት ሁኔታ፡ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን ቁጣ ለመጨረሻው ፍጹም በሆነ መንገድ ለማስታገሥ የራሱን ደሙን ለስርየት ይዞ ገባ።  ትናንትና በሮሜ 1፡18 የእግዚአብሔርን እውነት እያወቁ ችላ ባሉ፥ ለመታዘዝ በማይፈልጉ፥ በክፉዎችና በዐመፀኞች ላይ የእግዚአብሔር የጽድቅ ቁጣ እንደሚወርድ አስተውለናል። በሮሜ 1፡19፥ በመጀመሪያ ሐዋርያው ጳውሎስ ሰዎች ሁሉ ኃጢአተኞች ስለ መሆናቸው ለመግለጽ ሁለት ምዕራፎችን ጽፎአል። ሰዎች እንዲህ ኃጢአተኛች ከመሆናቸው የተነሣ፥ የእግዚአብሔር የጽድቅ ቁጣ ሊወርድባቸው ይገባል። ነገር ግን ሐዋርያው ወደ ሮሜ 3፡21 ሲደርስ፥ እግዚአብሔር እንዴት በኃጢአት ላይ የነበረውን የጽድቅ ቁጣ እንደ ታሠ ይገልጻል። ከዚህም በስተቀር እግዚአብሔር አስቆጥቶት ለነበረው የኃጢአታችን ችግር መፍትሔውን ሲሰጥ እናያለን። እንደዚሁም በሮሜ 3፡25-26 ውስጥ፥ እግዚአብሔር ራሱ ኢየሱስን የማስተሰሪያ መሥዋዕት አድርጎ እንዳቀረበውና፥ እኛም ይህንን በደሙ ባለን እምነት እንደምንቀበል ይገልጻል። ከዚያም

የኢየሱስ ሞት የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቁጣ ለማርካት (ለማብረድ) የቀረበ መሥዋዕት ነው።  Read More »

ኢየሱስ ለኃጢአት ፍጹም የሆነ መሥዋዕት ሆነ፦ የአዲስ ኪዳን መፈጸም

This entry is part 67 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

በትናንትናው ትምህርት ስለ እግዚአብሔር ቅድስናና ስለ ሰው ልጅ ኃጢአተኝነት ተምረን ነበር። እንደዚሁም በብሉይ ኪዳን ውስጥ፥ እግዚአብሔር ቅዱስ ሆኖ ሳለ፥ ሰዎች ግን ኃጢአተኞች በመሆናቸው ምክንያት ለሰው ልጅ ኃጢአት ምትክ የሆነ መሥዋዕት ማስፈለጉን አስተውለናል። የብሉይ ኪዳን መሥዋዕቶች ለጊዜው ብቻ የብሉይ ኪዳንን አማኛች ኃጢአት የሚሸፍኑ ነበሩ። ነገር ግን አንድ ቀን ፍጹምና ዘላቂ የሆነ የኃጢአት መሥዋዕት እንደሚመጣ ያስተምሩ ነበር። ያ ፍጹምና ዘላቂ የሆነ መሥዋዕት ኢየሱስ ክርስቶስ ነበር።  ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም የሆነ የጽድቅ ሕይወትን ኖረ።  ኢየሱስ ለእኛ ደኅንነትን የመስጠቱ ተግባር፥ በእርሱ ፍጹም የሕይወት ምሳሌነት ተጀመረ። ከኃጢአት ተለይቶ ሙሉና ፍጹም የሆነ የሰው ልጅን ሕይወት ስለ ኖረ በሞቱ ፍጹም መሥዋዕት በመሆን ለሚያምኑት ሁሉ ጽድቅን አጎናጸፈ።  ጥያቄ፡– ዕብራውያን 4፡15 አንብቡ። ኢየሱስ ኃጢአት ስለ መሥራቱም ሆነ ስላለመሥራቱ ይህ ጥቅስ ምን ይላል?  ጥያቄ፡- ዮሐንስ 8፡46 እንብብ። ኢየሱስ ላቀረበው ጥያቄ መልሱ ምንድን ነው?  ጥያቄ፡- ርሜ 5፡10 አንብቡ። ሀ) ሐዋርያው ጳውሎስ በኢየሱስ ሞት አማካይነት ከእግዚአብሔር ጋር ታረቅን ይላል። ታዲያ ስለ እኛ መዳን የሚናገረው እንዴት ነው? ለ) ሮማ 5፡19 አንብቡ። ሐዋርያው ጳውሎስ ብዙዎች ጻድቃን የሚሆኑት በምን ምክንያት ነው አለ?  ጥያቄ፡– 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡21 አንብቡ። ሀ) ኢየሱስ ስለ እኛ ምን ሆነ? ላ) ከዚህ የተነሣ እኛ ምን ሆንን?  ጥያቄ፡– 1ኛ ጴጥሮስ 1፡8-19 አንብቡ። ሐዋርያው ጴጥሮስ ኢየሱስ ምን ዓይነት በግ ነው አለ?  ለኃጢአት ፍጹምነት ያለው መሥዋዕት ለመሆን፥ ፍጹምነት ያለው ጽድቅንም እንዲሰጠን ክርስቶስ ራሱ ፍጹምና ጻድቅ የሆነ ሰብአዊ ሕይወትን መኖር ነበረበት። በሁለተኛው ክፍለ ትምህርት ውስጥ እንደ ተመለከትነው፥ አዲስ ኪዳን ኢየሱስ በሕይወት ዘመኑ ፈጽሞ ኃጢአት አለመሥራቱን ያስተምራል። ዕብራውያን 4፡5 ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ ሌሎች ሰዎች በተፈተኑበት ፈተና ተፈትኖአል ይላል። እርሱ ሁልጊዜ ለእግዚአብሔር ይታዘዝ ነበር። በዮሐንስ 8፡46 ውስጥ ኢየሱስ ሕዝቡን አንዳቸው እንኳ ኃጢአት ሠርተሃል ብለው ሊከሱት ይችሉ እንደሆነ ይጠይቃቸዋል። አንዳቸውም ደፍረው ሊከሱት አልቻሉም። ምክንያቱም በምንም ዓይነት ኃጢአት አልበደለም ነበር።  ምንም እንኳን የኢየሱስ የማዳን ሥራ የሚያተኩረው ሰሞቱ ላይ ቢሆንም፥ ከጻድቅ ሕይወቱ የተነሣ ደኅንነት ሊመጣልን ችሏል። የኢየሱስ የጻድቅ ሕይወት የደኅንነታችን አካል የሆነው በሁለት መንገድ ነው። አንደኛው፥ ኢየሱስ ፍጹም ጻድቅ በመሆኑ፥ የእርሱን ጽድቅ ለእኛ በመስጠት እኛን ጻድቃን አድርጎናል። በሮሜ 5፡10 ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ የኢየሱስ ሞትና ሕይወት ሁለቱም ለእኛ ጥቅም እንዳላቸው ይገልጻል። በዚሁ በሮሜ 5፡10 ውስጥ በአንድ ሰው በኢየሱስ) መታዘዝ ጻድቃን እንሆናለን ይላል። በ2ኛ ቆሮንቶስ 5፡21 ደግሞ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ኃጢአታችንን በመሸከሙ እኛ ጽድቁን እንዳገኘን ይናገራል። ኢየሱስ እኛን ጻድቃን ለማድረግ፥ ፍጹም የሆነ የጽድቅ ሕይወት በሰብአዊነቱ መኖር ነበረበት። የእርሱን ጽድቅ በእኛ ኃጢአት በመለወጥ እኛን ፍጹም ጻድቃን አደረገን። የእርሱን ፍጹም ጽድቅ በመቀበላችን፥ ከእግዚአብሔር ጋር ልንታረቅ ቻልን። ሌላም ሁለተኛ ምክንያት አለ። ይህም እኛ እንድንድን ኢየሱስ ጻድቅ ሆኖ መኖር ነበረበት። በሁለተኛውና በአሥረኛው ትምህርት ውስጥ እንደ ተመለከትነው ኢየሱስ ለኃጢአታችን ፍጹምነት ያለው መሥዋዕት ለመሆን እንዲችል፥ ፍጹም የሆነ የጽድቅ ሕይወትን መኖር ነበረበት። የፋሲካ በጎችና የመሥዋዕት እንስሳት ለኃጢአት መሠዋት እንዲችሉ ፍጹም መሆን ነበረባቸው፡፡ እንደዚሁም ለዓለም ኃጢአት የሚቀርበው መሥዋዕት ፍጹም ጽድቅን የተጎናጸፈ መሆን ነበረበት። በ1ኛ ጴጥሮስ 1፡18-19 ኢየሱስ ነውርና እድፍ የሌለበት የመሥዋዕት በግ እርሱ ነው ይላል። የኢየሱስ ፍጹም የጽድቅ ሕይወት ማለት፥ እርሱ ፍጹምነት ያለው ለኃጢአት መሥዋዕት ለመሆን የሚችልና «እኛ በእርሱ የእግዚአብሔር ጽድቅ» እንድንሆን፥ የራሱን ጽድቅ ስለ ኃጢአታችን መለወጥ የቻለ ነው።  ኢየሱስ በመሥዋዕትነቱ ሞት ኃጢአታችንን ተሸከመ፡፡  የኢየሱስ ፍጹም የሆነ ሕይወት፥ የደኅንነታችን የመጀመሪያ ነጥብ ነው። አዲስ ኪዳን ደኅንነታችን በኢየሱስ ሞት አማካይነት ስለ መገኘቱ የበለጠ አጽንዖት ሰጥቶታል። ኢየሱስ ኃጢአታችንን የተሸከመ የመሥዋዕትነት ሞትን ሞተ።  ጥያቄ፡- ዮሐንስ 1፡29 አንብቡ። ዮሐንስ መጥምቁ ኢየሱስን ማን አለው? ምንስ ያደርጋል አለ?  ጥያቄ፡– ኤፌሶን 5፡2 አንብቡ። ኢየሱስ ለእኛ ምን አደረገልን?  ጥያቄ፡- ገላትያ 1፡3-4 አንብቡ። ክርስቶስ ለእኛ ምን አደረገልን?  ጥያቄ፡- 1ኛ ጴጥሮስ 2፡24 አንብቡ። ክርስቶስ በመስቀል ላይ በሞተ ጊዜ በሥጋው ምንን ተሸከመው?  በዮሐንስ 1፡29 ውስጥ እንደተጻፈው፥ ዮሐንስ መጥምቁ ኢየሱስን ከአይሁድ ሕዝብ ጋር አስተዋወቀው። ዮሐንስ፥ ኢየሱስ በዮርዳኖስ ወንዝ አድርጎ ወደ እርሱ ዘንድ በመጣበት ጊዜ፥ ወደ እርሱ እያመለከተ «እነሆ፥ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ» ሲል ጮኸ።  ዮሐንስ ይህን ቃል ባዕተጋባበት ጊዜ አድማጮቹ ብዙ ነገር ማሰባቸው አልቀረም። በመጀመሪያ፥ ምናልባት ትዝ ያላቸው ባእስራኤል በኩር ወንድ ልጆች ፈንታ ስለ ተሠዉት በጎች ሳይሆን አይቀርም። ሁለተኛ ደግሞ፥ በየቀኑ በቤተ መቅደስ ውስጥ ለኃጢአት ይቅርታ ተብለው ስለሚሠዉ በጎች ሳያስቡ አልቀሩም። ሦስተኛ፥ በኢሳይያስ 53 «ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ ‘ አፉንም አልከፈተም፥ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ» የሚለው ትዝ ብሎአቸው ሊሆን ይችላል። ዮሐንስ ኢየሱስ ልክ እንደ እነዚህ በጎች ይሆናል ሲል ነበር የነገራቸው። እርሱም የዓለምን ኃጢአት የሚሸከም ፍጹምና የመጨረሻ መሥዋዕት ነው። እርሱ የዓለምን ኃጢአት ሊሸከም ስለ መጣ ዓለም የራሱን ኃጢአት መሸከም አያስፈልገውም።  ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ የተናገራቸው ነገሮች በመልእክታት ውስጥ ተደጋግመው ቀርበዋል። በኤፌሶን 5፡2 ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ፥ «ኢየሱስ ራሱን መሳና መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ሰጠ» ይላል። በገላትያ 1፡3-4 ደግሞ፥ ክፉ ከሆነ ከአሁኑ ዓለም ያድነን ዘንድ ስለ ኃጢአታችን ራሱን ሰጠ ይላል። በ1ኛ ጴጥሮስ 2፡24 ውስጥ «እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ» ይላል። የዚህ ውጤት ከአሁን ጀምሮ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሕይወት መኖር እንችላለን ማለት ነው። እርሱ ኃጢአታችንን በራሱ ላይ ስለ ተሸከመ ሕይወታችን ተለውጦአል። ቀድሞ ግን በኃጢአታችን ምክንያት የሞትና የኃጢአት ባሪያዎች ነበርን። አሁን ግን፥ ለኃጢአት ስለ ሞትን የጽድቅን ሕይወት ለመኖር እንችላለን። ካሁን ወዲያ ኃጢአትን እምቢ ጽድቅን እሺ ማለት እንችላለን። በመንፈስ ሞተን የነበርነውንና የዘላለም ሞት የተፈረደብንን በመንፈስ ሕያዋን እንድንሆን፥ እንዲሁም ለጽድቅ ለመኖር እንድንችልና የዘላለም ሕይወት ተስፋ ተሳታፊዎች እንድንሆን የኢየሱስ ሞት ለውጦናል።  ኢየሱስ በመሥዋዕትነት ሞቱ አማካይነት የተሸከመው ኃጢአታችንን ብቻ አልነበረም። ነገር ግን በመሥዋዕትነት ሞቱ አማካይነት የእኛ ቤዛ (ምትክ) ሆኖ ይገባን የነበረውን በደልና ቅጣት ተቀበለ።  ኢየሱስ በእኛ ምትክ በደላችንንና ቅጣታችንን ወሰደ።  ጥያቄ፡- ገላትያ 3፡13 አንብቡ። ክርስቶስ በመስቀል ላይ በሞተ ጊዜ፥ ለእኛ ምን አደረገልን?  ጥያቄ፡- ሮሜ 1፡18 አንብቡ። ሀ) በሰዎች ክፋትና ዐመፀኝነት ምክንያት ምን ይገለጣል? ለ) ሮሜ 5፡9 አንብቡ። እኛ የዳንነው ከምንድን ነው?  ጥያቄ፡- ማርቆስ 10፡45 አንብቡ። የሰው ልጅ ምን አደረገ?  ጥያቄ፡ ዮሐንስ 10፡11 አንብቡ። መልካም እረኛ ለበጎቹ ምን ያደርጋል?  ጥያቄ፡- 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡14 አንብቡ። አንዱ ለሁሉ ስለ ሞተ፥ ምን ተደረገ?  አዲስ ኪዳን ኢየሱስ በመስቀል ላይ በሞተ ጊዜ በእኛ ፈንታ መሞቱን በጥብቅ ያስተምራል። ለእኛ ይገባን የነበረውን በደልና የኃጢአት ቅጣት እርሱ ተቀበለ። ዛሬ ቀደም ብለን እንደ ተመለከትነው 1ኛ ቆሮንቶስ 5፡21 እግዚአብሔር የኢየሱስን ጽድቅ በኃጢአታችን እንደ ለወጠው ያስተምራል። ኃጢአታችንን የወሰደ ቢሆንም፥ እንደ እውነቱ ከሆነ በእኛ ፈንታ ኃጢአት ሆነ። ስለዚህ እኛ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን እንድንሆን የእርሱን ጽድቅ ወሰድን። ኢየሱስ ስለ እኛ ኃጢአት ለመሆን በእኛ እግር ተተካ (ምትካችን ሆነ)። ገላትያ 3፡13 እንደሚያስተምረን እርሱ በተሰቀለ ጊዜ፥ ለእኛ ይገባን የነበረውን እርግማን ተቀበለ። ከኃጢአታችንም የተነሣ ለዘላለሙ ከእግዚአብሔር እንድንለይ ተረግመን ነበር። ኢየሱስ በእኛ ፈንታ መርገምን በላዩ ላይ ተሸከመ። ሮሜ 1፡18 ደግሞ ከሰዎች ክፋትና ዐመፃ የተነሣ የእግዚአብሔር ቁጣ በሰዎች ሁሉ ላይ ይወርዳል ይላል። ይህንኑ ነጥብ ሐዋርያው ጳውሎስ በሮሜ 1፡18-3፡20 በዝርዝር ይገልጻል፤ በሮሜ 3፡21 5፡8 ውስጥ ደግሞ ስለ ክርስቶስ ሞትና በእርሱ በሚኖረን እምነት አማካይነት እንዴት ደኅንነቱን እንደምንቀበል ያብራራል። በሮሜ 5፡9 ውስጥ ሊያጠቃልል ይህን ደኅንነት በምንቀበልበት ጊዜ ከእግዚአብሔር ቁጣ እንደምንድን ይነግረናል። በዚህም ጳውሎስ እኛ ቁጣውን እንዳንሸከም ኢየሱስ በእኛ ፈንታ የእግዚአብሔርን ቁጣ እንደ ተሸከመ ያስገነዝባል።  ኢየሱስ በእኛ ፈንታ ተተክቶ በደላችንና የኃጢአታችንን ቅጣት መቀበሉን ግልጽ

ኢየሱስ ለኃጢአት ፍጹም የሆነ መሥዋዕት ሆነ፦ የአዲስ ኪዳን መፈጸም Read More »

የእግዚአብሔር ቅዱስነት የኃጢአትን መሥዋዕት ይሻል፡- የብሉይ ኪዳን ምሳሌ 

This entry is part 66 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

የኃጢአት ይቅርታ ለማስገኘት አንድ ሰው እንዲሞት ለምን አስፈለገ? ብዙ ሙስሊሞች፥ ያላንዳች መሥዋዕት አቅርቦት እግዚአብሔር ኃጢአትን ይቅር ይላል ብለው ያምናሉ። እግዚአብሔር ሉዓላዊ ሥልጣን ያለውና የዓለም ገዥ በመሆኑ ኃጢአታችሁ ይቅር ተብሏል ብሎ በቀላሉ ለመናገር ኃይልም ሥልጣንም አለው ይላሉ። ስለዚህ ስለ ኃጢአት ቅጣት ሊከፈል አያስፈልግም፥ ምክንያቱም እግዚአብሔር ኃጢአት ይቅርታ እንዲያገኝ በቀላሉ ሊያዝ ይችላል ብለው ያምናሉ። ሌሎች ሰዎች ደግሞ ስለሌላው ኃጢአት ሌላው ሰው መሞት አለበት ብሎ መናገር ስሕተት ነው ባይ ናቸው። አንዱ ሰው ሌላውን ቢበድለው፥ ለዚያ ኃጢአት ካሣ ለመክፈል ሌላው መሞት አይገባውም ይላሉ። ስለዚህ የተበደለው ሰው ለበዳዩ ሰው በቀላሉ ይቅርታ ሊያደርግለት ይችላል ይላሉ። ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ብሉ በመስቀል ላይ ስለ መሞቱ የምናምነው በምን ምክንያት ነው?  ጥያቄ፡- ዘሌዋውያን 11፡45፤ 20፡26 አንብቡ። ሀ) በእነዚህ ጥቅሶች አማካይነት፥ እግዚአብሔር ራሱን በምን አኳኋን ይገልጻል? ለ) እግዚአብሔር በዚህ አኳኋን ሲገልጽ የእግዚአብሔር ሰዎችስ ምን ሊያደርጉ ይገባቸዋል?  ጥያቄ፡- ኢሳይያስ 6፡1፥ 5-7 አንብቡ። ሀ) በኢሳይያስ ራእይ ውስጥ እግዚአብሔር በምን ሁኔታ ተገለጸ? ለ) ኢሳይያስ ስለታየው የእዚአብሐር ራእይ ስሜቱና አስተያየቱ እንዴት ነበር? ሐ) መልአኩ ለኢሳይያስ ምን አደረገ? መ) የመልአኩ ተግባር ውጤት ምን ነበር?  ጥያቄ፡– ዘፀአት 3፡5 አንብቡ። ሙሴ አድርግና አታድርግ ተብሉ የታዘዘው ምን ነበር?  ጥያቄ፡- ዘሌዋውያን 10፡1-3 አንብቡ። ሀ) ናጻብና አብዩድ በምን ምክንያት ሞቱ? ለ) ዘሌዋውያን 16፡2 አንብቡ። የአሮን ሁለቱ ወንዶች ልጆቹ ተራና ያልተቀደሰ እሳት ይዘው በእግዚአብሔር ፊት በመቅረባቸው ተቀስፈው ከሞቱ በኋላ፥ እግዚአብሔር አሮንን ምን አዘዘው?  ጥያቄ፡- 1ኛ ዮሐንስ 1፡5ና ዕብራውያን 12፡17 አንብቡ። በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ እግዚአብሔር በምን መልክ ተገልግል?  ጥያቄ፡- ዘሌዋውያን 18፡25 አንብቡ። ሀ) እግዚአብሔር ከነዓናውያንን በምን ምክንያት ከምድራቸው አስወጥቶ አባረራቸው? እግዚአብሔር ከነዓናውያንን ከምድሩ አስወጥቶ እንዴት እንዳባረራቸው ጥቅሱ በምን አኳኋን ይገልጸዋል? ለ) ዘሌዋውያን 20፡22-23 አንብቡ። እስራኤላውያን የከነዓናውያንን ተግባር ቢከተሉ ኖሮ ምን ይደርስባቸው ነበር?  ክርስቶስ ለእኛ ኃጢአት ሲል በምን ምክንያት እንደ ሞተ ለመገንዘብ፥ በመጀመሪያ የእግዚአብሔርን ቅድስናና የሰውን ልጅ ኃጢአተኝነት ማወቅ ያሻል፡ እግዚአብሔር «ቅዱስ» ነው በምንልበት ጊዜ፥ እርሱ ከማንኛውም ተራ ከሆነ ነገር ሁሉ፥ በተለይም ከኃጢአት ፈጽሞ የተለየ ነው ማለታችን ነው። ዘሌዋውያን 1፡45ና 20፡26 እንደሚያስታውሰን እግዚአብሔር ቅዱስና ከኃጢአት የነፃ ፍጹም እንደሆነ ሁሉ፣ ሕዝቡም ቅዱስና ከኃጢአትም ንጹሐን እንዲሆኑ መፈለጉን ይናገራል። የእግዚአብሔር ሕዝብ ራሳቸው ቅዱስና ከኃጢአትም የተለዩ ካልሆኑ በስተቀር በእርሱ ጸንተው ሊቆዩ አይችሉም።  እግዚአብሔር ቅዱስ ስለ መሆኑ፥ ከኃጢአት ምን ያህል የራቀ እንደሆነና ኃጢአት በእርሱ ዘንድ የረከሰ ላለ መሆኑ፥ መጽሐፍ ቅዱስ እፍታቶ ለእኛ ለመግለጽ በተለያዩ ምስሎች ይጠቀማል። በመጀመሪያ፣ መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ከፍጥረታቱ ሁሉ በላይ ከፍ ብሎ እንደሚገኝ ይናገራል። ኢሳይያስ ስለ እግዚአብሔር ዙፋን ሊገልጽ፥ ከፍ ከፍ ያለና ከሁሉም በላይ የከበረ የላቀ መሆኑን ያስረዳል። እግዚአብሔር ምን ያህል ከፍ ያለና ቅዱስ እንደሆነ በተመለከተ ጊዜ በመጀመሪያ ያረጋገጠው እርሱ ምን ያህል ኃጢአተኛ እንደ ነበረ ነው። ከዚያም ኢሳይያስ በእግዚአብሔር ፊት ጸንተ ሊቆም ይችል ዘንድ መልአኩ ከኃጢአቱ ሊያነጻው ብሎ በምድጃ ው ላይ ከነበረው ፍም በጉጠት ወስዶ ከንፈሩን ዳሰሰው። ከንፈሮቹ በእሳት መዳሰሳቸው ብቻ ኢሳይያስን ከኃጢአቱ ሊያጠራው አይችልም ነበር። ስለዚህ በእሳት የተዳሰሰው የኢሳይያስ ከንፈር ኃጢአት በእግዚአብሔር ፊት ሊኖር እንደማይችልና ኃጢአተኞች ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ከመቅረባቸው አስቀድሞ ከኃጢአታቸው መንጻት እንዳለባቸው የሚያስገነዝብ ሥዕላዊ መግለጫ ነው። እንዲሁም ሙሴ ይቃጠል የነበረውን ቁጥቋጦ በቀረበ ጊዜ እግዚአብሔር ወደ ቁጥቋጦው እንዳይቀርብ፥ ጫማውንም እንዲያወልቅ አዘዘው። ይህ እንግዲህ እንደ ሙሴ ያለ ተራና ኃጢአተኛ ሰው፥ ቅዱስ ወደሆነው እግዚአብሔር ፊት ሊቀርብ እንደማይችል ማስጠንቀቂያ ነበር። በብሉይ ኪዳን ውስጥ ወደ ነበረው የኪዳኑ ድንኳን፥ ተራው ሕዝብ ሊቀርብ አይችልም ነበር። በኪዳኑ ድንኳን ውስጥ ያገለግሉ የነበሩት ካህናቱ ብቻ ነበሩ። ስለሆነም ናዳብና አብዩድ ያልተቀደሰ ተራ ፍም ይዘው በእግዚአብሔር ፊት በቀረቡ ጊዜ እግዚአብሔር ስለ ቀሰፋቸው ሞቱ። ከዚያም እግዚአብሔር ለአሮን፥ እርሱ በማይፈቅድበት ጊዜ፥ ማንም ሰው ሊቀ ካህናትም ቢሆኑ ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ ሊቀርቡ እንደማይችሉ አዝዞታል። የእግዚአብሔር ቅድስና ማለት እርሱ ከፍጥረቱ ሁሉ በላይ ነው ማለት ነው። በተለይም የእግዚአብሔር ቅድስና ማለት እርሱ ኃጢአተኛ ከሆነው ከሕዝቡ ሁሉ የተለየ ነው ማለት ነው።  ሁለተኛ፥ መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን እንደ እሳትና ብርሃን አድርጎ ይገልጸዋል። በ1ኛ ዮሐንስ 1፡5 ውስጥ እግዚአብሔር የኃጢአትን ጨለማ የሚገልጥ ብርሃን ነው ይላል። በዕብራውያን መልእክት 12፡18 እግዚአብሔር የኃጢአትን ርኩሰት ሁሉ የሚያቃጥል እሳት ነው ይላል። እግዚአብሔር ንጹሕና እጅግ በጣም የደመቀ ብርሃን ስለሆነ፥ እርሱ እጅግ ሞቃትና የሚንበለበል እሳት በመሆኑ እግዚአብሔርና ኃጢአት አብረው ሊኖሩ አይችሉም።  ምናልባት እግዚአብሔር ከኃጢአት ነፃ የሆነና የተቀደሰ ስለ መሆኑ ግልጽ በሆነ ምሳሌ የተናገረው «ትፋት» በሚለው ቃል መግለጫነት ነው። በዘሌዋውያን 18፡5 ውስጥ እግዚአብሔር ሲናገር፥ የከነዓንን ሰዎች ከኃጢአታቸው የተነሣ ምድሪቱ ልትተፋቸው ነው ይላል፡፡ በዘሌዋውያን 20፡22-23 ደግሞ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፥ እስራኤላውያንም በክፋታቸው ቢቀጥሉ →ምድሪቱ እንዲሁ ታደርጋቸዋለች፥ ከምድራቸውም ትተፋቸዋለች። ትፋት ወይም ትውከት የሚከሰተው አንድ ሰው ጨጓራው የማይፈጨውንና ሰውነቱን የሚመርዝ ምግብ ሲመገብ ነው። እንደዚሁም ኃጢአት መርዝ ስለሆነ፥ እግዚአብሔርን በምንም መልኩ «ሊዋሃደው» አይችልም። ስለዚህ ኃጢአት የሚሠሩትንም ሰዎች እግዚአብሔር ይተፋቸዋል።  እግዚአብሔር በፍጹም ከኃጢአት የተለየ ቅዱስ ነው። እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ፥ ልጆቹም እንደዚሁ ቅዱሳን ሊሆኑ ይገባል። ወንዶችም ሴቶችም ቅዱሳን ካልሆኑ የእግዚአብሔር ልጆች መሆን አይችሉም። ነገር ግን ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ እንደ ተከታተልነው በምድር ላይ ያሉ ሰዎች ሁሉ ኃጢአተኞች ናቸው። ሁላችንም ኃጢአተኛች ከመሆናችን የተነሣ፥ ራሳችንን የእግዚአብሔር ጠላቶች (ሮሜ 8፡9፤ ቆላስይስ 1፡21፤ ያዕቆብ 4፡4)። የሰይጣን አገልጋዮች (ኤፌሶን 2፡2)፥ የኃጢአት ባሪያዎች (ዮሐንስ 8፡34)። የእግዚአብሔር የጽድቅ ቁጣ የሚፈጽምባቸው አድርገናል (ኤርምያስ 4፡4፤ ሮሜ 1፡18)።  እግዚአብሔር ሉዓላዊ የሆነ የፍጥረታት ገዥ እስከሆነ ድረስ ኃጢአታችንን በቀላሉ ይቅር ሊለን የማይችለው ለምንድን ነው? እግዚአብሔር እጅግ ፍጹምና ጻድቅ ስለሆነና እኛም ራሳችንን ኃጢአተኛ ጠላቶቹ ከማድረጋችን የተነሣ እግዚአብሔር እንዲህ በቀላሉ ኃጢአታችንን ይቅር አይለንም። ይቅርታ ከማግኘታችን በፊት ኃጢአታችን መቀጣት አለበት። እንዲሁም ይቅርታ ከመቀበላችን እስቀድሞ የበደላችንና የኃጢአታችን ቅጣት ሊከፈል ይገባል። ይቅርታ ከማግኘታችን በፊት የእግዚአብሔር የጽድቅ ቁጣ ሊፈጸም ይሻል። ይቅርታ ከመቀበላችን አስቀድመን የእግዚአብሔር ወዳጆች ልንሆን ይገባል። ይቅር ከመባላችን በፊት ከኃጢአት ባርነትና ከሰይጣን አገልግሎት ልንድን ይገባል። እግዚአብሔር ቅዱስና ንጹሕ በአንጻሩ እኛ ደግሞ ኃጢአተኞች በመሆናችን፥ የእኛ ኃጢአት ሊቀጣ ያስፈልጋል።  ጥያቄ፡- ዘሌዋውያን 16፡1-34 አንብቡ። በምታነቡበት ጊዜም መሥዋዕቱና የአቅርቦቱ ሥነ ሥርዓት ለኃጢአታችን «ስርየትን» እንደሚሰጥ እግዚአብሖር ስንት ጊዜ እንደ ተናገረ ቁጠሩ።  ጥያቄ፡- ዘሌዋውያን 4፡27-35 አንብቡ። ሀ) በብሉይ ኪዳን ጊዜ የነበሩ እስራኤላውያን ኃጢአት በሚሠሩበት ጊዜ ምን ማድረግ ነበረባቸው? ይህን በራሳችሁ ቃል በአጭር መግለጫ ጻፉ። ለ) ውጠቶቹ ምን ይሆናሉ (ቁጥር 31ና 5)?  ጥያቄ፡- ዕብራውያን 10፡3-4 አንብቡ። ሀ) እነዚህ የብሉይ ኪዳን መሥዋዕቶች በእውነት የብሉይ ኪዳን እስራኤላውያንን ኃጢአት ያስወግዱ ነበር? ለ) ዕብራውያን 9፡13 አንብቡ። ሰዎች በእምነት ያቀርቡዋቸው የነበሩ የብሉይ ኪዳን መሥዋዕቶች ምን ይጠቅሟቸው ነበር? ሐ) ሮሜ 3፡25 እንብቡ። እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ጊዜ ስለተፈጸሙ ኃጢአቶች ምን አደረገ?  ጥያቄ፡- ኢሳይያስ 53፡4-6 አንብቡ። ከዚያም የሚሠቃየው ባሪያ፥ በእውነት በመጨረሻው የኃጢአትን ቅጣት እንደሚሸክም የሚያመለክቱ ሐረጉችን ጻፉ።  በብሉይ ኪዳን ዘመን እግዚአብሔር ለሕዝቡ ለኃጢአት የሚቀርቡ መሥዋዕቶችን በተመለከተ መመሪያ ሰጥቶ ነበር። መመሪያው በስርየት ቀን ይጀመር ነበር። ይህ ሥርዓት በዓመት አንድ ጊዜ ይፈጸም ነበር። ይህ የስርየት ቀን መላው ሕዝብ የኃጢአት መንጻት ስርየት የሚያገኝበት ነበር። በዘሌዋውያን 16 ውስጥ እግዚአብሔር አሥራ ስድስት ጊዜ በዚያን ቀን የሚቀርቡለት መሥዋዕቶች የኃጢአት ስርየትን እንደሚያስገኙ ይናገራል። በዚህ ለመላው ሕዝብ ስርየት የሚቀርበውን መሥዋዕት መሠረት በማድረግ እያንዳንዱ እስራኤላዊ በበኩሉ የኃጢአት ይቅርታ የሚያገኝበትን መሥዋዕት ያቀርብ ነበር። በዘሌዋውያን 4 የተነገረው የኃጢአት ይቅርታ መሥዋዕት አንዱ ምሳሌ ነው። ሊቀ ካህኑ መሥዋዕት ላመጡት ግለሰቦች ስርየት የሚያሰጥ አንድ በሬ በመሠዊያው ላይ

የእግዚአብሔር ቅዱስነት የኃጢአትን መሥዋዕት ይሻል፡- የብሉይ ኪዳን ምሳሌ  Read More »