አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ሰዎች የክርስቶስን መልእክት ሳይሰሙ ሊድኑ ይችላሉ? 

This entry is part 95 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

እንግዲህ ዛሬ ስለ ደኅንነት ከሚነሡ ከባድ ከሆኑ ጥያቄዎች አንዱን ለመመለስ እንሞክራለን። ስለ ክርስቶስ ስፍጹም ሰምተው የማያውቁ አንዳንድ ሰዎች በእግዚአብሔር በማመናቸው ይድናሉ?  ከአንድ መቶ ዓመት በፊት አካባቢ፥ በደቡብ ኢትዮጵያ ኢሳ የተባለ ነቢይ ተነሥቶ ነበር። ይህ ነቢይ በሕይወቱ ዘመን በአብዛኛው በኢትዮጵያ ደቡባዊው ክፍል እየተዘዋወረ፥ ሰዎች ለርኩስ መናፍስት መስገዳቸውን ትተው አንዱን በሰማይ የሚኖር እውነተኛ አምላክ እንዲያመልኩ ያስተምራቸውና ያሳስባቸው ነበር። እስከምናውቀው ድረስ፣ ኢሳ የክርስቲያኖችን ወንጌል ጨርሶ አልሰማም ነበር። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውም አምላክም ሆኖ ወደዚህ ዓለም በመምጣት የንጽሕና ሕይወትን በመኖር የመሥዋዕትነትን ሞት እንደ ሞተ በፍጹም አልሰማም። እንዲሁም ከኃጢአቱ ለመዳን ሲል በክርስቶስ የማመን ዕድልም አላገኘም። ሆኖም ግን ኢሳ የሰማይ አምላክ የሆነውን አንዱን እግዚአብሔርን የማምለክ ዝንባሌ ይታይበት ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ ኢሳን ስለ መሰሉ ሰዎች የሚናገረው ነገር አለው? እግዚአብሔር እንደ ኢሳ ያለ፥ በእርሱ የሚያምን፥ ግን የክርስቶስን መልእክት ለመስማት ዕድል ያላገኘን ሰው ያድን ይሆን? እግዚአብሔር በክርስቶስ ሞት የተገኘው ትሩፋት፥ እንደ ኢሳ ያሉ ስለ ክርስቶስ ጨርሰው ያልሰሙ ወይም በእርሱ ያላመኑ ሰዎች እንዲድኑበት ያደርግ ይሆን?  1. የአዲስ ኪዳን አጠቃላይ ዓላማ ሰዎች የክርስቶስን መልእክት ሰምተው፥ ደኅንነቱን ስለ መቀበላቸው በእምነታቸው አማካይነት እንዲያስታውቁ ነው።  ጥያቄ፡- ዮሐ 14፡6 አንብብ። ወደ አብ የሚያደርሰው ብቸኛው መንገድ ማን ነው?  ጥያቄ፡- የሐዋ. ሥራ 4፡12 አንብብ። ሰዎች በማን ስም ብቻ ይድናሉ?  ጥያቄ፡- ሮሜ 1፡18-23 አንብብ። ሀ) ሰዎች ሁሉ ለለ እግዚአብሔር ምን ያውቃሉ? (ቁጥር 20) ለ) ሰዎች ስለ እግዚአብሔር ባላቸው በዚህ እውቀት ምን ያደርጋሉ? (ቁጥር 18፣ 21-23)  ጥያቄ፡- ሮሜ 10፡13-14 እንብብ። ሀ) የሚድነው ማን ነው? (ቁጥር 13) ለ) ሰዎች የጌታን ስም መጥራት እንዲችሉ ምን ያስፈልጋቸዋል? (ቁጥር 14)  አዲስ ኪዳን በግልጽ እንደሚናገረው፥ የደኅንነት አጠቃላይ ዓላማ፥ የክርስቶስን መልእክት ማድመጥና የሰሙትንም በእምነት መግለጥ ነው። በዮሐንስ 14፡6 ውስጥ ኢየሱስ ራሱ፥ ማንም ቢሆን በእርሱ በኩል ካልሆነ ወደ አብ ሊመጣ እንደማይችል ተናግሮአል። ብዙ ምንባቦችን ከጻፈ በኋላ ሰዎች መዳን ከፈለጉ እምነታቸውን በኢየሱስ ላይ ማድረግ እንዳለባቸው ዮሐንስ ጽፎአል (ምሳሌዎቹ፡- ዮሐንስ 1፡12፤ 3፡15፤ 16፣ 36)። በግልጽ እንደሚታየው፥ ኢየሱስ የተናገረው፥ ወደ አብ ለመድረስ የሚቻለው በእርሱ በማመን ብቻ መሆኑን ነው። ቀደም ባሉት የሐዋርያት ሥራ ምዕራፎች እንደተጻፈው፥ ሐዋርያት በኢየሱስ አማካይነት ስለሚገኘው ደኅንነት ስለ ሰበኩ፥ የአይሁድ መሪዎች ተቆጥተው ነበር። ልክ እንደ ሐዋርያት፥ እነዚህ የአይሁድ መሪዎችም በእስራኤል አንድ አምላከ ያምኑ ነበር። እንዲሁም መዳን የሚገኘው በእርሱ መሆኑን ያወቁ ነበር። ነገር ግን በሐዋርያት ሥራ 4፡10-12 ውስጥ፥ ጴጥሮስ አንዱንና የደኅንነት መንገድ እርሱ ብቻ የሆነውን ክርስቶስን አለመቀበላቸውን ነገራቸው። ስለሆነም እነዚህ የሃይማኖት መሪዎች ደኅንነትን ለማግኘት በሰማይ የሚኖር አንዱን እውነተኛ አምላክ ማመናቸው ብቻ አይበቃም ነበር። ደኅንነትን ለማግኘት እንዲችሉ በኢየሱስ ማመን ነበረባቸው።  ሐዋርያው ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱም እንደሚያስተምረው፥ በሰማይ ስለሚኖረው አምላክ ማወቅ ብቻ አይበቃም ይላል። ቀጥተኛው የደኅንነት መንገድ ስለ ክርስቶስ የሚታወጀውን ቃል መስማትና የሰሙትን በእምነት መግለጥ ነው። በሮሜ ምዕራፍ 1 ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ እንደሚለው፥ ሰዎች ሁሉ ስለ ሰማዩ አምላክ የተወሰነ እውቀት አላቸው። ነገር ግን ይህ እውቀት ሊያድናቸው የሚበቃ አይደለም። በሰማይ ስለሚኖረው አምላክ የሚያውቁት «ዘላለማዊ ኃይሉንና አምላክነቱን» ነው (ሮሜ 1፡20) ይላል። ታዲያ ሰዎች በዚህ እውቀት እንዴት ይጠቀሙበታል? «እውነቱን ሸፈኑበት» እግዚአብሔርን በማክበር ፈንታ፥ ፍጥረታትን አመለኩ (ሮሜ 1፡18፥21-23)። በፍጥረታት አማካይነት ስለ እግዚአብሔር ማወቅ ደኅንነትን ለማስገኘት በቂ አይደለም። ብዙ ጊዜ ሰዎች ይህን እግዚአብሔርን የማወቅ ሁኔታ ትተው ፊታቸውን ያዞሩና እግዚአብሔር የፈጠራቸውን ነገሮች ያመልካሉ (ሮሜ 1፡25)፡፡ ጳውሎስ በሮሜ 10፡13-14 እንደሚናገረው፥ ሰዎች መዳን ከፈለጉ የጌታን ስም መጥራት አለባቸው፡፡ ጳውሎስ፥ «የጌታ ስም» በሚልበት ጊዜ፥ በትክክል ስለ ጌታ ኢየሱስ ማሰቡ ነው። (በሮሜ 10፡9 ውስጥ የተጻፈውን ዐውደ ንባብ ተመልከት።) ሰዎች፥ የጌታን ስም ለመጥራት ስለ ክርስቶስ የተነገረውን መልእክት ሰምተው በእምነት ሊገልጡት ይገባል (ሮሜ 10፡14)። የደኅንነት ዓላማ ሰዎች ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወትና ሞት የተነገረውን ሰምተው ለደኅንነታቸው በእርሱ ማመን ነው።  2. ሰዎች ሁሉ ስለ ክርስቶስ ሳይሰሙ እንዲድኑ እግዚአብሔር በቂ ፍንጭ ሰጥቶአል?  ቢያንስ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ሁለት ጥቅሶች ስለ ክርስቶስ ጨርሶ ያልሰሙና በእርሱ አምነው ደኅንነትን ስላላገኙ ሰዎች እግዚአብሔር የሚለው ፍንጭ እንዳለ ይጠቁማሉ። እነዚህ ጥቅሶች ለእኛ ምን ይሉናል?  ጥያቄ፡- ዮሐ 1፡9 አንብብ። ሀ) ጌታ ኢየሱስ ወደ ዓለም በመጣ ጊዜ ለእነማን ብርሃንን ሰጠ? ለ) ዮሐንስ 1:5፥10 አንብብ። ኢየሱስ ግን እንደ ነበረ ሁሉም አውቀው ነበር? ሐ) ዮሐ 1:12 አንብብ። እነማን በእውነት የእግዚአብሔር ልጆች ሆኑ?  ጥያቄ፡- የሐዋ. ሥራ 14፡16-17 አንብብ። ባለፉት ዘመናት እግዚአብሔር ለሕዝቦች ሁሉ ምን አደረገላቸው?  ዮሐንስ 1፡9 እንደሚናገረው ኢየሱስ ወደ ዓለም በመጣ ጊዜ ለእያንዳንዱ ሰው የሚያበራ ብርሃን ነበር ይላል። ነገር ግን ይህን ክፍል ሲመለከቱት መሠረተ አሳቡ ግልጽ እንደሚያደርገው የኢየሱስ መምጣት ሰዎች ሁሉ ለመዳን እግዚአብሔርን በበቂ ሁኔታ እንዲያውቁ አላደረጋቸውም የሚል ነው። ኢየሱስ የሚያበራው ብርሃን፥ በሰዎች ልቦና ላይ የሚበራ ብርሃን ነው። በልባቸው ውስጥ ያለውን ጨለማ ወደ ብርሃን አውጥቶ ያሳያል ( ዮሐንስ 1፡5)። እርሱ ራሱ እግዚአብሔር ለሰዎች የገለጠው ዋናው መገለጫ ነው። ይህን ብርሃን ያዩ ብዙዎች ግን እንደ ፈጣሪያቸው አድርገው አላወቁትም፥ ደግሞም እግዚአብሔርን የሚገልጥ ብርሃን አድርገው አልተቀበሉትም (ዮሐንስ 15፥10)። ነገር ግን ስለ እርሱ የሰሙት፥ ሰምተውም በእምነት የተቀበሉት የእግዚአብሔር ልጆች ስመሆን ደኅንነትን አገኙ ዮሐንስ 1፡12)። ዮሐንስ 1፡9 እግዚአብሔር፥ ሰዎች ሁሉ ስለ ክርስቶስ ዉርሶ ባይሰሙም፥ ይድኑ ዘንድ በቂ ብርሃን ይሰጣል ብሎ አያስተምርም። ምክንያቱም የጥቅሉ መሠረተ አሳብ፥ ሰዎች የእግዚአብሔር ልጆች ለመሆን ሲፈልጉ፥ አስቀድመው ሊቀበሉት እንደሚገባ በግልጽ ያስተምራል (ዮሐ 1፡12)።  በሐዋርያት ሥራ 14፡16-17 ውስጥ እንደተጻፈው፥ እግዚአብሔር ሕዝቦች ሁሉ በገዛ ራሳቸው መንገድ እንዲሄዱ ትቶአቸው ነበር። ይሁን እንጂ እርሱ እንዴት ያለ ቸር አምላክ መሆኑን የሚመሰክር መልካም ሥራ ማድረጉን አልተወም ነበር። ልብ በሉ እነዚህ ጥቅሶች እግዚአብሔር ለሕዝቡ ደኅንነትን ሰጠ አይሉም። በዚህ ፈንታ እነዚህ ጥቅሶች በርሜ ምዕራፍ 1 ውስጥ ካለው ጋር አንድ ዓይነት አሳብ ይናገራሉ። እርሱም እግዚአብሔር ሰዎች ስለ እርሱ የሚያውቁትን እንዳላወቁ ሆነው የራሳቸውን መንገድ ተከትለው ወደ ኃጢአት እንዲሄዱ አድርጎ ነበር። አሁን ግን በክርስቶስ ወደ ደኅንነት ይጠራቸዋል። ምንም እንኳን በመረጡት መንገድ እንዲሄዱ እርሱ ቢተዋቸውም፥ በተፈጥሮ አማካይነት ስለ ቸርነቱ በአጠቃላይ ሁኔታ መግለጡን ቀጠለ። የሐዋርያት ሥራ 14፡16-7 ያለው ክፍል፥ እግዚአብሔር ስለ ክርስቶስ ጨርሰው ያልሰሙ ሰዎችን ያድናል ብሎ አያስተምርም።  አንዳንድ ጊዜ ቆርኔሌዎስ ስለ ክርስቶስ ከመስማቱ በፊት በእግዚአብሔር አምኖ የዳነ ሰው ምሳሌ ሆኖ የሚቀርብበት ጊዜ አለ። እግዚአብሔር ቆርኔሌዎስን ስለ ክርስቶስ ከመስማቱ በፊት ነበር ያዳነው? የሐዋርያት ሥራ 10፡2 ቆርኔሌዎስና ቤተሰቡ ሃይማኖተኛችና እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ ይላል። ከኢየሱስ የተነገራቸውን መልእክት ከመስማታቸውም በፊት ቢሆን፥ አንዱን እውነተኛ የእስራኤል አምላክን ያመልኩና እርሱንም ለመታዘዝ ይጥሩ ነበር። ቢሆንም፣ ቆርኔሌዎስና ቤተሰቡ የእስራኤል አምላክ አንዱና እውነተኛው አምላክ መሆኑን ተረድተው ሊያመልኩት ይጥሩ የነበሩ አሕዛብ ነበሩ። ነገር ግን የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 10 ቆርኔሌዎስ ለለ ኢየሱስ ከመስማቱ በፊት ጻነ አይልም። ታዲያ እግዚአብሔር እንዲህ ለሚያከብረውና እንዲያድነውም ለሚፈልገው ለቆርኔሌዎስ ምን እደረገለት? ሐዋርያው ጴጥሮስ ሄዶ ስለ ክርስቶስ እንዲሰብክለት ላከው። ቆርኔሌዎስ፥ «በኢየሱስ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአት ይቅርታ ያገኛል» (የሐዋ. ሥራ 10፡43) የሚለውን የጴጥሮስ መልእክት እንደ ሰማ፥ እርሱና ቤተሰቡ በኢየሱስ አመኑ፥ መንፈስ ቅዱስንም ተቀበሉ። ስለ ኢየሱስ የተናገራቸውን መልእክት ከሰሙ በኋላ ነበር ሙሉ የአዲስ ኪዳን አማኞች በመሆን ሙሉውን የአዲስ ኪዳን ደኅንነትን ያገኙት። ስለዚህ የቆርኔሌዎስ ታሪክ እንደሚያመለክተው፥ በአንድ እውነተኛ አምላክ ለማምለክ የሚፈልጉ ሰዎች ካሉ፥ እግዚአብሔር ስለ ክርስቶስ የሚናገር መልእክት የሚያቀርብላቸው ሰው እንደሚልክላቸው ነው። እግዚአብሔር የእርሱን ደኅንነት ለማግኘት በእርሱ ለማመን የሚፈልጉትን አይኮንናቸውም።  3. ክርስቶስ ለኃጢአት ሲል ለመሞት ከመምጣቱ በፊት ሰዎች ቀድሞ በብሉይ ኪዳን

ሰዎች የክርስቶስን መልእክት ሳይሰሙ ሊድኑ ይችላሉ?  Read More »

ለመሆኑ በመጨረሻው ሰዎች ሁሉ ይድናሉ ወይ? 

This entry is part 94 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ሰዎች በክርስቶስ ሥራ ብቻ እንደሚድኑ ተመልክተናል (ትምህርት 13 እና 14)። እንደዚሁም እግዚአብሔር ወደ ራሱ የጠራቸው የሚያምኑና ንስሐ የሚገቡ፥ ኋላም ወደ እግዚአብሔር የሚመለሱ፥ በመጨረሻ የደኅንነትን በረከቶች እንደሚያገኙ ተገንዝበናል (ትምህርት 5 እና 16)። ስለዚህ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተረጋገጠው፥ በክርስቶስ ውስጥ እምነታቸው የተረጋገጠላቸው ብቻ ይድናሉ። በተጨማሪም፥ እግዚአብሔር ክርስቶስን ንቀው ሳይቀበሉት የሚቀሩትን ለዘላለም እንደሚቀጣቸው የሚያስተምሩን ብዙ ጥቅሶች አሉ።  ጥያቄ- ማቴ. 25፡41፥ 46 አንብብ። ሀ) ክርስቶስ አድቃን ባለመሆናቸው የሚፈርድባቸው ወዴት ይሄዳሉ? ለ) 2ኛ ተሰ. 1፡8-9 አንብብ። እግዚአብሔር የማያውቁትን እንዴት አድርጎ ይቀጣቸዋል? ሐ) ራእይ 20፡10፥ 14-15፤ 21፡8 አንብብ። በሕይወት መጽሐፍ ውስጥ ያልተገኙ ምን ይሆናሉ? መ) ለምን ያህል ጊዜ በዚያ ይሆናሉ?  መጽሐፍ ቅዱስ ደኅንነት በክርስቶስ አማካይነት ይመጣል፥ ደግሞም በክርስቶስ የሚያምኑ ይድናሉ ብቻ ብሎ እያስተምረንም። እንደዚሁም ክርስቶስን የሚንቁ ለዘላለም ይጠፋሉ ሲልም ያስተምራል። በማቴዎስ 25፡31-46 ውስጥ ኢየሱስ ስለ በጎችና ፍየሎች ፍርድ ይነግረናል። በዚህም እርሱን የሚቀበሉትንና እርሱን የሚንቁና የሚተዉትን ለማመልከት ነው። ላይቀበሉት ንቀው የተዉት በዘላለማዊ ኩነኔና በእሳት ይቀጣሉ (ቁጥር 41፥46)። በ2ኛ ተሰ. 1፡8-9 ውስጥ ጳውሎስ ሲናገር፥ እግዚአብሔርን የሚያውቁት ከኃይል ክብሩ ተለይተው በዘላለማዊ ጥፋት ይቀጣሉ ይላል። እንደዚሁም ራእይ ምዕራፍ 20፥ ስማቸው በሕይወት መጽሐፍ ተጽፎ ያልተገኘ ሁሉ ቀንና ሌት ስለሚሠቃዩበት የእሳት ባሕር ይገልጻል። ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ በመጨረሻው ጊዜ ሰዎች ሁሉ እንደሚድኑ የማይናገር መሆኑ ግልጽ ነው። በመሆኑም አንዳንዶች ክርስቶስን ባለመቀበላቸው ይጠፋሉ።  ሆኖም ቀን፥ በአዲስ ኪዳን ውስጥ በመጨረሻው ጊዜ ሰዎች ሁሉ እንደሚድኑ የሚያስተምሩ የሚመስሉ ጥቂት ክፍለ-ምንባቦች አሉ። እንግዲህ ክርስቶስን ያልተቀበሉ እንደሚጠፉ በግልጽ የተመለከትን ከሆነ፥ የተባሉት ክፍለ ምንባቦች ታዲያ ምን ያስተምራሉ?  ጥያቄ፡- ሀ) ዮሐ 1፡29ን አንብብ። የእግዚአብሔር በግ የማንን ኃጢአት ነው የሚያስወግደው? ለ) 1ኛ ጢሞ. 2፡6ን አንብብ። ክርስቶስ ራሱን እንደ ቤዛ አድርጎ የሰጠው ለማን ነው? ሐ) 1ኛ ጢሞ. 4፡10ን አንብብ። ክርስቶስ የሚያድነው ማንን ነው? መ) ዕብ 2፡9 አንብብ። ክርስቶስ ሞትን የቀመሰው ለማን ሲል ነው? ሠ) 1ኛ ዮሐ 2፡2ን አንብብ። ክርስቶስ የኃጢአት ማስተሰሪያ የሆነው ለማን ነው? ረ) 1ኛ ዮሐ 4፡14ን አንብቡ። የልጁ መድኃኒትነት ለማን ነው?  ጥያቄ፡– 2ኛ ጴጥ. 3፡9 አንብብ። እግዚአብሔር ወደ ንስሐ እንዲመጣ ማንን ይፈልጋል?  የተወሰኑ የአዲስ ኪዳን ጥቅሶች በአንድ በኩል ክርስቶስ ለመላው ዓለም ኃጢአት መሞቱን ያስተምራሉ። ዮሐ 2፡9 ክርስቶስ እንደ እግዚአብሔር በግ የዓለምን ኃጢአት መውሰዱን ይናገራል። 1ኛ ጢሞ. 2፡6 ደግሞ ክርስቶስ ራሱን አሳልፎ ቤዛ አድርጎ ለጠ ይላል። 1ኛ ጢሞ. 4፡10 ከርስቶስ የሰዎች ሁሉ አዳኝ ነው ይላል። እንዲሁም ዕብ. 2፡9 ክርስቶስ ለሁሉም ሲል ሞትን ቀመሰ ይላል። 1ኛ ዮሐ 2፡2 ክርስቶስ የዓለም ሁሉ ኃጢአት ማስተሰሪያ ነው ይላል። ቀጥሎም በ1ኛ ዮሐ 4፡14 ውስጥ ወልድ የዓለም አዳኝ ነው ይላል። ለማንኛውም ዘርና ጎሣ በዓለም ክፍሎች ሁሉ ላሉ የሰው ልጆች ክርስቶስ ሞቶአል ብለው እነዚህ ጥቅሶች እንደሚያስተምሩ አድርገው ይገምታሉ። ነገር ግን እነዚህ ጥቅሶች ከዚህ የበለጠ የሚናገሩ ይመስላሉ። በዚሁ መሠረት የክርስቶስ የመሥዋዕትነት ሞት በዓለም ላይ ላሉ ለኃጢአታቸው ቤዛ ሊሆን ይችላል የሚል ግንዛቤ ያላቸው ይመስላሉ። 2ኛ ጴጥ. 3፡9 ሰው ሁሉ ንስሐ እንዲገባና የዘላለምን ሕይወት እንዲያገኝ ይላል። ሐዋርያው በ2ኛ ጴጥ. 2፡1-3 ባለው ክፍል ሲያስጠነቅቅ፥ «የዋጃቸውን ጌታ የሚክዱ» ሐሰተኞች መምህራንና ነቢያት ይነሣሉ ብሏል። የክርስቶስ ሞት የኃጢአታቸውን ዋጋ ሊከፍላላቸው ሲችል ነገር ግን ክርስቶስን ንቀውና ችላ ብለው እነርሱ በፈቀዱት መንገድ ሄዱ። እግዚአብሔር ሰው ሁሉ እንዲድን ፈቃዱ ነው፥ የክርስቶስ ሞት ቤዛ ሆኖ የሁሉንም የኃጢአት ዋጋ እንዲከፍል አደረገ (ዮሐ 1፡29)። እነሆ፥ ክርስቶስ ለሁሉም አስፈላጊውን ቤዛ ከፍሏል (1ኛ ጢሞ. 2፡6)። ክርስቶስ በመሥዋዕትነቱ የኃጢአታችን ማስተሰሪያ ሆኖአል (1ኛ ዮሐ 2፡2)። ክርስቶስ ለሰው ሁሉ ሞትን ቀምሶአል (ዕብ. 2፡9)። ክርስቶስ ሁሉን የሚቤዥ መድኅን ነው (1ኛ ጢሞ. 4፡10፤ 1ኛ ዮሐ 4፡14)። የደኅንነት ተግባር ሁሉ ለሰዎች ሁሉ ተፈጽሞአል። ነገር ግን እያንዳንዱ ግለሰብ ክርስቶስ ያደረገለትን ይህን ተግባር ሊቀበል ወይም ላይቀበል ይችላል። ነገር ግን ይህን ክርስቶስ ያከናወነላቸውን ተግባር ሁሉ በእምነት የሚቀበሉ የደኅንነት በረከቶችን ተቋዳሽ ይሆናሉ። በአንጻሩም ክርስቶስ ያደረገላቸውን ሥራ ንቀው የተዉትን ደግሞ ለዘላለም ይቀጣቸዋል። ልብ አድርጉ እነዚህ ጥቅሶች የሚሉት ሰዎች ሁሉ ይድናሉ ሳይሆን፥ የሚድኑት ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ የፈጸመውን ተግባር በእምነት የሚቀበሉት እንደሚሆኑ ነው። በ16ኛው ትምህርት ውስጥ ሌሎች ጥቅሶች እንደሚናገሩት፥ ጌታ ኢየሱስ የፈጸማቸውን ተግባራት የሚቀበሉና መቀበላቸውንም የሚገልጹ የዘላለምን ደኅንነት ያገኛሉ።  ጥያቄ፡- ፊልጵ. 2፡10-11 አንብብ። በክርስቶስ ፊት ተንበርክከው ንስሐ የሚገቡት እነማን ናቸው?  ጥያቄ፡- ሮሜ 5፡18 አንብብ። ሀ) የአንዱ ጽድቅ ሕይወትን የሰጠው ለማን ነው? ለ) ሮሜ 5፡17 አንብብ። በሕይወት ሳሉ በክርስቶስ አማካይነት የሚገዙ እነማን ናቸው? ሐ) 1ኛ ቆሮ. 6፡22 አንብብ። ሕያዋን የሚሆኑት እነማን ናቸው?  ጥያቄ፡- ሮሜ 11፡32 አንብብ። እግዚአብሔር ምሕረቱን ለእነማን አሳየ?  በመጨረሻው ጊዜ ሰዎች ሁሉ እንደሚድኑ በማስመላል፥ አንዳንዶች የሚጠቀሙባቸው ጥቂት ጥቅሶች አሉ። ነገር ግን እነዚህ የሚጠቅሱዋቸው ክፍሎች የሚያስተምሩት በጣም የተለየ አሳብ ነው። ፊልጵ. 2፡10-11 ላይ ስንመለከት፥ ጉልበት ሁሉ ይንበረከካል፣ ምላስም ሁሉ ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ ይመሰክራል፣ ሰዎች ሁሉ የኢየሱስን ደኅንነት ይቀበላሉ ማለቱ ነው ይላሉ። ነገር ግን ይህ ጥቅስ በመጨረሻ ሰዎች ሁሉ ይድናሉ አይልም።  ይልቅስ ፊልጵ. 2፡10-11 የሚለው፥ የተፈጠሩት ሁሉ ማለትም፥ የሰው ልጆች፥ መላእክት ሆኑ ሰይጣናትም ሳይቀሩ፥ በመጨረሻው ኢየሱስ ጌታ መሆኑን ይመሰክራሉ ነው የሚለው። ስለዚህ ክርስቶስን በፈቃዳቸው የተቀበሉት ሁሉ ጌታ መሆኑን ይመሰክራሉ። በአንጻሩ ደግሞ ፈቅደው ያልተቀበሉት በግድ ጌታ መሆኑን ይመሰክራሉ። ስለሆነም፥ ሁሉም ኢየሱስ ጌታ መሆኑን ይመሰክራሉ፣ ይሁን እንጂ፣ ሁሉም ደግሞ አይድኑም።  ሮሜ 5፡18 የአንዱ የአዳም ኃጢአት የቅጣትን ፍርድ በሰው ሁሉ ላይ እንዳመጣ፥ እንዲሁም የአንድ የክርስቶስ የጽድቅ ሥራ ብዙዎችን ከቅጣት ነፃ አድርጎ ሕይወትን ይሰጣል ይላል። ይህ ጥቅስ ይህን ማለቱ፥ ሁሉም ሰው ይጸድቃል ማለቱ አይደለም። ጳውሎስ ለመናገር የፈለገው፥ የአዳም ዘር የሆነ ሁሉ እንደ ተኮነነ፥ እንደዚያው ደግሞ በክርስቶስ የጸደቀ ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንደሚያገኝ ነው። በቁጥር 17 ግልጽ እንደሆነው፥ ጳውሎስ በምድር ላይ ያለ እያንዳንዱ ሰው ይድናል አላለም፥ እርሱ ያለው የእግዚአብሔርን ጸጋና ጽድቅ የተቀበሉ ብቻ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት የዘላለምን ሕይወት ይወርሳሉ ነው። ሮሜ ምዕራፍ 5ም እንደሚያስተምረው፥ አንድ ሰው ለመዳን የእግዚአብሔርን ጸጋ መቀበል አለበት ይላል። ይህን ሲል ሰው ሁሉ ይድናል ማለት አይደለም። በተመሳሳይ መንገድ 1ኛ ቆሮ. 5፡22 ውስጥ ያለው ቃል፥ ሰው ሁሉ ሕያው ይሆናል አይልም። ሕያዋን የሚሆኑት፥ በክርስቶስ የሆኑ ብቻ ናቸው። እንደ መጨረሻው ጥቅስ ሆኖ ሰዎች ሁሉ በጊዜው ፍጻሜ ላይ እንደሚድኑ ይናገራል ተብሎ የሚጠቀሰው ሮሜ 11፡32 ነው። ቃሉም፥ እግዚአብሔር ምሕረቱን ለሰው ሁሉ ያሳያል የሚለው ነው። ነገር ግን ይህ ጥቅስ ሐዋርያው እስራኤላውያን እግዚአብሔርን ሳይቀበሉ ስለ ቀሩ፥ እግዚአብሔር በመጨረሻ ደኅንነትን ለአሕዛብ አሳልፎ እንደ ሰጠ፥ በሦስት ምዕራፎች ላይ የተናገረው ትምህርት ማጠቃላያ ነው። እዚህ ላይ የሐዋርያው ጳውሎስ ማጠቃለያ፥ እግዚአብሔር ደኅንነትን ለመስጠት የሰዎችን ታዛዥነትና ወደ እርሱ መመለስን እንደሚፈልቀ ለማስረዳት ነው። ስለዚህ ደኅንነት ለአይሁዶች ብቻ የተሰጠ ነገር አይደለም። ደኅንነት በዓለም ላሉ ሰዎች ሁሉ ሊሰጥ የሚችል ነው። ሮሜ 11፡32 እግዚአብሔር ሁልጊዜ ምሕረቱን ለሌሎች ለመስጠት በአንዳንድ ሰዎች እምቢተኝነት እንደሚጠቀም ለማስተማር ነው።  ጥያቄ፡- ክርስቶስ ለሰዎች ሁሉ ደኅንነትን ስለ መስጠቱ ያላችሁ አስተያየት ምንድን ነው?  ክርስቶስ ሰዎች ሁሉ ደኅንነትን እንዲያገኙ የፈቀደ በመሆኑ ተስፋ ቆርጠን ግንኙነታችንን ማቆም የለብንም። እነዚህ ሰዎች ከሃይማኖታቸውና ከእድሜያቸው ሁኔታ ወይም አስቀድመው ክርስቶስን ባለመቀበላቸው ወደ እርሱ ሊመጡ አልቻሉ ይሆናል። ሆኖም ክርስቶስ ለእነርሱ ሲል ሞቶአል። ደግሞም እግዚአብሔር ደኅንነት ሊሰጣቸው ተዘጋጅቷል። ስለዚህ የወንጌልን ቃል በታማኝነት ልንነግራቸውና በድፍረት ልንቀርባቸው ይገባል። ምንጭ፡- “አስተምህሮ ክርስቶስና ደኅንነት”፤ ጽሑፍ፣ በዶ/ር ስቲቭ ስራውስ፤ ትርጉም በኃይሉ ልመንህ

ለመሆኑ በመጨረሻው ሰዎች ሁሉ ይድናሉ ወይ?  Read More »

የሚሞቱ ሕፃናት ይድናሉ? 

This entry is part 93 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ሕፃናት በሚሞቱበት ጊዜ የሚድኑ ወይም የማይድኑ ስለመሆናቸው ብዙ ሰዎች ጥያቄዎችን ይሰነዝራሉ። ይህ ጥያቄ ሕፃናት ለሚሞቱባቸው ክርስቲያን ለሆኑ ወላጆች በተለይ ጠቃሚ ነው። ሕፃናት የሚሞቱባቸው ወላጆች በጣም ያዝናሉ። ከዚህም በላይ የሚያስጨንቃቸው ጥያቄ፡- «ልጄን በሰማይ አገኘዋለሁን?» የሚለው ነው።  የሚሞቱ ሕፃናት በቀጥታ ወደ ሰማይ ይሂዱ ወይም ይቅሩ መጽሐፍ ቅዱስ በቀጥታ መልስ አይሰጥም። ሆኖም፣ ለዚህ ጥያቄ መልስ እንድናገኝ የሚረዱን ጥቂት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች አሉ።  ጥያቄ፡- ሀ) 2ኛ ሳሙ. 12፡22-23 አንብብ። ሀ) ዳዊት ሕፃኑ ከሞተ በኋላ ምን ማጽናኛ አገኘ? ለ) መዝሙር 23፡6 አንብብ። ጻዊት ለዘላለም የት እንደሚኖር ይገነዘብ ነበር?  ጥያቄ፡- ማር. 10፡13-16 እንብብ። ሀ) ኢየሱስ የእግዚአብሔር መንግሥት የማን ነው አለ? ለ) ሕፃናትን ወደ ኢየሱስ ባመጡ ጊዜ ምን አደረገላቸው?  ጥያቄ፡- ማቴ. 18፡1-4 እንብብ። ሀ) በእግዚአብሔር መንግሥት ታላቁ ማን ነው? ለ) ማቴዎስ 18፡10-14 አንብብ። እነዚህ ትንንሽ ልጆች በሰማይ ምን ያገኛሉ? (ቁጥር 1) ሐህ እግዚአብሔር ስለ ትንንሽ ልጆች ያለው ስሜት እንዴት ነው (ቁጥር 14)?  በ2ኛ ሳሙ. ምዕራፍ 12 ውስጥ ዳዊት ከቤርሳቤህ ጋር በማመንዘርና ኦርዮንን በማስገደል፥ ስለ ሠራው የከፋ ኃጢአት ነቢዩ ናታን ወደ እርሱ ዘንድ ቀርቦ ነገረው። ጳዊትም ወዲያው ጥፋቱን በኑዛዜ አስታወቀ (ቁጥር 13)። ሆኖም ናታን ዳዊት ለፈጸመው ኃጢአት ተግሣጽ ይሆን ዘንድ ከቤርሳቤህ የተወለደው ሕፃን እንደሚሞት አረዳው። ዳዊትም እግዚአብሔር ምሕረት አድርጎለት ልጁን ከሞት እንዲያተርፍለት በማሰብ በጾምና በጸሎት ራሱን አስ። ግን በሰባተኛው ቀን ሕፃኑ ሞተ። ዳዊትም ሕፃኑ መሞቱን እንደ ሰማ፥ ኦሙን አቆመና ፊቱን ታጠበ፥ ልብሱንም ቀየረ፥ ከዚያም ለእግዚአብሔር ሰዶ ምግቡን በላ። ዳዊት ሕፃኑ ከሞተ በኋላ ይህን ሁሉ ነገር በማድረጉ አገልጋዮቹ ሁሉ ተገረሙ። በምን ምክንያት ነው ሕፃኑ ከሞተ በኋላ ኀዘኑን ያልቀጠለው? ዳዊት በጊዜው የሰጠው መልስ፥ እግዚአብሔር ልጁን ከሞት እንዲያድንለት ተስፋ በማድረግ ኦሞና ጸልዮ እንደ ነበረ ነው። አሁን ግን ልጁ ሞቶአል። ስለዚህ ሊያደርገው የሚችለው ነገር አይኖርም። ጾምና ጸሎቱን ቀጥሎ ቢሆንም፥ ሕፃኑን ከሞት ወደ ሕይወት መልሶ ሊያመጣው አይችልም ነበር። ነገር ግን ዳዊት በመጨረሻ፥ በሚሞትበት ጊዜ ከሕፃኑ ጋር ሊሆን ወደ እርሱ ዘንድ ይሄዳል። ዳዊት ለዘላለም በእግዚአብሔር ቤት እንደሚኖር እርግጠኛ ነበር። በ2ኛ ሳሙኤል 12 ውስጥ ዳዊት ሲናገር፥ አንድ ቀን ሄዶ በሚኖርበት ስፍራ ሕፃኑ የዘላለም ሕይወትን አግኝቶ በእግዚአብሔር ቤት መኖር መጀመሩን ዳዊት ያመነ መሆኑ ይገመታል። ጳዊት በንግሩ ሕፃኑ እንደ ሞተ ሁሉ እርሱም የሚሞት መሆኑን ብቻ ሊናገር አይችልም ነበር? የተናገረው ይህን አይመስልም። ለእግዚአብሔር ሰቶአል፥ እንደዚሁም ራሱን በማጽናናት ላይ ነበር (ቁጥር 22-23)። ጻዊት *ከሕኑ ሞት በኋላ ለእግዚአብሔር መስገድና ከዚያም መጽናናቱ እርሱም አንድ ቀን ሟች መሆኑን ብቻ አሳሰበው ብሎ መገመት ያዳግታል። በቁጥር 3 እንደምናነበው፥ ዳዊት አንድ ቀን ከሕፃኑ ጋር እንደሚሆን ተስፋ ያደረገ ይመስላል። ስለዚህ በ2ኛ ሳሙ. 12፡22-23 የተጻፈው ቃል የሚሞቱ ሕፃናት በእግዚአብሔር ዘንድ ሆነው የዘላለምን ሕይወት እንደሚኖሩ ያመለክታል።  ኢየሱስ በወንጌል ውስጥ ብዙ ጊዜ ስለ ትንንሽ ልጆች ይናገራል። በማርቆስ 10፡13-16 ኢየሱስ እንዲዳስሳቸው ሰዎች ልጆችን ወደ ኢየሱስ ዘንድ እንዳመጡ ተጽፎአል። ደቀ መዛሙርቱ ግን እነዚህ ትንንሽ ልጆች ኢያሱስን ስቶሩታል ብለው ጉ። ን ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን በዚህ ጉዳይ ገሠጻቸው። ለኢየሱስ ልጆች ናቸው። ኢየሱስ ሕፃናትን ተቀብሎ ጠቃሚ የሆነ መንፈሳዊ ትምህርት ያስተምራቸው ነበር። አብረውት ለነበሩት ሰዎች የእግዚአብሔር መንግሥት እነዚህን ሕፃናት ለመሰሉት ነው ሲል ነገራቸው። ኢየሱስ ዘንድ ይመጡ የነበሩ ልጆች ትንንሾች እንደ ነበሩ ግልጽ ነው። ምክንያቱም ቁጥር 16 እንደሚለው አንሥቶም በክንዱ አቀፋቸው ይላል። ምንም እንኳን ልጆቹ ገና የተወለዱ ሕፃናት ባይሆኑም፣ ኢየሱስ በቀላሉ እንሥቶ ሊያቅፋቸው የሚችላቸው ዓይነት ነበሩ። እነዚህ ልጆች ኢየሱስ አዳኛቸው ለመሆኑ እምነታቸውን በሚገልጹበት ዕድሜ ላይ አልነበሩም። ኢየሱስ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደዚህ ላሉት ነው ሲል ተናገረ። እዚህ ላይ ይህን ቃል የመናገሩ ሁኔታ፥ መልካም ሥራቸውን ይዘው ሳይሆን፥ ደካሞች፥ አነስተኞችና በማንም ዘንድ ጎልተው የማይታዩ መሆናቸውን ተገንዝበው ወደ እርሱ ዘንድ የሚመጡ እነርሱ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንደሚገቡ ሲያሳስብ ነው። ኢየሱስ በዚህ ንግግሩ ምናልባት እነዚህ ሁለት ወይም እራት ዓመት የሚሆናቸው ልጆች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ይገባሉ ብሎ በግልጽ አልተናገረም። ግን የንግግሩ አንድምታ ወይም አቅጣጫው ይህንኑ የሚጠቁም ነው። በተለይ በማርቆስ 10፡13-16 ያለው ቃል፥ የሚሞቱ ትንንሽ ልጆች ከእግዚአብሔር ጋር ሆነው የዘላለምን ሕይወት እንደሚኖሩ በጥብቅ የሚያመለክት ክፍል ነው።  በማቴዎስ 18፡1-14 ያለውም ተመሳሳይ ቃል ነው። በዚህ ክፍል የጌታ ደቀ መዛሙርት ኢየሱስን በእግዚአብሔር መንግሥት ታላቁ ማን ነው? ሲሉ ጠየቁት። ኢየሱስም ትንሽ ልጅ በመጥራትና በመካከላቸው በማቆም መልሱን ሰጣቸው። ተጠርቶ የቆመው ልጅ መቆም የሚችል ነበር፥ ግን ጥቅሱ ትንሽ ልጅ ያደርገዋል። እንደዚሁም ኢየሱስ ሲናገር፥ በመንግሥተ ሰማይ ከሁሉም ታላቅ የሚሆኑት ወደ እርሱ ዘንድ የዚህን ልጅ ትሕትና ተላብሰው የሚመጡ መሆናቸውን አስገንዝቧል። በኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚታየው በኢየሱስም ጊዜ የልጆች ድርሻ በጸጥታ በዕድሜ የገፉትን ማገልገል ነበር። ስለዚህ ልጆች ትሑት፥ ራሳቸውን ያስገዙና ታዛዦች መሆን ይጠበቅባቸው ነበር። ስለ ራሳቸው ትልቅነት ስለማያስቡ፥ ሁልጊዜ ጥገኝነትና ጎልቶ ያለመታየት ሁኔታ ይታይባቸዋል። ስለዚህ ኢየሱስ ወደ እርሱ ለሚመጡት ሰዎች ሁሉ እንደዚህ ያሉ ልጆችን በምሳሌነት በማቅረብ እነርሱ ወደ እርሱ ሊመጡ የሚችሉበትን ሁኔታ ይገልጥላቸው ነበር። ይህም በትሕትናና በእርሱ ላይ በመመርኮዝ፥ ኢየሱላ የሚሰጣቸውን ለመቀበል ብቁ አለመሆናቸውን በመገንዘብ ወደ እርሱ እንዴት እንደሚቀርቡ ምሳሌ ሆኖ የሚገልጽላቸው ነበር።  ነገር ገን ኢየሱስ ነገሩን ከፍ አድርጎ በማጉላት፥ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደዚህ ሕፃን ናት አለ። በቁጥር 10 ውስጥ ክሎ ሲናገር፥ ለእነዚህ ታናናሾቹ «በሰማይ መላእክት አሉዋቸው አለው። ኢየሱስ ይህን ሲናገር አባባሉ ትንንሽ ልጆች በሰማይ አብረዋቸው ሆነው የሚጠብቋቸው መላእክት አሉ ማለቱ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የእግዚአብሔር ሰዎች የሚጠብቁዋቸው መላእክት እንዳሉዋቸው የሚጠቁሙ ክፍሎች አሉ (መዝ 34፡7፤ 91፡11)። እንግዲህ እንዲህ ከሆነ፣ የኢየሱስ አነጋገር ትንንሽ ልጆች ከእግዚአብሔር ሰዎች ጋር የሚቆጠሩ መሆናቸውን ያመለክታል። እንዲያውም በቁጥር 14 ውስጥ አባቴ ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዳቸውም እንዲጠፉ አይፈልግም በማለት ግልጽ ያደርገዋል። ይህ ጥቅስ እግዚአብሔር ለልጆቹ በጣም ትልቅ ግምት እንደሚሰጥ ይገልጻል። ነገር ቀን ከዚህ የበለጠ የሚናገር ይመስላል፥ ይህም ለማቴዎስ 18፡14 ትንንሽ ልጆች አይጠፉም የሚለው ነው።  በዚህ ክፍል እንደተገለጸው፥ እግዚአብሔር የሚሞቱትን ትንንሽ ልጆች ወደ እርሱ ዘንድ አምጥቶ የዘላለም ሕይወትን የሚሰጣቸው ስለመሆኑ ግንዛቤ ይፈነጥቃል። ሆኖም እነዚህ ሕፃናት ከሞቱ በኋላ ወደ ሰማይ የሚገቡት በልዩ ተሰጥኦዋቸው ወይም ከኃጢአት ነፃ ስለሆኑ አይደለም። በ1ኛውና በ12ኛው ትምህርት ውስጥ እንደ ተከታተልነው፥ ሰዎች ሁሉ በኃጢአት መወለዳቸው የታወቀ ነው። ምንም እንኳን መጽሐፍ ቅዱስ ሕፃናት ደኅንነትን ስለሚያገኙበት መንገድ ባይገልጽም፥ ክርስቶስ በሞቱና በትንሣኤው የሰጠውን ደኅንነት፥ እምነትን በተግባር ለመግለጽ ላልደረሱ ሕፃናት እግዚአብሔር ሰጥቶአቸዋል።  እንዲሁም እግዚአብሔር ሕፃናት ስለተጠመቁ እንደማያድናቸው፥ ደግሞም ስላልተጠመቁ እንደማይኮንናቸው እርግጠኞች ልንሆን እንችላለን። እንደተመለከትነው ሁሉ፥ ጥምቀት ደኅንነትን አያመጣም። ነገር ግን ጥምቀት ለሰዎች የማዳን እምነታቸው ምልክትና ማኅተም ነው። ሕፃናትን የማጥመቅ ሁኔታ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ የተነሣበት አንዱ ምክንያት፥ ክርስቲያኖች በሚሞቱበት ጊዜ ወደ ሰማይ የሚሄዱ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ነበር። ነገር ግን ሕፃናትና ትንንሽ ልጆች በጥምቀት ምክንያት እግዚአብሔር ያድናቸዋል የሚል የመጽሐፍ ቅዱስ አሳብ የለም። የእግዚአብሔር ሕፃናትን የማዳን ነገር፥ እርሱ በክርስቶስ ሞት ትሩፋት ተጠቅሞ እምነታቸውን ለመግለጽ ለማይችሉ ሕፃናትና ትንንሽ ልጆች የሚሰጠው ሉዓላዊ የሆነ ምሥጢራዊ ሥራው ነው።  ጥያቄ፦ ልጆቻቸውን በሞት ላጡ ወላጆች ማጽናኛነት በእነዚህ ጥቅሶች እንዴት ትጠቀማላችሁ?  ወላጆች ልጆቻቸውን በሞት በሚያጡበት ጊዜ፥ ከባድ የሆነ የትምህርተ መለኮት የማጽናኛ ቃል አያስፈልጋቸውም። ይህን በመሰለ ከባድ ወቅት ከእነርሱ ጎን ሆኖ መጽሐፍ ቅዱስን አብሮ ማንበብና እብሮ መጸለይ ያሻል። መጽሐፍ ቅዱስን በምታነቡበት ጊዜ፥ አሁን ያጠናናቸውን ክፍሎች ብታነቡ የተሻለ ነው። እነዚህ ክፍለ ምንባቦች እግዚአብሔር ለልጆቻቸው ስላለው ፍቅር በመግለጽ ያጽናናቸዋል። ምንጭ፡- “አስተምህሮ ክርስቶስና ደኅንነት”፤ ጽሑፍ፣ በዶ/ር ስቲቭ ስራውስ፤ ትርጉም በኃይሉ ልመንህ

የሚሞቱ ሕፃናት ይድናሉ?  Read More »

ቅዱስ ቁርባንን መቀበል፥ ደኅንነት ያስገኛል? 

This entry is part 92 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ጥያቄ፡- ዮሐ 6፡53-54 እንብብ። ሀ) ጌታ ኢየሱስ፥ አንድ ሰው ሕይወትን ማግኘት ከፈለገ ምን ያድርግ ይላል? ለ) ጌታ ኢየሱስ አንድ ሰው ሥጋውን ቢበላና ደሙን ቢጠጣ ምንን ያገኛል አለ?  ጥያቄ ዮሐ. 6፡35 አንብብ። ጌታ ኢየሱስ አንድ ሰው እንዳይራብ ወይም እንዳይጠማ ምን ያድር አለ?  ብዙ ሰዎች የእግዚአብሔርን ጸጋ ተቀብለው ለመዳን ሲሉ ቅዱስ ቁርባንን መቀበል ይፈልጋሉ። ሌሎች ደግሞ ካልቀረቡ በስተቀር ሊድኑ እንደማይችሉ ይሰማቸዋል። የተቀሩት ሰዎች ደግሞ፥ የቅዱስ ቁርባን ተካፋዮች በመሆን የእግዚአብሔርን ጸጋ በመቀበል መዳናቸውን እንደሚያረጋግጡ ያምናሉ። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ እነዚህ ሰዎች በቅዱስ ቁርባን ላይ መሳተፍ በዮሐንስ 6፡53-54 ውስጥ እንደተጻፈው የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ የሚያሰጣቸው መሆኑን ለአሳባቸው ድጋፍ አድርገው ያቀርባሉ፡ በዚህ ክፍል ኢየሱስ የሚናገረው፥ ሰዎች «ሥጋውን በልተው፥ ደሙን የሚጠጡት» ሕይወትን ለማግኘት ስለሆነ፥ ማንም ሰው ሥጋውን የሚበላና ደሙን የሚጠጣ ሁሉ የዘላለም ሕይወትን ያገኛል። ለአንዳንድ ሰዎች ጌታ ኢየሱስ ስለ ቅዱስ ቁርባን የተናገረ ይመስላቸዋል። በመጀመሪያ ጊዜ፥ ኢየሱስ ቅዱስ ቁርባንን ለደቀ መዛሙርቱ በሰጠ ጊዜ፥ «ይህ ለእናንተ የሚሰጥ ሥጋዬ ነው። ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው ደሜ የሚፈጸም አዲስ ኪዳን ነው» አላለምን? (1ኛ ቆሮንቶስ 11፡24-25። እነዚህ ሰዎች በቅዱስ ቁርባን ጊዜ ኅብስቱን መብላትና ከጽዋው መጠጣት የዘላለምን ሕይወት የሚሰጣቸው አድርጎ ኢየሱስ የተናገረ አድርገው ያምናሉ።  ሆኖም፤ ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን እንዲበሉና ደሙንም እንዲጠጡ ኢየሱስ ሲነግራቸው ምን ማለቱ እንደሆነ በጣም የተሻለ ማብራሪያ አለ። በዮሐንስ 6፡53-54 ውስጥ ኢየሱስ ስለ ኅብስት ከአይሁዶች ጋር ያደረገው ረጅም ውይይት ከፊሉ ይገኛል። የመጽሐፍ ቅዱስን አንድ ክፍለ ምንባብ ትርጉም የመተንተን የመጀመሪያውና እጅግ በጣም ጠቃሚ የሆነው መመሪያ፥ የክፍለ ምንባቡን ጭብጥና ይዘት ማጥናት ነው። ኢየሱስ በዮሐንስ 6፡52-53 ውስጥ ስለተናገረው ጥቅል ትርጉም ለመተንተን የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 6 መላውን ክፍል ማጥናት ይገባናል። በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 6 በመጀመሪያዎቹ ጥቅሶች ላይ ኢየሱስ አምስት እንጀራና ሁለት ዓሣዎችን ለአምስት ሺህ ሰዎች እንደ መገበ እንነዘባለን። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ሕዝቡን ተለይቶ ሄደ። ወዲያው ቀን አገኙት (ዮሐንስ 6፡25)። ሕዝቡ ኢየሱስን ባገኙት ጊዜ፥ እንጀራ ስላበላቸው የፈለጉት መሆናቸውን ነገራቸው። ቀጥሎም፥ ለሚጠፋ ምግብ አትሥሩ፥ የዘላለም ለሚሆን ምግብ ሥሩ አላቸው (ዮሐንስ 26፡27)። ነገር ግን አይሁዶቹ በሥጋዊ ምግብ ፍላጎት ስላየለባቸው፥ ኢየሱስ እነርሱን ለመመገብ ሌላ ተአምር እንዲፈጽም ጠየቁት (ዮሐ 6፡31-32)። ከዘላለም ሕይወት ይልቅ ምግብን አስበልጠው ስላዩ፥ እርሱ ከሰጣቸው ሥጋዊ ምግብ ይልቅ እርሱን እንዲች አሳሰባቸው። እውነተኛ የእግዚአብሔር እንጀራ ከሰማይ የመጣው መሆኑን ነገራቸው (ዮሐ. 6፡33)። ሰዎቹ ግን አሁንም ኢየሱስ ስለ ዓለማዊ እንጀራ የሚናገር መሰላቸው። ይህን እንጀራ እንዲሰጣቸው ጠየቁት (ዮሐ 6፡34)። በጣም ጠቃሚ በሆነ ጥቅስ አማካይነት ኢየሱስ ስለሚናገረው በትክክል ያስገነዝባቸዋል። በዮሐንስ 6፡35 ውስጥ ኢየሱስ ራሱ ከሰማይ የመጣ እንጀራ መሆኑንና ወደ እርሱ የሚመጣ ጨርሶ እንደማይራብ፥ የሚያምንበትም የማይጠማ መሆኑን ይነግራቸዋል። ኢየሱስ የመንፈስን ምግብና መጠጥ የማግኘቱ መንገድ ወደ እርሱ ዘንድ መምጣትና በእርሱ ማመን መሆኑን በማስረዳት፥ ወደ እርሱ ዘንድ ቢመጡ እርሱ ከሰማይ የመጣ እንጀራ ስለሆነ በፍጹም የማይራቡና በመንፈስም የማይጠሙ መሆናቸውን አስገንዝቦአቸዋል። ኢየሱስ ከሰማይ ስለ መምጣቱ በተናገረ ጊዜ አይሁዶች አጉረመረሙ (ቁጥር 41-42)። ምክንያቱም እርሱ የተናገረው ቃል አልገባቸውም ነበር። ኢየሱስ በመመገብ ሥጋዊ ፍላጎታቸውን የፈጸመላቸው፥ መንፈሳዊ ትምህርትን ሊያስተምራቸው እንደነበረ አልገባቸውም ነበር። ኢየሱስም አያይዞ፥ ሰዎች ሊመጡበት የሚገባ ከሰማይ የመጣ እንጀራ መሆኑን ስለ ራሱ ተናገረ (ዮሐ 6፡50-51)። ሰዎች ሥጋውን እንዲበሉና ደሙን እንዲጠጡ ሲናገራቸው (ዮሐ 6፡53-54)፥ በቁጥር 32 ውስጥ በተናገረው ስልት ዓይነት ነበር አሳቡን የገለጸው። ኢየሱስ ሊናገር የፈለገውን የአነጋገር ስልትና ምሥጢር ቁጥር 35 ውስጥ ትርጉሙን አብራርቶታል። ሥጋውን መብላትና ደሙን የመጠጣት ምሥጢር ወደ ኢየሱስ የመምጣትና በእርሱ የማመን ምሥጢር ነው። ኢየሱስ ለአይሁዶች ሲናገር፥ የዘላለም ሕይወትን ለማግኘት ቢሹ ወደ እርሱ ዘንድ መጥተው በእርሱ ማመን እንዳለባቸው አሳስቦአቸዋል።  ቅዱስ ቁርባን በእያንዳንዱ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ እጅግ በጣም ጠቃሚ የሆነ ሥነ ሥርዓት ነው። ቅዱስ የሆነ የአምልኮ ጊዜ ነው። በዚህን ጊዜ አማኙ ኃጢአቱን ይናዘዛል፥ የክርስቶስን ሞት ያስባል፥ ከእግዚአብሔርና ከሌሎች ምእመናን ጋር ይገናኛል። ደግሞም ኢየሱስ ደኅነትን ሊሰጠው ስለ ፈጸመው ሁሉ ምሥጋና ያቀርባል፥ እርሱንም ያመልካል። ሆኖም ቅዱስ ቁርባንን መቀበል ማንንም ሊያድን ወይም የዘላለም ሕይወትን ሊሰጥ አይችልም። የዘላለምን ሕይወት የምናገኘው፥ ወደ ኢየሱስ ዘንድ በእምነት በመምጣት ነው። ይህንንም ራሱ በዮሐንስ 6፡35 ውስጥ ተናግሮአል። ምንጭ፡- “አስተምህሮ ክርስቶስና ደኅንነት”፤ ጽሑፍ፣ በዶ/ር ስቲቭ ስራውስ፤ ትርጉም በኃይሉ ልመንህ

ቅዱስ ቁርባንን መቀበል፥ ደኅንነት ያስገኛል?  Read More »

ደኅንነትን የመቀበል ጥያቄ፣ እምነትና ጥምቀት  

This entry is part 91 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

በትምህርት 16 ውስጥ፥ ክርስቶስ በመስቀል ላይና በትንሣኤው የሰጠንን ደኅንነት እንዴት ሰዎች በየግላቸው ሊያገኙ እንደሚችሉ ተምረን ነበር። በዚህም ለደኅንነት መሠረታዊ የሆነ አንድ ዋና ነገር፥ በሦስት የተለያዩ መንገዶች መገለጣቸውን ተመልክተናል። እነዚህም ሦስቱ ንስሐ፥ እምነትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ ናቸው። ሰዎች ኃጢአታቸው ከእግዚአብሔር ለይቶአቸው እንደ ነበረ መገንዘብና ከእግዚአብሔር ጋር ለመታረቅ በራሳቸው ሥራና በሌላም ነገር መታመን እንደሌለባቸው አውቀው፥ በአኳያው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱና በትንሣኤ ብቻ ማመን አለባቸው። ስለዚህ በዚህ አኳኋን ሰዎች ከኃጢአታቸው በሚመለሱበትና ወደ ኢየሱስ ለደኅንነት በሚመጡበት ጊዜ፥ እግዚአብሔርም የደኅንነትን በረከቶች ይሰጣቸዋል። ይህንን አዳኝ የሆነ እውነተኛ እምነትን ያገኙ ሁሉ፥ ኢየሱስን የመከተልና የመታዘዝ የሕይወት ፈለግ ይኖራቸዋል። መልካም ሥራቸው የደኅንነታቸው ውጤትና ፍሬ ይሆናል።  ነገር ግን ሰዎች ደኅንነት እንዴት ሊገኝ እንደሚችል ብዙ ጥያቄዎችን ይሰነዝራሉ። በዚህ ሳምንት ትምህርታችን ከእነዚህ ጥያቄዎች ውስጥ ጥቂቶችን ለመመለስ እንሞክራለን።  መጀመሪያ ቀን-  እምነትና ጥምቀት  ክርስቲያኖች በክርስቶስ ያላቸውን እምነት በሰዎች መካከል ለመግለጥ ቢሹ፥ ሊያደርጉት የሚገባ አንዱና ዋናው ነገር፥ ቅዱስ ጥምቀትን መቀበል ነው። ምክንያቱም በክርስቶስ የሚያምኑ ሁሉ ጥምቀትን እንዲቀበሉ ታዝዘዋል። በአዲስ ኪዳንም ውስጥ ቅዱስ ጥምቀት ከደኅንነት ጋር በጥብቅ የተቆራኘ መሆኑን በመገንዘብ ደኅንነትን ለማግኘት መጠመቅ ነበረባቸው። በ16ኛው ትምህርት ውስጥ ለደኅንነት አስፈላጊ የሆነው አንዱ ዐቢይ ነገር በሦስት መንገዶች ተገልጧል። እነዚህም ሦስቱ መንገዶች፡- ንስሐ፥ እምነትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ ናቸው። እንግዲህ የጥምቀት ሚና ምንድን ነው? ጥምቀት ለደኅንነት ማግኛ በሁለተኛው ደረጃ ተፈላጊ ነገር መሆኑ ነው? ሰዎች እንደ መጀመሪያ የደኅንነት ክፍል አድርገው በማሰብ በክርስቶስ ይመኑና ከዚያ በኋላ እንደ ሁለተኛው የደኅንነት ክፍል ቅዱስ ጥምቀትን ይቀበሉ? በዛሬ ትምህርታችን ላይ ስለ ጥምቀት ስላሉዋችሁ ጥያቄዎች አንሥተን ሁሉንም በዝርዝር ልንወያይባቸው አንችልም። ሆኖም ቅዱስ ጥምቀት ደኅንነትን ለእኛ ለማስገኘት፥ ከንስሐና ከእምነት ጋር እንዴት ያለ ተዛምዶ እንዳለው፥ በሚነሡ ጥያቄዎች ላይ መልስ ለመስጠት እንጥራለን።  1. በአዲስ ኪዳን ውስጥ አማኞች በክርስቶስ እንዳመኑ ወዲያውኑ ያጠመቁ ነበር። ይህም ጥምቀት ውጫዊ ምልክትና የውስጣዊ እምነታቸው ማኅተም ነበር።  ጥያቄ፦ ማቴ. 28፡19-20 አንብብ። የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት በምንሆንበት ጊዜ ምን ማድረግ ይኖርብናል?  ጥያቄ፡- የሐዋ. ሥራ 2፡41 አንብብ። ጴጥሮስ በጴንጠቆስጤ ቀን በለማው የምስክርነት ቃል ያመኑ ሰዎች ቃሉን መቀበላቸውን ለማሳየት ምን አደረገ?  ጥያቄ፡- የሐዋ. ሥራ 8፡36-38 አንብብ። ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ በክርስቶስ ያመነ መሆኑን ለማረጋገጥ ምን ለማድረግ ፈለገ?  ጥያቄ፡- የሐዋ. ሥራ 10፡47-48 አንብብ። ቆርኔሌዎስና ቤተሰቡ መች ተጠመቁ?  ጥያቄ፡- የሐዋ. ሥራ 16፡14-15 አንብብ። ሊድያ መች ተጠመቀች?  ጥያቄ፡- የሐዋ. ሥራ 16፡31-33 አንብቡ። ሀ) ሐዋርያው ጳውሎስ የፊልጵስዩስ ወኅኒ ቤት ዘበኛ ደኅንነትን እንዲያገኝ ምን ማድረግ እንዳለበት ነገረው? ለ) የፊልጵስዩስ ወኅኒ ቤት ዘብ መች ተጠመቀ?  በጥንታዊትዋ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ፥ በኢየሱስ ያመኑ ሰዎች ሁሉ፥ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት መሆናቸውን ለማሳየት ወዲያውኑ ይጠመቁ ነበር። በማቴዎስ 28፡19-20 ላይ ኢየሱስ አሥራ አንዱ ደቀ መዛሙርት ወደ ዓለም ሁሉ ሄደው ብዙ ደቀ መዛሙርትን እንዲያፈሩ እዝዞአቸው ነበር። ስለዚህ ሰዎች ኢየሱስን ለመከተል በሚወስኑበት ጊዜ የእርሱ ተከታዮች መሆናቸውን ለማስመስከር በመጀመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቅዱስ ጥምቀትን መቀበል ነው። በጰንጠቆስጤ ቀን ሐዋርያው ጴጥሮስ ስብከቱን ለኢየሩሳሌም አይሁዶች ካሰማ በኋላ፥ በሐዋርያት ሥራ 2፡41 ላይ እንደተጻፈው፥ የሐዋርያውን መልእክት የተቀበሉ ሁሉ ተጠመቁ ይላል። በመሆኑም ኢየሱስን እንደ መሢሐቸውና ከኃጢአት እንደሚያድን መድኅን ከተቀበሉ በኋላ ሁሉም በአንድ ቀን ተጠመቁ። በሐዋርያት ሥራ 8፡26-38 ውስጥ ፊልጶስ በትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 53 ውስጥ ስለ ክርስቶስ የተጻፈውን ቃል ከኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ጋር ተወያየ። ወደ ውኃ በቀረቡ ጊዜም፥ ጃንደረባው በራሱ ፍላጎት ለመጠመቅ ጠየቀ። ጥምቀትን በመቀበል፥ በኢየሱስ የማመንና እርሱንም አዳኙ አድርጎ መቀበሉን ሕይወት አለመሰከረ። እግዚአብሔር የልድያንና የቤተሰቦችዋን ልብ እንደ ከፈተ፥ የኢየሱስ ተከታይ መሆንዋን ለመግለጥ ተጠመቀች (የሐዋ. ሥራ 16፡14-15)። ጴጥሮስ በቆርኔሌዎስ ቤት በሰበከ ጊዜና በኢየሱስ የሚያምኑ ሁሉ የኃጢአት ይቅርታ እንደሚያገኙ (የሐዋ. ሥራ 10፡43) ባብራራበት ወቅት ያዳምጡ በነበሩ ሰዎች ላይ መንፈስ ቅዱስ ወረደ፥ (የሐዋ. ሥራ 10፡44)። ጴጥሮስም እነዚህ ሰዎች በልባቸው ክርስቶስን አምነው እንደ አዳኛቸው መቀበላቸውን ይህ ድርጊት ሊያረጋግጥለት ቻለ። እርሱም እነዚህ ሰዎች ምንም ቃል ሳይተነፍሱ ወዲያው እንዲጠመቁ አዘዘ።  ምናልባት አዲስ አማኞች በክርስቶስ እንዳመኑ ወዲያውኑ ይጠመቁ እንደ ነበረ ግልጽ ምሳሌ ሆኖ የሚጠቀሰው የሐዋርያት ሥራ 16፡31-33 ውስጥ ያለው ክፍል ነው። ሐዋርያው ጳውሎስና ሲላስ በፊልጵስዩስ ከተማ በነበሩ ጊዜ ከአንዲት አገልጋይ ክነበረች ልጃገረድ ውስጥ ርኩስ መንፈስን ስላስወጡ ታስረው ነበር። በሌሊትም እግዚአብሔር የምድር መንቀጥቀጥ እንዲሆን አደረገ፥ የታሰሩበት ሰንሰለትም ተፈታ፥ የእስር ቤቱ በርም ተከፈተ፡፡ የወኅኒ ቤቱ ዘብ በሩ መከፈቱን ባወቀ ጊዜ ራሱን ሊገድል ነበር። ይህን ያደረገበት ምክንያት እስረኞቹ ሁሉ ያመለጡ ስለ መሰለውና እርሱም በእነርሱ ገመድ እንደሚገባ ስለ ተሰማው ነው። ጳውሎስ ግን ድምፁን ከፍ አድርጎ እስረኞቹ ሁሉ በእስር ቤቱ ውስጥ መሆናቸውን ነገረው። የእስር ቤቱ ዘብ ይህን ጊዜ በደስታ ተውጦ ወደ ጳውሎስ በመምጣት፥ «ለመዳን ምን ማድረግ ይገባኛል?» ሲል ጠየቃቸው? ሐዋርያው ጳውሎስ ሰውዩው ለሚድንበት ሁኔታ ብዙ ነገር ለመዘርዘር አልፈለገም። አንድ ነገር ብቻ እንዲያደርጎ መከረው፥ ይህም፥ «በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እመን፡፡» በዚያን ምሽት የወኅኒ ቤት ዘበኛው ጳውሎስንንና ሲላስን ሊያስተናግድ ወደ ቤቱ ይዟቸው በሄደ ጊዜ ሐዋርያው ጳውሎስ እርሱንና ያመኑትን ቤተሰቦቹን አጠመቃቸው።  ይህ ታሪክ በሦስት ምክንያቶች ጠቃሚ ሆኖ ይገኛል። መጀመሪያ፥ ጳውሎስ ለደኅንነት ይበጃል ብሎ የተናገረው አንድ አስፈላጊ ነገር ነበር። እርሱም እምነት ነው። ሐዋርያው፥ የወኅኒው ጠባቂ ለመዳን መጠመቅ አለበት አላለም። ይህ እንግዲህ በትምህርት 16 ውስጥ የተማርነውን ያላስበናል። ይህም ለደኅንነት አስፈላጊ የሆኑት ንስሐና እምነት ናቸው የሚለው ነው። ሁለተኛው ደግሞ፥ ምንም እንኳን በእምነታቸው ብቻ ድነው ቢሆኑም፥ ጳውሎስ የወኅኒ ቤቱን ዘበኛና ቤተሰቡን ወዲያው አጠመቃቸው። የአዲሱ እምነታቸው ውጪአዊ መግለፃ ጥምቀታቸው ነበር። ሦስተኛ፥ ዘበኛውና ቤተሰቡ ስለ አዲሱ እምነታቸው የሚያውቁት ጥቂት ቢሆንም ተጠመቁ። መሬት እስከ ተንቀጠቀጠበት ጊዜ ድረስ፥ የጥንታዊ ግሪክና የሮማ ጣዖታት ተከታዮች ነበሩ። ስለ ኢየሱስ የሚያውቁት ጥቂት ነበር። ስለ ብሉይ ኪዳን የአይሁድ እምነትም ግንዛቤአቸው አናሳ ነበር። የገባቸውና ያወቁት ኢየሱስ የደኅንነት መንገድ መሆኑን ስለነበረ፥ በእርሱ አመኑ። እምነታቸውንም ስለ ገለጡ ጳውሎስ ሊያጠምቃቸው ቻለ።  እነዚህ ቁጥሮች በጥንቷ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጥምቀት የነበረውን ሚና እንድንረዳ ይረዱናል፥ ጥምቀት የውስጣዊው እምነት ውጫዊ መገለጫ (አዋጅ ነው፡፡ ሰዎች ክርስቶስን እንደ አዳኛቸው ሲያምኑት፥ አሁን ክርስቶስን እንደሚያምኑና እንደሚከተሉ ለሰው ሁሉ ለማወጅ ይጠመቁ ነበር፡ ጥምቀት ወደ ደኅንነት የሚወስዳቸው መንገድ አልነበረም፡፡ ይልቁንም የደኅንነት መንገዶቻቸው ንስሐና እምነት ነበሩ፡፡ ነገር ግን ጥምቀት ሊሆን የተገባውና አፋጣኝ የሆነ የውስጣዊው እምነት ውጫዊ መገለጫ ነበር። ጥምቀት ውስጣዊውን እምነት ለሌሎች ለማሳየት የሚጠቅም ውጫዊ ሥርዓት ነበር። አንድ ሰው ባይጠመቅ እንዳላመነ ይቆጠር ነበር። አንድ ሰው ንስሐ ሲገባና ቢያምን ውስጣዊ እምነቱን ሊመሰክር እንደ ውጫዊ ምልክት አድርጎ በፍጥነት ይጠመቅ ነበር።  አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች ጥምቀትን፥ የውስጣዊ እምነት ምልክትና ማኅተም ነው ይላሉ። አንድ ሰው እምነት ያለው ለመሆኑ፥ ጥምቀት ለሌሎች ምልክቱ ነው። እንደዚሁም ጥምቀት ይህንኑ እምነት የሚያረጋግጥ ማኅተም ነው። ጥምቀት ለጥንት ቤተ ክርስቲያን ምን እንደ ነበረ አንድ ምሳሌ እነሆ፡- በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚደረጉ የሠርግ ሥነ ሥርዓቶች ውስጥ አንዱ የቀለበት ሥነ ሥርዓት ነው። ሙሽራውና ሙሽራዋ የቃል ኪዳናቸው ምልክትና ማኅተም አድርገው ቀለበት ይለዋወጣሉ። በሕይወት ዘመናቸውም ቀለበቶቻቸውን እንደ ጋብቻ ቃል ኪዳን ምልክትና ማኅተም አድርገው፥ አንዳቸው የሌላው መሆናቸውን ለማሳየት በጣቶቻቸው ላይ እንዳጠለቋቸው ይኖራሉ።  ሰዎች ያለ ቀለበት ሥነ ሥርዓት ሊጋቡ ይችላሉ? አዎን፥ ሊጋቡ ይችላሉ። ነገር ግን ይህ የቀለበት ሥነ ሥርዓት፥ የጋብቻ ዋና የውጪአዊ ምልክትና እንዲሁም ሙሽሮቹ እርስ በርስ ለሚያደርጉት የቃል ኪዳን ማኅተም ነው። ሙሽሪትና ሙሽራው እርሱም የእርሷ እርሷም የእርሱ ለመሆናቸው የሚያሳዩበት ምልክት የቀለበት ማድረግ ሥነ ሥርዓት ስለሆነና ይህ ድርጊት ተለምዶ በመካሄድ ላይ በመሆኑ ሙሽራው ወይም ሙሽራይቱ አንዳቸው

ደኅንነትን የመቀበል ጥያቄ፣ እምነትና ጥምቀት   Read More »

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 3 

This entry is part 90 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ በተከታተልነው ትምህርት ላይ፥ መጽሐፍ ቅዱስ በእውነት ዳግም የተወለዱ ክርስቲያኖች ለዘላለም ዋስትናቸው የተጠበቀ መሆኑን እንደሚያስተምር ተገንዝበናል። እግዚአብሔር እነርሱን የማዳኑን ተግባር እነርሱ ከእርሱ ጋር የታረቁ መሆናቸውን በማሳወቅ ጀምሮአል፤ ይህንንም የጀመረውን የማዳን ተግባር በታማኝነት ከግብ ያደርሳል። በዚሁ መሠረት የመጨረሻው የደኅንነታቸው ዋስትና እንዲሆንም የራሱን መንፈስ ቅዱስ ሰጥቶአቸዋል፤ ይህንንም ሲያደርግ ማንም ከፍቅሩ ሊለያቸው እንደማይችል ተስፋውን አክሎ ሰጥቶአቸዋል። እነዚህ አማኞችም የክርስቶስ አካል ክፍል ስለሆኑ፥ ኃጢአት በሚሠሩበት ጊዜ ጌታ ኢየሱስ ራሱ ይማልድላቸዋል። እነዚህ ሁሉ አስደናቂ የሆኑ እውነታዎች በእርግጥ ዳግም የተወለዱ ክርስቲያኖች የደኅንነታቸው ነገር ዋስትና ያለውና የተረጋገጠ መሆኑን ያስገነዝበናል።  ነገር ግን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ክርስቲያኖች ደኅንነታቸውን የሚያጡ ዓይነት ትርጉም የያዙ የሚመስሉ ክፍሎች የሉምን? እንደዚሁም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ደኅንነታቸውን ያጡ አማኞች ስለመኖራቸው በምሳሌነት የሚጠቀስባቸው ክፍሎች የሉምን? እንግዲህ በዛሬው ትምህርታችን ውስጥ፥ አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ እንደሚችሉ የሚመስሉ ክፍሎች ስለሚሰጡት ትምህርት እንመረምራለን። እነዚህን ክፍሎች ሁልጊዜ ልናስታውሳቸው ከሚገባን ሁለት መንፈሳዊ መመሪያዎች በመነሣት የምናጠና ሲሆን፥ መመሪያዎቹም፡- 1) በክርስቶስ ማመንን ለማመልከት የሚደረግ የሃይማኖት መግለጫ፥ በክርስቶስ ከሚኖረን እውነተኛ እምነት ጋር አንድ አይደለም። 2) እውነተኛ ክርስቲያኖች ኃጢአትን ይሠራሉ፥ ከዚህ በኋላም ዘላለማዊ ደኅንነታቸውን ሳያጡ ስለሠሩት ኃጢአት እግዚአብሔር ይቀጣቸዋል።  1. በክርስቶስ ላይ ያለንን እምነት ማሳወቅ፥ በክርስቶስ ላይ ካለን እውነተኛ እምነት ጋር አንድ አይደለም።  ጥያቄ፡- 1ኛ ዮሐ 2፡19 አንብብ። ሰዎች የክርስትና እምነታቸውን ጨርሰው በሚተዉበት ጊዜ ይህ ምንን ያመለክታል? ጥያቄ፡- ዮሐ 8፡31 አንብብ። ሰዎች በእውነት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ለመሆናቸው ምልክቱ ምንድን ነው?  ጥያቄ፡- ዕብ. 3፡14 አንብብ። ከክርስቶስ ጋር ወራሾች ለመሆናችን ምልክቱ ምንድን ነው?  በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከምናገኛቸው እውነታዎች መካከል እጅግ በጣም ጠቃሚ የሆነው፥ በክርስቶስ ማመንን መናገር፥ በክርስቶስ ላይ ካለ እውነተኛ እምነት ጋር አንድ አለመሆኑን በግልጽ የሚያስረዳው ነው። በ16ኛው ትምህርት ውስጥ እንደ ተመለከትነው፥ ሰዎች በክርስቶስ የሚያምኑ መሆናቸውን መግለጣቸው ብቻ ወይም እርሱን በአዳኝነት አምነው የተቀበሉ መሆናቸውን መናገራቸው ብቻ በቂ አለመሆኑን ተገንዝበናል። እንደዚሁ ሁሉ ሰዎች ከልብ ሳይሆን ላይ ላዩን ብቻ ክርስቶስን የተቀበሉ አስመስለው ቢጸልዩ ይህም በቂ አይደለም። ይህ ብቻም አይደለም፥ ሰዎች ሰይጣንን ክደውና ኮንነው ክርስቶስን መቀበላቸውን መናገራቸው ብቻም በቂ አይደለም። ስለዚህ ከልብ ሳይሆን በውጪአዊ ስሜት ላይ ብቻ የተመሠረተ በክርስቶስ ስለማመን የሚደረግ የአፍ መግለጫ ብቻም ማንንም ሊያድን አይችልም። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ከልባቸው አምነው የተቀበሉትን ማዳን የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ኃጢአታቸው ከእግዚአብሔር የለያቸው መሆኑን የሚገነዘቡትና ለደኅንነታቸው በራሳቸው መልካም ሥራ ምንም ተስፋ ሳያደርጉ እርሱን የሚማጠኑትን እግዚአብሔር ያድናቸዋል። በኢየሱስ የሚመኩትንና እርሱን ተገን የሚያደርጉትን ብቻ እግዚአብሔር ያድናል።  እንደዚሁም ሰዎች ክርስቶስን ከልባቸው አምነው በመቀበላቸው ምክንያት፥ ለእርሱ ታማኞች ሆነው እንደሚኖሩ፥ በውጪአዊ ድርጊታቸው በምልክትነት የሚገልጡ መሆናቸውን መጽሐፍ ቅዱስ አክሎ ያስተምረናል። ሰዎች በክርስቶስ የሚያምኑ መሆናቸውን በይፋ ከመግለጥ ቢቆጠቡ ደግሞም ቢያቆሙ ይህ ድርጊት በመጀመሪያ ደረጃ እውነት ዳግም ያልተወለዱ መሆናቸውን የሚያሳይ ምልክት ነው። 1ኛ ዮሐ. 2፡19 ውስጥ ብዙ ሐሰተኞች የሆኑ ክርስቲያኖች የተቀበሉትን እምነትና ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር ያላቸውን እንድነት መተቸውን ይገልጻል። ዮሐንስ ሲናገር የተቀበሉትን እምነትና ከሊሎች አማኞች ጋር የነበራቸውን ኅብረት በተዉ ጊዜ፡ ይህ እነታቸውን ከጠበቁት ጋር አንድነት የሌላቸው ለመሆኑ ምልክት ነው ይላል። ክርስቶስን እንደ አዳኛቸው አላወቁትም፡ ቀድሞውንም ቢሆን እውነተኞች ክርስቲያኖች አልነበሩም። እውነተኞች ክርስቲያኖች ቢሆኑ ኖር፡ ዮሐንስ በእምነታቸው ጸንተው ሰቆዩ እና ከሌሎች አማኞች ጋር የነበራቸው አንድነትም አብሮአቸው በዘለቀ ነበር ብሏል። ምንም እንኳን ሌሎች እንደ እውነተኛ ክርስቲያኖች ቆጥረው ቢቀበሉዋቸውም፥ በመጨረሻው ላይ የተቀበሉትን እምነት መተዋቸው የሚያስረዳው ጌታን በእውነት ያላወቁት መሆናቸውን ነው። ጌታ ኢየሱስ በዮሐንስ 8 ውስጥ ደቀ መዝሙሮቹ መሆናቸውን ሊገልጡለት ለምክሩ ለተሰበሰቡ ብዙ አይሁዳውያን ሲናገር እንመለከታለን። በቁጥር 31 ውስጥ ኢየሱስ በእውነት እነርሱ ደቀ መዛሙርቱ ከሆኑ በቃሉ እንደሚኖሩ አስረዳቸው። በእውነት ዳግም በክርስቶስ የተወለዱ አማኞች እስከ መጨረሻው ድረስ ለኢየሱስ ቃል ታማኞች ሆነው ይኖራሉ። በምንም እኳኋን ክርስቶስን በመጨረሻው ጊዜ ሙሉ በሙሉ አይተዉትም።  ዕብራውያን 3፡14 እምነታችንን እስከ መጨረሻ አጽንተን ብንይዝ ከክርስቶስ ጋር ወራሾች ነን ሊል ይነግረናል። ይህ ጥቅስ የተገለጠበትን የግሥ ጊዜ በጥንቃቄ መመልከቱ እሳቡን ለመገንዘብ ይረዳናል። ቁጥሩ እምነታችንን እስከ መጨረሻው ድረስ አጽንተን ብንይዝ ከክርስቶስ ጋር ወራሾች እንሆናለን አይልም። እንዲህ ቢል ኖር የወደፊቱ ደኅንነታችን እነታችንን አጥብቀን ለመያዝና ለመጽናት በምናደርገው ጥረት ላይ ይመሠረታል የሚል አንድምታ ሰያዘ ነበር። ታዲያ ይህ ጥቅስ ምን ይላል? ጥቅሱ የሚለው እምነታችንን እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንይዝ፥ ከክርስቶስ ጋር ወራሾች ለመሆን ችለናል ነው። አስቀድመን በእውነት ድነናል፥ እንዲሁም በእውነት ም ተወልደናል የሚለው አሳብ በክርስትና እምነታችን ውስጥ አንተን ከመቆየታችን አቅጣግ የሚታይ እውነታ ነው። እንዲያው ብቻ በአንደበታቸው ክርስቲያኖች መሆናቸውን የሚለፍፉ ሁሉ፥ እውነተኞች ክርስቲያኖች አይደሉም። በእውነት ዳግም የተወለዱ ክርስቲያኖች ብቻ በክርስትና ዴታቸው ጸንተው ባለማወላወል ይዘልቃሉ። እንዲህ ያሉ የልብ ክርስቲያኖች ቀደም ሲል በይፋ የገለጡትን እምነታቸውን በምንም ሁኔታ በመጦረሻው ላይ ተስፋ ቆርጠው አይተዉም።  ጥያቄ፦ ማቴ 7፡21-23 አንብብ። በኢየሱስ ስም ታላቅ ኃይል የታየበት ሥራ በፊልሙ ለቶ ላይ በፍርድ ቀን ምን ብይን ይሰጥባቸዋል?  ጥያቄ፦ ማቴ 10፡1፣4 እንብብ ሀ) ኢየሱስ ለአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት የን ሥልጣንን ሰጣቸው? ለ) ዮሐ 6፡70-71 አንብብ። ይሁዳ ገና ደቀ መዝሙር ሆኖ ጌታን ሊከተል በነበረበት ጊዜ፥ ኢየሱስ ስለ ይሁዳ ምን ተናገረ?  ጥያቄ፦ ዘኁልቁ 24፡15-16 እንብብ። የበለዓም ትንቢት በምን ራእይና ዕውቀት ላይ የተመሠረተ ነበር? ለ) ኢያሱ 13፡22 አንብብ። የበለዓም ሙያ ምን ነበር? ምን እየተባለ ይጠራ ነበር? ሐ) 2ኛ ጴጥ. 2፡1፥5 አንብብ። ሐዋርያው ጴጥሮስ ስለ በለዓም ሊናገር እንዴት ያለ ሰው ነበር አለ?  ብዙ ሰዎች ዳግም የተወለዱ ክርስቲያኖችን እንደሚያውቁና እነዚህም ክርስቲያኖች ኋላ ላይ በክርስቶስ የነበራቸውን እምነት እንዳቋረጡ ይናገራሉ። እነዚህ ይህን የሚሉ ሰዎች፥ እነዚያ ክርስቲያኖች በእንቅስቃሴአቸው መልካም የሆነ የክርስትናን ሕይወት የኖሩ ስለሚመስሉ በእርግጥም ዳግም የተወለዱ እንደሆኑ አድርገው ያውቋቸው ነበር፡ ምናልባትም እነዚህ ሰዎች ኃይለኞች ወንጌላውያን ሆነው ይሆናል ፤ ወይም ታምራትን ይሠሩና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚከናወኑ ተግባራትንም ሲያከናውኑ ይታዩ ነበር። ምናልባትም ታላላቅ ክርስቲያናዊ መሪዎች ነበሩ። ኋላ ግን የክርስትና እምነታቸውንና ሕይወታቸውን ትተዋል። እነዚህ ሰዎች ደኅንነታቸውን ያጡ የእውነተኞች ክርስቲያኖች ምሳሌ ሊመስሉ ይችሉ ይሆናል። በዚሁ መንገድ መጽሐፍ ቅዱስ አማኛች ስለሚመስሉ ሰዎች አያሌ ምሳሌዎችን ያቀርባል። እነዚህ ሰዎች እውነተኞች አማኞች አለመሆናቸውን በመጨረሻው ተግባራቸው ያሳዩ ናቸው። ጌታ ኢየሱስ በማቴዎስ 7፡21-23 ሲናገር ብዙዎች በስሙ ትንቢትን እንደሚናገሩ፥ ተአምራትን እንደሚያደርጉና አጋንንትን እንደሚያወጡ ገልጾአል። ነገር ግን እነዚህ ሰዎች እርሱ በፍጹም ስለማያውቃቸው፣ በመጨረሻው ቀን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት አይገቡም። ምንም እንኳ እነዚህ ሰዎች በሚያደርጉዋቸው ድንቅ በሆኑ መንፈሳዊ ተግባራት የኢየሱስ ተከታዮች መስለው ቢታዩም፡ በውስጣቸው ግን ዳግም የተወለዱ አማኞች አልነበሩም። ማስተዋል ያለባችሁ ነገር ኢየሱስ አንድ ጊዜ አውቃቸዋለሁ አለማለቱና የእነርሱም ደኅንነትን የማጣት ሁኔታ ነው። ጌታም፣ በፍጹም አላውቃችሁም ነው ያላቸው። በእውነትም፥ የተረጋገጠላቸው በክርስቶስ የሚታመኑ አማኛች አልነበሩም።  ይሁዳ እንዲህ ያለ ሰው ነበር። ማቴዎስ 10፡1 እንደሚነግረን፣ ጌታ ኢየሱስ ለአሥራ ሁለቱም ደቀ መዛሙርት የመፈወስንና አጋንንትን የማውጣት ሥልጣንን ሰጥቷቸው ነበር። በተለይ ቁጥር 4 እንደሚለው፣ ይሁዳ ከአሥራ ሁለቱ መካከል አንደኛው ነበር። ስለዚህ ይሁዳ በኢየሱስ ሰም አጋንንትን ያወጣና ደግሞም ይፈውስ ነበር። ነገር ግን ይሁዳ በጭራሽ በክርስቶስ የሚያምን እውነተኛ አማኝ አልነበረም። በዮሐንስ 6፡70-71 ውስጥ፥ ይሁዳ በውጢአዊው ሁኔታው የኢየሱስ ተከታይ በነበረበት ጊዜ፥ ኢየሱስ አሥራ ሁለቱን የመረጠ ቢሆንም፥ እንደኛው (ይሁዳ) ን ዲያብሎስ እንደ ነበረ ተናግሮአል። በዚያን ጊዜ ገና ይሁዳ ሐሰተኛ ደቀ መዝሙር መሆኑን ኢየሱስ አመልክቷል። ቢሆንም ከደቀ መዛሙርቱ መካከል እንጻቸውም እንኳን ይሁዳ ሐሰተኛ ደቀ መዝሙር መሆኑን የጠረጠረ አልነበረም። ኢየሱስና ይሁዳ ራሱ ብቻ ይህን ያውቁ ነበር። ነገር ን በእኛ ዮሐ 219 ውስጥ እንደምናነበው፥ በመጨረሻው ላይ

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 3  Read More »

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 2 

This entry is part 89 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

በትናቱ ዕለት ትምህርታችን ስለ አማኞች ዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጥ ወይም ጥበቃ ማጥናት ጀምረናል። በዚህ ትምህርት ላይም፥ አማኞች በደኅንነታቸው ረገድ ሁኔታው ዋስትና እንዳለውና የተጠበቀላቸው መሆኑን ተመልክተናል። ይህ ሊሆን የቻለበትም ምክንያት፥ ከእግዚአብሔር ጋር በመታረቃቸውና ሰላምንም በመመሥረታቸው ምክንያትና እንደዚሁም እግዚአብሔር ሁልጊዜ የጀመረውን ሥራ ስለሚፈጽም ነው። ከዚህም ጋር መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉ በመሆናቸውና ኢየሱስ ራሱ ስለሚጠብቃቸው፥ ከዚህም የተነሣ አዲስ ሰዎች ስለሆኑ ነው። ዛሬ ደግሞ አማኞች በተጨማሪም ለዘላለም የተጠበቁ የሆኑበት ምክንያት እያንዳንዳቸው የክርስቶስ አካል ክፍሎች ስለሆኑና ኃጢአት በሚሠሩበት ጊዜ ኢየሱስ ስለሚማልድላቸውም እንደሆነ እናጠናለን። እንዲሁም በርሜ ምዕራፍ 8 ውስጥ ስለ አማኞች ዘላለማዊ ዋስትና መጠበቅ ጠቃሚ የሆነ አጠቃላይ ትምህርትን በመከታተል፥ አማኞች ስለ ዘላለማዊ ዋስትናቸው መጠበቅ ስለሚኖራቸው ስሜት እናስተውላለን።  6. አማኞች ዘላለማዊ ዋስትናቸው የተጠበቀ ነው። ምክንያቱም እያንዳንዳቸው የክርስቶስ አካል ክፍሎች ስለሆኑ ነው። ጥያቄ፡- 1ኛ ቆሮ. 12፡27 አንብብ። እያንዳንዱ አማኝ ምን ይሆናል?  በ17ኛው ትምህርት ውስጥ እንደ ተመለከትነው፥ በክርስቶስ በማመን መድኃኒቱ አድርጎ የተቀበለው ሁሉ፥ የክርስቶስ የአካሉ ክፍል እንደሚሆን አስተውለናል። 1ኛ ቆሮ. 12፡27 እንደሚያስገነዝበው፥ እያንዳንዱ አማኝ የአካሉ ክፍል እንደሆነና እያንዳንዶቹ አማኞችም በመሰባሰብ የክርስቶስ አካል እንደሚሆኑ ይናገራል። ስለዚህ በዚህ ምድር ላይ ስላለን ሁላችን በአንድነት የክርስቶስ አካል በመሆን፥ እርሱን ለዓለም በጉልህ ማሳየት ይገባናል። አማኞች በእውነተኛው አኳኋን ደኅንነታቸው የተረጋገጠላቸው ካልሆነ በስተቀር፥ የክርስቶስ አካል አንድ መሆኑ ቀርቶ ይከፋፈላሉ። ቀን አንድ ሰው በክርስቶስ ካመነና ለዘላለሙም የአካሉ ክፍል ከሆነ፥ ደኅንነቱም ለዘላለም ዋስትና ያለውና የተጠበቀ ይሆናል።  7. አማኞች ኃጢአት በሚሠሩበት ጊዜ፥ ኢየሱስ ስለሚማልድላቸው፥ ለዘላለም ዋስትናቸው የተጠበቀ ነው።  ጥያቄ፡- ሮሜ 8፡34 እንብብ። ኢየሱስ አሁኑኑ ስለ እኛ ምን እያደረገ ነው?  ጥያቄ፡- 1ኛ ዮሐ 2፡1-2 አንብብ። ሀ) አማኞች ኃጢአት በሚያደርጉበት ጊዜ ስለ እነርሱ ሆኖ የሚናገር ማን ነው? ለ) ምልጃቸው በምን ምክንያት ውጤታማ ሊሆን ቻለ?  ጥያቄ፡- ዕብ 7፡24-25 አንብብ። ኢየሱስ ስለ እኛ የሚያደርገው ጸሎት ውጤት ምንድን ነው?  ብዙ ክርስቲያኖች ኃጢአት በሚሠሩበት ጊዜ እግዚአብሔር የሰጣቸውን ደኅንነት የሚቀማቸው እየመሰላቸው ይሸበራሉ። ነገር ግን በትናንትናው ትምህርታችን ውስጥ በሮማ 8፡34 እንደ ተመለከትነው፥ ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቀኝ ሆኖ ስለ እኛ እንደሚማልድ ተገንዝበናል። በ1ኛ ዮሐ 2፡1 እኛ ኃጢአት በምናደርግበት ጊዜ ኢየሱስ ስለ እኛ እንደሚማልድ በቀልጽ ይነግረናል። ኢየሱስ ስለ እኛ የሚያቀርበው ምልጃ ውጤታማ እንደሚሆን እርግጠኞች ልንሆን እንችላለን፥ ምክንያቱም እርሱ ራሱ የእግዚአብሔርን ቁጣ የሚመልስ መሥዋዕት ስለሆነ ነው። የኃጢአታችንን ቅጣት የከፈለልንና በእግዚአብሔር ቁጣ ምክንያት ስለ ኃጢአታችን የተሠቃየው እርሱ አሁንም ኃጢአት በምንሠራበት ጊዜ ይማልድልናል። ዕብራውያን 7፡24-5 ያለው ክፍል ክርስቶስ ባለማቋረጥ ስለ እኛ የሚያደርገው ምልጃ ፍጹም የሆነ ደኅንነት እንደምናገኝ ያረጋግጥልናል። በትምህርት 12 ውስጥ እንደተመለከትነው፥ እግዚአብሖር ኃጢአትን ይጠላል። በነገው ትምህርትም እንደምናጠናው የክርስቲያኖች ኃጢአት ሁልጊዜ የከፋ ውጤት ይኖረዋል። ነገር ቀን ኃጢአት በምንሠራበት ጊዜ፥ ኢየሱስ ይማልድልናል። አማኞች ደኅንነታቸውን የሚያጡበት ጊዜ ቢኖር፥ የኢየሱስ ጸሎት በማይመለስበት ጊዜ ነው። በእርግጥ ደግሞ የኢየሱስ ጸሎት ሁልጊዜ ይመለሳል። ኢየሱስ ሁልጊዜ የሚማልድላቸው በመሆኑ፥ አማኞች ደኅንነትን በማግኘታቸው ረገድ እርግጠኞች መሆናቸውን ሊገነዘቡ ይገባል።  8. ጠቃሚ የሆነ ማጠቃለያ፡- ሮሜ 8፡31-39  ጥያቄ፡- ሮሜ 8፡31–39 አንብብ። ሀ) እግዚአብሔር ልጁን ለእኛ የሰጠ ስለሆነ፥ ከልጁ ጋር ምንን እንደሚሰጠን እርግጠኞች ልንሆን እንችላለን? (ቁጥር 32) ለ) ሐዋርያው ጳውሎስ በቁጥር 33፡34ና 35 ውስጥ ለጠየቃቸው ጥያቄዎች ውስጠ ታዋቂ ሆኖ የቀረበው መልስ ምንድን ነው? ሐ) እንደ ቁጥር 38ና 39፥ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን የሚችል ምንድን ነው?  በሮሜ 8፡31-39 የቀረበው ቃል፥ ጳውሎስ ከሮሜ ምዕራፍ 5-8 ያቀረበው ትምህርት ማጠቃለያ ወይም የተሰባሰበ አሳብ ሲሆን፥ አሳቡም ስለ አማኛች የደኅንነት ዋስትና መረጋገጥ የሚናገር ነው። በሮሜ 8፡31-32 ውስጥ የማጠቃለያ አሳቡን በሚጀምርበት ጊዜ፥ እግዚአብሔር እስከ ዛሬ ያደረገልን ተግባር፥ ያጸድቀናል፥ መንፈስ ቅዱስን ይሰጠናል፥ ያስታርቀናል፥ የጀመረውን ሥራ ይፈጽምልናል፥ ደግሞም የዘላለም ሕይወትን ይሰጠናል በማለት ያረጋግጥልናል። ከዚያም በቁጥር 33-35 ውስጥ ጳውሎስ አማኞች ለዘላለም የጻኑ መሆናቸውን ለመግለጽ፥ ሦስት ጥያቄዎችን ይጠይቃል። በመጀመሪያም፥ የሚያቀርበው ጥያቄ፥ «በእግዚአብሔር ፊት በድፍረት ቆሞ አማኞችን በደለኞች ናቸው ብሎ በመክሰስ፥ በኃጢአታቸው ምክንያት መሠቃየት ይገባቸዋል የሚል ይኖር ይሆን?» የሚል ሲሆን፥ መልሱም «በእግዚአብሔር ፊት በድፍረት ቆሞ አማኛችን የሚከስስ ሊኖር አይችልም። ምክንያቱም እግዚአብሔር አስቀድሞ «በደለኞች አይደሉም»፣ በኢየሱስ ደም ምክንያት «ጻድቃን» ናቸው ሲል አስታውቋልና ነው። ስለዚህ እግዚአብሔር አስቀድሞ «በደለኞች አይደሉምስላለ፥ በክርስቶስ አማኛች የሆኑትን ሁሉ ተሳክቶለት ሊከስስ የሚችል ከቶ አይኖርም።  በሁለተኛ ደረጃ ጳውሎስ በሚያቀርበው ጥያቄ፥ አማኞች በኃጢአታቸው ምክንያት እንዲቀጡ ማን ሊኮንናቸው ይችላል? የሚል ነው። ለጥያቄውም መልስ ለመስጠት ሲል ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አስቀድሞ ለአማኞች ኃጢአት ቅጣት አጸፋውን የከፈለ በመሆኑ፥ ፈራጅ በሆነው በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ እንደሚማልድላቸው ያስታውሰናል። ሰይጣን አማኞችን በእግዚአብሔር ፊት በሚከስስበት ጊዜ፥ በአማኞች ፈንታ ለመናገር ጌታ ኢየሱስ በእዚያ ነው። እርሱም ሲናገር፥ «አዎን! ይህ ሰው ሊኮነን የሚገባው ኃጢአተኛ ነው። ነገር ግን እኔ ስለ እርሱ ኩነኔ ሥቃይን ተቀብያለሁ። ስለ ኃጢአቱም ይከፍለው የነበረውን ቅጣትም ከፍየለታለሁ። ስለዚህ የሚኮነንበት ምንም ምክንያት አይኖርም» በማለት ይመልሳል። በትምህርት 17 ውስጥ በሮሜ 8፡1 እንደተመለከትነው፥ ከክርስቶስ ጋር ኅብረት ያላቸው ሁሉ አይኮነኑም። ጳውሎስ ደግሞም ሲናገር፥ ከክርስቶስ ጋር የተባበርን እንደ መሆናችንና ኢየሱስም በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ ስለ እኛ ስለሚማልድ፥ ኩነኔ ጨርሶ ሊኖርብን አይችልም ይላል።  ሦስተኛው ጳውሎስ የሚያቀርበው ጥያቄ አማኞችን ማንኛውም ነገር ቢሆን፥ ከእግዚአብሔር ፍቅር የሚለያቸውና የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ ውርስ የሚያሳጣቸው እንደሌለ ነው። በተለይም እርሱን የሚያሳስበው በአማኞች ሕይወት ውስጥ ስለሚከሰተው የሥቃይ ሁኔታ ነው። በአማኞች ሕይወት ውስጥ ሥቃይ አለ ማለት፥ የአማኞች ሕይወት ከእግዚአብሔር ፍቅር ይለያል ማለት ነውን? እንደዚሁም አማኞች በስደት፥ በረሃብ፥ በድኅነትና በጦርነት ምክንያት ሥቃይን ቢቀበሉ፥ ይህ ሁሉ ከእግዚአብሔር ፍቅር ለይቶ ዘላለማዊ ውርሳቸውን ያሳጣቸዋል ማለት ነውን? አይደለም! ጳውሎስ መዝሙር 44፡22ን በመጥቀስ፥ የእግዚአብሔር ተከታዮች ለሆኑት ሁሉ ሥቃይን መቀበል የተለመደ ክስተት በመሆኑ እንደ ቁጣ ሊታይ አይገባም ይላል። በእግዚአብሔር የሚያምኑ ሰዎች ሁሉ ሁልጊዜ እንደሚታረዱ በጎች ይቆጠራሉ። ምንም እንኳን አማኞች ሥቃይን የሚቀበሉ ቢሆኑም፥ በመጨረሻው ቀን ድልን እንደሚቀዳጁና ዘላለማዊ ውርስን እንደሚያገኙ የተረጋገጠላቸው ሐቅ ነው (ቁጥር 37)።  በመጨረሻውም ላይ፥ በቁጥር 38 እና 39 ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ ታይቶ ያልታወቀና አሁን የታየ እንግዳ ነገርም ቢሆን፥ አማኞችን ከእግዚአብሔር ፍቅር ፈጽሞ ሊለያቸው እንደማይችል በማረጋገጥ ነገሩን ይቋጫል። በዚህ ማጠቃለያ አሳቡም ላይ አማኞችን ከእግዚአብሔር ፍቅር ለመለየት የሚሞክሩ ጠላቶችን በዝርዝር ይገልጻል። እነዚህም፥ ዲያቢሎስ፥ ሞት፥ ወደፊት የሚሆነው ነገር ጥርጣሬና የመሳሰሉትን አደናቃፊዎች ከዘረዘረ በኋላ፥ ምንም ልንፈራው የሚገባን ነገር ከቶ ሊኖር እንደማይችል በማበረታታት ነገሩን ይደመድማል። የትኞቹም ዓይነት ጠላቶቻችን ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለዩን አይችሉም፡፡  Tያቄ፡- ሀ) ከእግዚአብሔር ሊለየን ይሆናል ብላችሁ አንዳንዴ የምትፈሩት ነገር ምንድን ነው? ለ) ይህ የተመለከታችሁት ክፍል እንዴት ሊያጽናናችሁና አለኝታ ሊሆናችሁ ይችላል?  ሁሉም አማኞች ቢሆኑ በሕይወታቸው ውስጥ ጥርጣሬ የሚያጋጥማቸው ወቅት አለ። ይህም ሊከሰት የሚችለው ስለ መዳናቸው ተጠራጥረው ፍርሃት በሚሰማቸው ጊዜ ነው። ይህ የጥርጣሬ ስሜትም ወደ አእምሮአችን የሚገባው በሰይጣን አማካይነት ነው። ሰይጣን ስለ እግዚአብሔር ፍቅርና ስለ እርሱ እንክብካቤ እንድንጠራጠር ይፈልጋል። ስለ ዘላለማዊ ደኅንነታችንም ጥርጣሬ እንዲገባን ያደርጋል። ከዚያም ያለፈው ኃጢአታችን ፊታችን ተደቅኖ እንዲታወሰንና ጨርሶ ወደ እግዚአብሔር ፊት ለመቅረብ ብቃት የሌለን አድርጎ ያሳየናል። እኛም ምንኛ ኃጢአተኛች መሆናችንን በምናስታውስበት ጊዜ፥ ስለ ደኅንነታችን መጠራጠር እንጀምራለን። እንደዚሁም ሰይጣን የአጋንንቱን ኃይል አጉልቶ ሊያስታውሰን ይሻል። ከዚህም የተነሣ ስለ ሞትና ወደፊት ስለሚሆነው ሁሉ እንድንጠራጠር ያደርጋል። «ምን ሊሆን እንደሚችል የምታውቀው ምን ነገር አለ?» በማለት ይጠይቃል። ይቀጥልና፥ «ወደፊት ስለሚሆነው ነገር፥ ስለ ሞትና መቃብር መፍራት አለብህ። እንዲሁም የማንኛውንም አጋንንቶቼን ኃይልና አቅም መፍራት አለብህ» ይላል። ነገር ግን እግዚአብሔር በተስፋው ቃል እንዳረጋገጠው፥ በክርስቶስ የሚያምኑትን ሁሉ ኃጢአታቸውንና በደላቸውን ይቅር ብሎአቸዋል። እርግጥ ነው፥ እኛ የእግዚአብሔር ደኅንነት የማገባን ኃጢአተኞች ነን። በዚህ በኃጢአታችን ሁኔታና በክፋታችን

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 2  Read More »

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫ እና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 1 

This entry is part 88 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

በክርስቲያኖች መካከል የሚነግ አንደኛው አስቸጋሪና አከራካሪ የሆነ ርእሰ ጉዳይ፥ እውነተኛና ዳግም የተወለዱ አማኞች ደኅንነታቸውን ይዘውት ይቆያሉ ወይስ ያገኙትን የሚያጡበት ሁኔታ ይኖራል? የሚለው ነው። / ማንኛውም ክርስቲያን በአንድ ወቅት ክርስቶስን አምነው የተቀበሉና ኋላ ግን ይህን እምነታቸውን የተዉ ሰዎችን የሚያውቅ ይመስለኛል። አብዛኛዎቹ እማኞች አንድ ጊዜ መልካም የክርስትና አካሄድ የነበራቸውና ኋላ ላይ በኃጢአት ውስጥ ከመውደቃቸው የተነሣ ያንን የመልካም ሕይወት አኗኗርን የማይኖሩ ሰዎች ያውቃሉ። ከዚህ የሕይወት ገጠመኝ የተነሣ፣ ብዙ ሰዎች በአንድ ወቅት ድነው ይዘውት የነበረውን ሕይወት በሌላ ጊዜ ከኃጢአታቸው የተነሣ ወይም በክርስቶስ ማመናቸውን ስለሚያቆሙ፥ የተቀበሉትን ደኅንነት ያጣሉ የሚለውን አሳብ መቀበሉ ቀላል ነው፡፡ ነገር ግን በትናንትናው ትምህርታችን ላይ እንደተከታተልነው ሁሉ፥ ሌላውን የደኅንነቱን በረከቶች የሚቀበሉትን ሁሉ ክብርን እንደሚቀበሉ እግዚአብሔር ተስፋ ይሰጣል፡ ምንም እንኳን ደኅንነታቸውን ያጡ የሚመስሉ ሰዎችን የምናውቅ ብንሆንም፥ እኛ መደምደሚያ ልናደርገው የሚገባን መጽሐፍ ቅዱስ የሚሰጠውን ትምህርት እንጂ የግል ተሞከሮአችንን ወይም ወንዛቤአችን ሊሆን አይገባም፡ አማኞች ስላላቸው ዋስትና ወይም መተማመኛ+ እንደዚሁም የክርስትና ሕይወታቸውን በማራመድ ረገድ ስላላቸው ጽናትና የመንፈስ ብርታት መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያስተምረናል? ስለሆነም በሚቀጥሉት ሦስት ቀናት ውስጥ ስለ እነዚህ ጥያቄዎች መጽሐፍ ቅዱስ የሚሰጣቸውን መልሶች እንመረምራለን።  ጥያቄ፦ ሮሜ 4፡22-25፤ 5፡1-2፥ 6፥8-10 አንብቡ። ሀ) ጽድቅ ለማን ተሰጠ? (ሮሜ 4፡22-25) ለ) በእምነት ከጸደቅን ምንን እናገኛለን? (ሮሜ 5፡1) ሐ) በእምነት ከጸደቅን ትርፋችን ምን ይሆናል (ሮሜ 5፡2)? መ) ለዘላለም ሕይወት ያለን ተስፋ በምን ምክንያት አያሳፍረንም? (ሮሜ 5፡5) ሠ) ከቁጥር 8-10 በተጻፈው መሠረት፥ ከእግዚአብሔር ቁጣ እንዴት እንደምንድንና የዘላለምን ሕይወት እንዴት እንደምናገኝ አብራራ?  1. አማኞች ለዘላለም ዋስትና አላቸው፥ ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ጋር የታረቁ መሆናቸው ስለ ታወቀና ከእርሱም ጋር ሰላም ስላላቸው ነው።  ባለፈው ትምህርት 18 ላይ አስደናቂ ስለሆነው የጽድቅ ደኅንነት በረከት አጥንተን ነበር። በዚሁ ወቅት ሰዎች ክርስቶስን እንደ መድኃኒታቸው አምነው ሊቀበሉ፥ እግዚአብሔር ከበደላቸው ነፃ መሆናቸውን እንደሚያሳውቅ ተገንዝበናል። እግዚአብሔር እነዚህ ሰዎች ከእርሱ ጋር የታረቁ መሆናቸውን በይፋ ያሳውቃቸዋል። በኢየሱስ ባላቸው እምነት፥ እግዚአብሔር የኢየሱስን ጽድቅ ጽድቃቸው አድርጎ ይሰጣቸዋል። እግዚአብሔር ይህ በኢየሱሰ ጽድቅ ላይ የተመሠረተ ጽድቅን የሚሰጣቸው ላለፈው ኃጢአታቸው ብቻ ሳይሆን፥ ለሠሩት ኃጢአት ሁሉ ነው፡፡ ሮሜ 5፡1-2 እግዚአብሔር አማኞች ከእርሱ ጋር ታርቀው ኅብረት መመሥረታቸውን ስለ ገለጠ፥ ከአሁን ወዲያ ከእርሱ ጋር ሰላም አላቸው ይላል። በእምነት ከእርሱ ጋር ለታረቁት፥ እግዚአብሔር በክርስቶስ መስቀል ላይ የተጠቀመበትን የማስታረቅ ተግባር እዚህም በሥራ ላይ ያውላል። ስለሆነም አማኞች ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ሰላም፥ ለወደፊቱ ለሚያገኙት ዘላለማዊ ሕይወት ተስፋን ይሰጣቸዋል። በአዲስ ኪዳን ውስጥ «ተስፋ» የሚለው ቃል አሳብ መተማመን ወይም ዋስትናን ያመለክታል። ከእግዚአብሔር ጋር ያለን እርቅ ቀደም ሲል የታወቀ በመሆኑ፥ ለዘላለም ዓለም እግዚአብሔር ባለበት እኛም እንደምንሆን ለትናው የተረጋገጠልን ነው።  ጳውሎስ በሮሜ 5፡8-10 ውስጥ፥ ጽድቅ ለዘላለማዊ ደኅንነታችን ማረጋገጥ እንደሚሰጠን ሰፋ አድርጎ በዝርዝር ይጽፋል። እኛ በእግዚአብሔር ላይ ያመጽን ኃጢአተኞች ሆነን ሳለን፥ እግዚአብሔር ጻድቃን አድርጎ እኛን በመቀበል ከእርሱ ጋር ሰላም እንዲኖረን ሲያደርግ፥ ይህን ተግባሩን ከፍጻሜ በማድረስ የዘላለምን ሕይወት እንደሚሰጠን እርግጠኛች ነን። በእነዚህ ሦስት ጥቅሶች ውስጥ፥ ሐዋርያው ጳውሎስ በሁለት ሐረጎች ተጠቅሞ ክርስቶስ ስለሞተላቸው ሰዎች ገልጾአል። በቁጥር 8 ውስጥ ኃጢአተኞች ነበርን ይላል። እንዲህ ሲል እኛ ሕጉን ስላፈረስን ከመንገዱ ወጥተን የትም ስንቅበዘበዝ ነበርን ማለት ነው። ለእግዚአብሔር ባለመታዘዛችን ምክንያት፥ ከእርሱ የምንጠብቀው ምንም መልካም ተግባር እልነበረም። በቁጥር 10፣ ሐዋርያው የእግዚአብሔር ጠላቶች እንደ ነበርን ይናገራል። እንዲህ ማለት በእግዚአብሔር ላይ በግልጽ በማመፃችን፥ በእግዚአብሔርና በእኛ መካከል ጦርነት ነበር ማለት ነው። ያም ሆኖ፣ እኛ ደካሞች፥ ሕግ አፍራሾችና ጠላቶቹ ሳለን፥ ክርስቶስ ለእኛ ምን አደረገልን? ለእኛ ሲል ሞተ! ስለዚህ ድርጊት ጳውሎስ ሲጽፍ በመገረም ነው። ምክንያቱም አንድ ሰው ለሌላው ሕይወቱን አሳልፎ በመስጠት የመሞት ድርጊት ያልተለመደና ብርቅ ስለሆነ ነው። ለጠላቱ ሲልሶ የሚሞት ማን ነው? ለበደለውስ ራሱን አሳልፎ ለሞት የሚሰጥ እረ ማን ነው! ነገር ግን እግዚአብሔር በእርሱ ለሚያምኑት ያደረገው ይህን ነው።  በቁጥር 9 እና 10 ውስጥ ጳውሎስ ነገሩን ሲያጠቃልል፥ «እግዚአብሔር ጠላቶቹ ለነበሩ ለኃጢአተኞች ያደረገውን ተመልከቱ» ይላል። ኢየሱስ ሞቶአል፥ የእርሱም ደም የኃጢአትን ቅጣት ከፍሎአል። እግዚአብሔርም በፊቱ ጻድቃን አድርጎ ተቀብሎአቸዋል። እንደዚሁም ከእነርሱ ጋር ሰላምን መሥርቷል። በዚህም ወዳጆቹ አድርጓቸዋል። ኢየሱስ አሁን ይህን ግንኙነት ጠብቆ ለዘላለም ይኖራል። እንግዲህ እግዚአብሔር ይህን ሁሉ ካደረገ፥ እነዚህ ኃጥአን የነበሩ ሁሉ፥ በፍርድ ቀን የእግዚአብሔር ቁጣ አይወርድባቸውም። ክርስቶስ በመጨረሻው ጊዜ ፍጹም የሆነ ደኅንነትንና የዘላለም ሕይወትን እንደሚሰጣቸው እርግጠኞች ነን። አንድ ክርስቲያን ደራሲ እነዚህን ጥቅሶች በሚከተለው ሁኔታ አጠቃሎአቸዋል፡ «እግዚአብሔር አስቸጋሪ የነበረውን ነገር አስቀድሞ ያደረገ ከሆነ፥ ማለትም የመጨረሻ ኃጢአተኞችን የሚያጸድቅ ከሆነ፥ አስቀድሞ በፊቱ ጻድቃን አድርጎ የተቀበላቸውን ከቁጣው እንደሚያድናቸውና እንደሚያጸድቃቸው ያላንዳች ጥርጥር ልናረጋግጥ እንችላለን።»  አንድ የተከሰሰ ሰው ፍርድ ቤት ውስጥ እንደ ቆመ ገምቱ። ከዚያም ዳኛው ይህን ችሎቱ ፊት ቆሞ ያለውን ሰው ከተከሰሰበት ወንጀል ነፃ መሆኑን በይፋ ያሳውቃል። እዚያው ችሎቱ ውስጥ የነበሩ ዘመድ ወዳጆቹ ይህን ሊሰሙ ብድግ ብለው ያቅፉትና ደስታቸውን ይገልጹለታል። ከዚያም ዛኛው ሰውዬውን አሁን ነፃ ስለሆንክ ልትሄድ ትችላለህ ይለዋል። ሰውዬውና ዘመድ ወዳጆቹ አብረውት ከፍርድ ቤቱ ወጥተው ይሄዳሉ። ነገር ግን በፍርድ ቤቱ በር ላይ ዘብ ቆሞአል። ታዲያ ይህ ነፃ የወጣው ሰው ዘቡን አልፎ መውጣት ይፈራልን? ዘቡ አቁሞ ይዞ ወደ እሥር ቤት እንደሚመልሰው ሰግቶ ይፈራ ይሆን? በፍጹም አይፈራም! ቀደም ሲል ዳኛው በደል እንደሌለበት የገለጸ ስለሆነ ምንም ጥርጥር አያድርበትም። ደግሞም ነፃ ስለሆነ በልበ ሙሉነት በበሩ ወጥቶ ወደፈለገው ሊሄድ ይችላል።  ለእኛ በክርስቶስ ላመንነው ዳኛው ከማንኛውም በደል ነፃ መሆናችንን አስታውቋል። ይህ መግለግ በመጨረሻ ከተሰጠ በኋላ ከፍርድ ቤቱ ወጥተን ለመሄድ የሚያሠጋን ምንም ምክንያት አይኖርም፡ ሞትንም ሆነ ወይም የመጨረሻውን በእግዚአብሔር የሚሰጥ ፍርድ መፍራት አያስፈልገንም። ጽድቅ ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም እንዲኖረን ያደርጋል። እግዚአብሔር በመጨረሻው ጊዜ ለሚሰጠን የዘላለም ሕይወት የማረጋገጥ ዋስትና ይሆናል። ስለዚህ ደኅንነታችን የታመንና የተረጋገጠ ነው። 2. እግዚአብሔር ሁልጊዜ የጀመረውን ሥራ ስለሚፈጽም የአማኞች ሁኔታ ለዘላለም የተረጋገጠ ነው።  ጥያቄ፡- ሮሜ 8፡30 አንብብ፡ እግዚአብሔር አስቀድሞ ለመረጣቸው፥ ለጠራቸውና ላጸደቃቸው ምን ተዘጋጅቶላቸዋል? ጥያቄ፡- ፊልጵ. 1፡6 አንብብ። ጳውሎለ እርጠኛ የሆነው ስለ ምንድን ነው?  በሮሜ 8 ውስጥ ጳውሎስ በሮሜ 5 ውስጥ የጀመረውን አሳብ ይቀጥላል። እግዚአብሔር ቀደም አድርጎ ከበደል ወይም ከወንጀል ነፃ መሆናችንን አሳውቆልናል፡ እግዚአብሔር የሚጀምረውን ሥራ ሁልጊዜ ከፍጻሜ ያደርሳል። በትምህርት 15 ላይ እንደ ተመለከትነው፥ የእግዚአብሔር የማዳን ተግባር የተጀመረው በራሱ ምርግና ጥሪ ነው። ትናንትናም በርማ 8፡30 ውስጥ እንደ ተከታተልነው፥ ጳውሎስ ሲናገር፥ አስቀድሞ የወሰናቸውን ጠራቸው፥ የጠራቸውንም አጸደቃቸው ብሏል። ስለዚህ ከእግዚአብሔር ጋር እርቅን ያገኙ ሁሉ ክብርን አግኝተዋል። በእግዚአብሔር ዓይን፥ ዘላለማዊው የደኅንነታቸው ክብርም አሁኑኑ ተረጋግጧል! በእርግጥ ዳግም የተወለዱ ክርስቲያኖች ወደፊት እንድን ይሆንን ብለው ሊሠጉ አይገባም። እግዚአብሔር እንደሚለው፥ በጽድቅ አማካይነት በደላቸውን ሁሉ ይቅር ካላቸው፥ አስቀድሞ በሰማይ ክብርን አዘጋጅቶላቸዋል። እንደ እግዚአብሔር አደራረግ፥ ሥራውን ለጀመረላቸው ሁሉ የደኅንነት ተግባርን አስቀድሞ ጨርሶላቸዋል። ከእርሱ ጋር የታረቁ መሆናቸውን ካሳወቀ፥ ዘላለማዊው ደኅንነታቸው ልክ አስቀድመው ዘላለማዊ ክብርን እንዳገኙ ያክል የተረጋገጠላቸው እውነታ ነው።  በእውነት ዳግም በተወለዱ ሰዎች ሕይወት ውስጥ እግዚአብሔር የጀመረውን ሥራ እንደሚፈጽም የሚያስተምረን ሌላው ጥቅስ ፊልጵ. 1፡6  ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ የፊልጵስዩስን ክርስቲያኖች ሲያበረታታቸው በሕይወታቸው ውስጥ የደኅንነት ሥራ የጀመረው አምላክ «እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን» የሚቀጥል መሆኑን ያረጋግጥላቸዋል። የኢየሱስ ክርስቶስ ቀን የሚባለው ክርስቶስ ወደ ምድር የሚመለስበት ቀን ነው። እንደዚሁም ሐዋርያው ጳውሎስ ሲናገር እግዚአብሔር አንድ ጊዜ የደኅንነት ተግባሩን በአንድ ሰው ሕይወት ውስጥ መሥራት ሊጀምር፥ እስከ ዘላለም ዓለም መጀመሪያ ድረስ ዘልቆ ይፈጽማል ይላል። ስለዚህ ክርስቶስን እንደ አዳኝ ተቀብለው ወደ እርሱ ዘንድ የሚመጡ ዘላለማዊ ደኅንነታቸው ተረጋግጦላቸዋል።  3. አማኞች ለዘላለም ደኅንነታቸው ተረጋግጦላቸዋል፥ ምክንያቱም የእግዚአብሔርን

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫ እና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 1  Read More »

የደኅንነት በረከቶች – እንከብራለን ሲባል ምን ማለት ነው?  

This entry is part 87 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ሰዎች ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ አዳኛቸው አምነው በሚቀበሉበት ጊዜ፥ እግዚአብሔር አስደናቂና የተትረፈረፉ የደኅነት በረከቶችን በላያቸው ላይ ያፈስሳል። በዚህም አዲስ ሕይወትን ይሰጣቸዋል፥ ከክርስቶስ ጋር ኅብረት እንዲኖራቸው በማድረግ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር ይላቸዋል፣ ከዚያም ከእርሱ ጋር መታረቃቸውን በማሳወቅ፥ የቤተሰቡ አካል ያደርጋቸውና በፊቱ ቅዱሳን ሆነው እንዲገኙ በሕይወታቸው ውስጥ ይሠራል። ሆኖም፣ እያንዳንዱን አማኝ ወደፊት የሚጠብቀው በረከት አለ፣ ይህም የክብር በረከት ነው። ስለሆነም ከዚህ ሕይወት ፍጻሜ በኋላ፥ አማኞች ሁሉ ዘላለማዊ የሆነ የክብር ሕይወት እንደሚያገኙ የተረጋገጠላቸው እውነታ ነው። ከዚህ በመነሣት በዚህ ሳምንት ስለሚመጣው የክብር በረከትና አማኞች ይህን የክብር በረከት የሚያገኙ ስለመሆናቸው ስላለው ዋስትና አብረን እናጠናለን።  መጀመሪያ ቀን – ክብር  በዚህ ዓለም ውስጥ ያሉትን በሽታዎችና የተለያዩ ሥቃዮችን በመመልከት፥ «ይህ ዓለም የከፋ ስፍራ ነው» ብላችሁ ያሰባችሁበት ጊዜ ይኖር ይሆን? «እርግጥ በዚህ ዓለም ውስጥ ብዙ የተዛነፉ ሁኔታዎች ሲከሰቱ እንመለከታለን። ልንገራችሁና የራሴም ሕይወት ቢሆን ችግር አለበት። ስለዚህ አካሌ በሕመም ምክንያት ኃይለኛ ስሜት የሚያመጣብኝ ጊዜ አለ። ላደርንው የማልፈልገውን ነገር ሳደርግ እገኛለሁ። የከፉ የኃጢአት ድርጊቶችንም እፈጽማለሁ። በዚህ ዓለም ላይ የእኔም ሕይወት ሆነ የዓለም ሁኔታ በትክክለኛው መንገድ እንደ ተመራ ቢኖር በጣም ደስ ባለኝ ነበር!» ሕይወታችንንም ሆነ፥ ይህን ዓለም በሚመለከት ብዙ የተበላሹ ነገሮች አሉ። የእግዚአብሔር የማዳን በረከቶች ግን እኛን ከእርሱ ጋር ለማስታረቅ በሂደት ላይ ናቸው። እግዚአብሔር በበረከቱ ሕይወትን ይሰጠናል፥ ከዚያም ከእርሱ ጋር መታረቃችንን በይፋ ይገልጥልናል። ቀጥሎም የቤተሰቡ አካል ያደርገናል፥ እንዲሁም በቅድስና ጎዳና ላይ ይመራናል። ይህም ሆኖ፥ ሥቃይና ክፋት በሰፈነበት ዓለም ውስጥ እንኖራለን። ሰውነታችንም በኃጢአት የተሞላ ርኩሰት ያሸነፈው በመሆኑ፥ ብዙ ጊዜ ከሥቃይ የራቀ አይደለም። ይህን እንጂ ክርስቲያኖች ሁሉ፥ ከዚህ ሕይወት በኋላ በሚመጣው ሕይወት፥ የክብር በረከቶችን እንደሚቀበሉ የተረጋገጠላቸው እውነታ ነው። መክበር የሚባለው፥ በመጨረሻው ጊዜ በሕይወታችንና በአካላችን ላይ ያለውን የኃጢአት መርገም የሚያስወግድልን የደኅንነት በረከት ነው። እንዲሁም መክበር፥ ሕይወታችንና አካላችንን እግዚአብሔር ወዳዘጋጀው የፍጹምነት ደረጃ የሚያደርስ የደኅንነት በረከት ነው።  1. እንከብራለን ሲባል ምን ማለት ነው?  1.1 መክብር (ክብር) ማለት ፍጹማንና ንጹሐን እንሆናለን ማለት ነው፡፡  ጥያቄ፡- 1ኛ ቆሮ. 1፡8 አንብብ። እግዚአብሔር ለአማኞች ምን ተስፋን ይሰጣል?  ጥያቄ፡– ኤፌ 5፡25-27 አንብብ፡ ቤተ ክርስቲያን በእግዚአብሔር ፊት እንዴት ሆና ትቀርባለች?  ጥያቄ፡- ቆላ. 1፡22 እንብብ። እግዚአብሔር እኛን ከራሱ ጋር የማስታረቁ ውጤት ምንድን ነው?  ጥያቄ፡- ይሁዳ 24 አንብብ። እግዚአብሔር ምን ያደርግልናል?  ጥያቄ፡- 1ኛ ተሰ. 5:23-24 አንብብ። እግዚአብሔር ታማኝ የሆነው ምን ሊያደርግልን ነው?  በምንከብርበት ጊዜ በመጀመሪያ የምንቀበለው በረከት፥ ያለነውር፥ ፍጹምና ንጹሕ መሆንን ነው። 1ኛ ቆሮ. 1፡8 ላይ እግዚአብሔር እስከ መጨረሻው ቀን ጠብቆ፥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስክመለስበት ቀን ያላነቀፋ ሆነን እንድንገኝ ያደርገናል ይላል። ይህ የጌታችን የኢየሱስ ቀን የተባለው እርሱ ተመልሶ የሚመጣበት ቀን ነው፡ በዚህ ምድር ላይም ክርስቶስን አምነው እንደ አዳኛቸው ተቀብለው ያሉትን ክርስቲያኖች እግዚአብሔር በሰጣቸው ተስፋ መሠረት ኢየሱስ እስኪመለስ ድረስ በእምነታቸው የጸኑና የጠከሩ፥ ከነውርም ሁሉ የጸዱ አድርጎ ይጠብቃቸዋል። ከኃጢአት ሁሉም የነጹ ይሆናሉ። በኤፌ. 5፡25-27 ውስጥ ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ክርስቶስ ፊት የመቅረብዋን ሁኔታ፥ በሠርጋቸው ቀን ሙሽሪት ወደ ሙሽራው በምትቀርብበት አኳኋን መስሎ ጽፎታል። እንደሚታወቀው ሁሉ ሙሽሮች በሠርጋቸው ቀን ቆንጆ ልብስ ይለብሳሉ፥ ባማረ ሁኔታም ያጌጣሉ። በዚህን ዕለት ሙሽሪት በሁለመናዋ ያማረችና የደቀች ሆና በሙሽራው ዓይን ትታያለች። ታዲያ ቤተ ክርስቲያን፥ በጌታ ኢየሱስ ፊት በምትቀርብበት ጊዜ፥ ፍጹም ለመሆን በመጣር ብቻ አትቀርብም፥ ነገር ግን እጅግ በጣም ፍጹምና እንከን የለሽ ሆና ትቀርባለች። ማለትም ያላንዳች ኃጢአት፥ እንከንና ነውር ሆና ፊቱ ትቀርባለች። እናም ፍጹም የሆነ ቅድስናን ትጎናጸፋለች። በቆላ 1፡22 ላይም፥ እግዚአብሔር ከራሱ ጋር ስለ አስታረቀን፥ ቅዱሳንና ንጹሐን፥ ነቀፋም የሌለብን አድርጎ በፊቱ አቆሙን ይላል። በምንከብርበት ወይም ክብርን በምንጎናጸፍበት ጊዜ፥ ከኃጢአት ፈጽመን ለምን ጊዜውም እንነጻለን። ከዚህ በኋላ ማንም ሰው ቢሆን በኃጢአት ወይም በስሕተት አሳብቦ ሊከስሰን አይችልም። በይሁዳ 24 ላይ እግዚአብሔር በደኅንነቱ ውስጥ እንደሚጠብቀንና በፊቱም ያላንዳች ነውር እንደምንም ተስፋ ይሰጠናል። በ1ኛ ተሰ. 5፡23-24 እዚአብሐር ያላንዳች ነውር ጠብቆ ክርስተስ ተመልሶ እስከሚመጣ ድረስ እንደሚያቆየን ያረጋግጥልናል።  ጥያቄ፦ በቅርቡ ኃጢአት የሠራችሁበትን ጊዜ አለቡ። ስለዚህ ኃጢአት ለእግዚአብሔር ከተናዘዛችሁ በኋላ እንኳን ምን ተሰማችሁ?  አንዳንድ ጊዜ ሰይጣን ወደ እኛ ዘንድ ይመጣና ስለ ሠራናቸው ብዙ ኃጢአቶች ያስታውሰናል። ይህን በመሰለ ሁኔታ ወደ እኛ ይጠጋና በደላችንን እያጎላ፥ ፈጽሞ ስእግዚአብሔር ፊት መቆም የማይገባን ኃጢአተኞች መሆናችንን እየነገረ ያስፈራራናል። ኃጢአታችንን በእግዚአብሔር ፊት የተናዘዝን ሆነን ሳለን እንኳን ቢሆን፥ ወደ እኛ ቀርቦ የኃጢአታችን ሸክም የከበደ መሆኑን እየወተወተ ማስፈራራቱን ይቀጥልበታል። ሰይጣን ይህን ያድርብን እንጂ እግዚአብሔር እንደሚሰጠን ተስፋ ከሆነ፥ ጌታ ኢየሱስ በመስቀል ላይ በከፈለው መሥዋዕትነት ኃጢአታችንን ይቅር በማለቱ፥ ከዚህ ሕይወት በኋላ የሥነ ተፈጥሮ ኃጢአት ጨርሶ ሊኖር እንደማይችልና፥ ከዚህም በስተቀር ኃጢአት የሚኖርበት ሥራ እንደማይሠራ ያረጋግጥልናል። በሁለመናችንም ፍጹማን ስለምንሆን፥ ሰይጣን ከዚያ ወዲያ እኛን የሚከስስበት ምክንያት ጨርሶ አይኖረውም። ክብርን በምንጎናጽፍበት ጊዜ፥ ካኃጢአት፥ ከበደልና ከክስ ነፃ እንሆናለን።  1.2 መክበር (ክብርን መጎናጸፍ) ማለት የአካላችን ወደ ፍጹምነት መታደስ ማለት ነው።  ጥያቄ፡- 1ኛ ቆሮ. 15፡20፥ 42-44፥ 49-57 ቀን አንብብ። ሀ) ሐዋርያው ጳውሎስ እካላችን አሁን ምን ይመስላል አለ? ሐዋርያው ወደፊትስ አካላችን ምን ይመስላል አለ?  ያቄ፦ 2ኛ ቆሮ 5፡1 አንብብ። ሀ) ሐዋርያው ጳውሎስ ያሁኑን አካላችንን ከምን ጋር ያመሳስለዋል? ለ) ደግሞስ በሞታችን ጊዜ የምንለብሰውን አካል ከምን ጋር ያመሳስለዋል?  ጥያቄ፡- ፊልጵ. 3፡21 አንብብ። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም በሚመጣበት ጊዜ፥ ይህን የተዋረደውን ሰውነታችንን ወደ ምን ይለወጣል?  ይህ የለበስነው አካላችን ወደፊት በሚመጣው የክብር አካል እንደሚተካው ከሚያስተምሩት እጅግ ግልጽ ከሆኑት ክፍሎች አንዱ የኛ ቆሮ. ምዕራፍ 15 ነው። በ10ኛው ትምህርት ላይ እንደተከታተልነው፣ የክርስቶስ ትንሣኤ እርሱን እንደ አዳኛቸው አምነው ለተቀበሉት ሁሉ የመጀመሪያው ፍሬ ወይም በኵር ነው። የእርሱ ትንሣኤ የእኛን መጪውን ትንሣኤ ያረጋግጥልናል። እንዲሁም የክርስቶስ የተነሣው አካል፥ ለመጪው ለሚነሣው አካላችን ምሳሌ ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ እንደሚናገረው፥ በምንሞትበት ጊዜ የሚቀበረው አካላችን ጠፊ፥ ደካማ፥ ተፈጥሮአዊና ክብር የለሽ ነው። ነገር ን ከሙታን በምንነሣበት ጊዜ፥ የማይጠፋና ሕያው፥ ክብርን የተጎናጸፈ፥ ኃይልና መንፈሳዊነትን የተሞላ አካል ይኖረናል። ጌታ ኢየሱስ ከሙታን በተነሣ ጊዜ እንደ ነበረው ያለ የተሟላ የሰው አካል ይኖረናል። ያሁኑ አካላችን , ከአፈር የተሠራውን የአጻምን አካል የሚመስል ነው፡ ነገር ን አካላችን ክብርን ሲለብስ ወይም ሲከብር፥ ከሰማይ የመጣውን የኢየሱስን አካል ይመስላል። ሐዋርያው ጳውሎስ “የማይጠፋ፥ ሕያው’ ብሎ ሊላ፥ በፍጹም የማይሞት አካል ይኖረናል ማለቱ ነው። የሰዎች የመጨረሻው ጠላት የሆነው ሞት ፈጽሞ ድል ይሆናል። የደኅንነት የክብር በረከት፥ የማይታመም፥ የማይደክምና የማይሞት አካልን ይሰጠናል። ጳውሎስ በፊልጵ. 3፡21 ውስጥ፥ እርሱ ይህን የተዋረደውን ሰውነታችንን በመለወጥ የእርሱን ክብሩ ሰውነት እንዲመስል ያደርገዋል” ይላል።  በ2ኛ ቆሮ. 5፡1 ውስጥ ጳውሎስ ይህን ሥጋችንን በድንኳን፥ ክብርን የሚጎናጸፈውን አካላችንን ደግሞ በእግዚአብሔር በታነጻ ዘላለማዊ መኖሪያ ይመስለዋል። ይህ ያለንበት አካላችን ጊዜያዊ ቤታችን ነው። ከዚህም የተኑግ ነው የሚያረጀው፥ የሚደከመውና ለሥቃይም በቀላሉ የሚጋለጠው ነገር ተን ይህ ሕይወት ካለፈ በኋላ፥ ከምንኖርበት፡ የተደረተ ጊዘያዊ ድንኳን ወደ አማረና ለዘላለም ወደማያረጀው ቤታችን እንዛወራለን። እዚህ ላይ ጳውሎስ፥ ይህ አካላችን ከፈረሰ በኋላ፥ ነዋሪ ወደ ሆነው ዘላለማዊ ቤታችን እንገባለን ብሎ የተናገረውን ሰጥሞና አስቡ። አማኞች የሆኑ ሁሉ ከዚህ ዓለም በሞት በሚያልፉበት ጊዜ፥ ወዲያውኑ የክብር በረከት የተሞላበትን አካል ይለብሳሉ። የተለምዶ ስለሆነ፥ ቤተሰቦቻችን ወይም ወዳጆቻችን በሞት በሚለዩን ጊዜ እናዝናለን ነገር ቀን በሞት ምክንያት ከምንወዳቸው ሰዎች የመለየት ሁኔታ እንዲሁ የተለምዶ ነው ማለት አንችልም። ሞት የኀዘን ወቅት ቢሆንም በተለይ በጌታ ኢየሱስ የሚያምኑ ሰዎች በሚሞቱበት ጊዘ የኀዘናቸው ጊዜ ሆኖ ሊወሰድ አይገባም። ምክንያቱም በክርስቶስ ለሚያምኑት በሚሞቱበት ጊዘ ወቅቱ አርጌና ጊዜያዊ ከሆነው የመኖሪያ ድንኳናቸው ወደ አማረውና ዘላለማዊ

የደኅንነት በረከቶች – እንከብራለን ሲባል ምን ማለት ነው?   Read More »

ቅድስና 

This entry is part 86 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ በደኅንነታችን ውስጥ ስለምናገኛቸው በረከተች ስናጠና ነበርን። በዳንንበት ጊዜ ስላገኘናቸው ብዙ የደኅንነት በረከቶች አጥንተናል። ዳግም በዳንንበት ወቅት፣ እግዚአብሔር በዳግም ልደት አዲስ ሕይወትን ሰጥቶናል። በደኅንነታችን ወቅት በውስጣችን ሊኖር ካመጣው ከክርስቶስ ጋር ኅብረት በምናደርግበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር እኛን ከክርስቶስ ጋር አንድ አድርጎ ያየናል። እግዚአብሔር ኃጢአታችንን ይቅር በማለት ደኅንነትን ባገኘንበት ወቅት፣ ወዲያው መጽደቃችንን አስታውቆልናል። እንደ ልጆቹ አድርጎ በመቀበል ደኅንነትን በሰጠን ወቅት፣ አስደናቂ የሆነ ውርስ እንደሚጠብቀን ተስፋ ሰጠን። እንግዲህ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን አምነን እንደ መድኃኒታችን በተቀበልን ጊዜ እግዚአብሔር እነዚህን ሁሉ በረከቶች ሰጠን።  ዛሬ ደግሞ በደኅንነታችን ወቅት ስለሚሰጠን ስለ አንድ ሌላ በረከት እንማራለን። ይህ በረከትም ቅድስና ነው። እግዚአብሔር በሚያድነን ጊዜ፣ ቅዱስ ሕዝቡ አድርጎ ይለየናል። ሆኖም ይህ የቅድስና ሂደት ሦስት የተለያዩ ደረጃ ዎች አሉት። በአንድ መልኩ ሲታይ፥ በክርስቶስ የሚያምኑ ሁሉ በደኅንነታቸው ወቅት ቅዱሳን ይሆናሉ። በሌላ መልኩ ሲታይ፥ በክርስቶስ የሚያምኑ ሁሉ አሁንም ቅዱሳን በመሆን ሂደት ላይ ናቸው። በሦስተኛ ደረጃ ሲታሰብ ደግሞ በክርስቶስ የሚያምኑ ሁሉ ወደ መንግሥተ ሰማይ ከመድረሳቸው በፊት ቅዱሳን አይሆኑም፤ በዚያ ስፍራ ግን ፍጹም ቅዱሳን ይሆናሉ። ነገር ገን በዛሬው ክፍለ ጊዜአችን ስለ ሦስቱ የቅድስና በረከት ደረጃ ዎች እናጠናለን።  1. እውነተኛ የሆኑ አማኞች ሁሉ በአቋም ደረጃ መጀመሪያ በዳኑበት ጊዜ ተቀድሰዋል።  ጥያቄ፡- ክርስቲያን ከመሆናችሁ በፊት ስለፈጸማችኋቸው ኃጢአቶች አስቡ። ከእነዚህ ኃጢአቶች የተነሣ አሁንም ርኩሰት ይሰማችኋል? ይህ ከሆነ በማስታወሻ ደብተሮቻችሁ ውስጥ በክርስቶስ ከማመናችሁ በፊት የፈጸማችኋቸውንና አሁንም ድረስ በደለኞች እያደረጉዋችሁ ያሉትን ኃጢአቶች ጻፉዋቸው።  ክርስቶስን አምነን እንደ ግል መድኃኒታችን ከመቀበላችን በፊት የፈጸምናቸውና አሁን ስናስባቸው የሚያሳፍሩን ኃጢአቶች ሁላችንም : ይኖሩናል። አንዳንድ ጊዜ ስለ እነዚህ ኃጢአቶች እናስብና በእግዚአብሔር , ፊት ራሳችንን አጉድለንና አቆሽሸን እናቀርባለን። ከእነዚህ ኃጢአቶች የተነሣ ወደ እግዚአብሔር ፊት ጨርሶ መቅረብ እንደሌለብንና ለዚህም የተገባን አለመሆናችን ይሰማናል። ግን እግዚአብሔር በዳንበት ጊዜ አስደናቂ የሆነ በረከትን ሰጥቶናል። እግዚአብሔር ከእነዚያ ኃጢአቶች ሁሉ አንጽተ በፊቱ ቅዱሳን አድርጎናል። እግዚአብሔር የተለየን ንጹሐን ሕዝብ አድርጎ ተቀብሎናል። በጌታ ኢየሱስ በምናምንበትና መድኃኒታችን አድርገን በምንቀበለው ጊዜ እግዚአብሔር በአዘጋጀልን ቅዱስ ስፍራ ያስቀምጠናል።  ጥያቄ፡- ሮሜ 1፡7፤ 1ኛ ቆሮ. 1፡2፤ ቆላ. 1:2፤ ኤፌ. 1፡1 እና ፊልጵ. 1፡1 አንብብ። ጳውሎስ በእነዚህ በእያንዳንዶቹ ጥቅሶች ውስጥ አማኞችን ምን ብሎ ይጠራቸዋል?  ጥያቄ፡- 1ኛ ቆሮ. 1፡30 አንብብ። ክርስቶስ ስለ እኛ ብሎ ምን ሆነ?  ጥያቄ፡- ዕብ 10፡10 አንብብ። የኢየሱስ መሥዋዕትነት ምን ጠቀመን?  ጥያቄ፡- 1ኛ ቆሮ. 6፡11 አንብብ። በቆሮንቶስ ስለነበሩ አማኞች እውነት የነበረው ነገር ምን ነበር?  በአዲስ ኪዳን ውስጥ በሚገኙ በርካታ ክፍሎች እንደተገለጸው በክርስቶስ የሚያምኑ ሰዎች “ቅዱሳን” ወይም “ቅዱሳን የሆኑ ሰዎች” በመባል ይታወቃሉ። ቅዱሳን የሚባሉት ሰዎች በጾምና በጸሎት ራሳቸውን ለእግዚአብሔር የለዩ ወይም በተለየ ኃጢአት ላይ አሸናፊዎች የሆኑ ልዩ ሰዎች ብቻም አይደሉም። በክርስቶስ የሚያምኑ አማኞች ሁሉ ቅዱሳን ተብለው ይጠራሉ። ጳውሎስ መልእክቶቹን ወደ ሮሜ ሰዎች (1፡7)፥ ወደ ቆላስይስ ሰዎች (1፡2)። ወደ ኤፌሶን ሰዎች (1፡1)፥ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች (1፡1) እና ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፡2) በጻፈበት የመጀመሪያ መልእክቱም በእነዚህ ከተሞች በእያንዳንዳቸው ውስጥ የሚገኙ ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳን ብሎ ጠርቶአቸዋል። በትክክል በክርስቶስ ያመንና እንደ ግል አዳኙ የተቀበለውና ዳግም የተወለደ ምእመን ሁሉ ቅዱስ ተብሎ ይጠራል። ቅዱሳን ተብለው ስለ ተጠሩ ዳግም ምንም ዓይነት ኃጢአት አይሠሩም ማለት አይደለም። እንዲህ ማለት፣ ከክርስቶስ ጋር ኅብረት ስላለን፥ እግዚአብሔር ወደ እኛ በሚመለከትበት ጊዜ የኢየሱስን ቅድስናና ጽድቅ ስለሚያሳይ ሁላችንም በእግዚአብሔር ፊት ቅዱስ የሆነ ስፍራ ይኖረናል።  «ቅዱስ» የሚለው ቃል «ተለይቶ የተቀመጠ» ማለት ነው። እግዚአብሔር ቅዱስ ነው በምንልበት ጊዜ ካኃጢአትና ተራ ከሆኑ ነገሮች የተለየ ነው ማለታችን ነው። ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛችን በምንቀበለው ጊዜ እግዚአብሔር ለእርሱ የተለየን አድርጎ ያስቀምጠንና፤ ከኃጢአትና ከኃጢአት ጋር ከተያያዙ ነገሮች የተለየን የእርሱ ንብረት አድርጎ ያኖረናል። ይህንን የመሰለውን ስፍራ ነ ከእግዚአብሔር የምናገኘው በመልካም ሥራችን አይደለም። በ17ኛው ትምህርታችን ውስጥ እንዳየነው፥ ደኅንነታችን ሊመጣ የቻለው ከክርስቶስ ጋር ባለን ኅብረት ነው። እግዚአብሔር ወደ እኛ በሚመለከትበት ጊዜ፣ የኢየሱስን ጽድቅና ቅድስና ያያል። 1ኛ ቆሮ. 1፡30 ኢየሱስ ቅድስናችን ሆነ ይላል። ከኃጢአት ተለይተን የተቀመጥነውና በእግዚአብሔር ፊት ቅዱሳን የሆንነው የኢየሱስ ቅድስና የእኛ ቅድስና ዕለሆነ ነው።  በተጨማሪም፣ ይህ ከኃጢአት ተለይቶ የመቀመጥ ወይም የመገኘት አዲስ ስፍራ ወይም አቋምና ለእግዚአብሔርም የተለዩ የመሆን ሂደት ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም ይቀጥላል። ዕብ 10፡10 ላይ የክርስቶስ መሥዋዕትነት በክርስቶስ እውነተኛ አማኞች የሆኑትን ሁሉ «ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዘ» ቀድሶአቸዋል ይላል። ክርስቶስን እንደ መድኃኒታችን አድርገን በምናምንበት ጊዜ፣ የክርስቶስ የመሥዋዕትነት ደም በእግዚአብሔር ፊት ቀድሶ ለእግዚአብሔር ተለይተን የተቀመጥን ያደርገናል። ይህ ቅዱስ ስፍራ ቋሚ ነው። «ለአንዴና ለመጨረሻ» የሚሆን ነው። ላለፈውም ለወደፊቱ ኃጢአት ይቅርታን አግኝተናል። እግዚአብሔርም በማንኛውም ጊዜ የሚመለከተን ንጹሐንና ቅዱሳን አድርጎ ነው።  አማኞች ኃጢአት በሚሠሩበት ጊዜ የነበራቸውን የቅድስና ስፍራ እንደ ያዙ ይቆያሉ? 1ኛ ቆሮ. 6፡11 እንደ ያዙ እንደሚቆዩ በግልጽ ይናገራል። ሐዋርያው ጳውሎስ ከመሠረታቸው አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን የባለች ኃጢአተኛ ነበረች። በምእመናኑ መካከል ጭቅጭቅና መከፋፈል (1ኛ ቆሮ. 1፡11-12)፣ ዝሙት (1ኛ ቆሮ. 5፡1)፣ እርስ በርስ መካሰስ (1ኛ ቆሮ. 6፡7)። በጌታ እራት ላይ ያላግባብ መብላትና ጠጥቶ መስከርና (1ኛ ቆሮ. 11፡21)፥ በመንፈሳዊ ስጦታ አላግባብ መጠቀም ሁሉ (1ኛ ቆሮ. 14፡26-40) ነበረባቸው። ነገር ግን ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮንቶስ 6፡11 ሲናገር፣ በቆሮንቶስ ያሉ አማኛች ሁሉ ተቀድሰዋል ደግሞም ጸድቀዋል ብሏል። በመጽደቅ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ተብለዋል። በእግዚአብሔር ዘንድ በያዙት ስፍራ አሁንም በመጽደቅ ከኃጢአት ተለይተው ተቀምጠዋል። የኃጢአት ተግባራቸው በእግዚአብሔር ዘንድ ከነበራቸው ቅዱስ ስፍራ አላስወገዳቸውም። በምትኩ፣ ጳውሎስ ኃጢአትን እንዳይሠሩ ምክንያት የሚሆናቸው በእግዚአብሔር ፊት ያላቸው ቅዱስ ስፍራ መሆኑን ነግሯቸዋል። አማኞች ሁሉ በመጀመሪያ በጌታ ኢየሱስ ባመኑ ጊዜ በእግዚአብሔር ፊት ቅዱሱን ስፍራ እንዲይዙ ተደርገዋል።  አንዳንድ ጊዜ ሰይጣን ወደ እኛ ዘንድ ይመጣና ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን አምነን እንደ መድኃኒታችን አድርገን ከመቀበላችን በፊት ስለሠራነው ኃጢአት ይከስሰናል። በዚህ አጋጣሚ እኛ በዚህ ኃጢአት የረከስንና ንጽሕና የሌለን መሆናችንን እየነገረን፣ ያገኘነውም ደኅንነት ለእኛ የማይገባ መሆኑን በመወትወት ለማዳከም ይጥራል። እንደዚሁም ሰይጣን ባለፉት ጊዜያት ከፈልምናቸው የኃጢአት በደሎች የተነሣ ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ቀርበን በስግደት ልናከብረውና በጸሎት ልንማጠነው እንደማንችል ይነግረናል። ነገር ገን እግዚአብሔር አባታችን በክርስቶስ መሥዋዕትነት ካለፉት ኃጢአቶች የነጻን መሆናችንን ያረጋግጥልናል። ለዚህ ማረጋገጫም በፊቱ ቅዱስ የሆነ ስፍራ ሰጥተናል። ይህ ብቻም አይደለም። ለእርሱ ለይቶ አስቀምጦናል። የመዳናችን አንዱና ታላቁ በረከት እግዚአብሔር በፊቱ የተቀደሰ ስፍራ ስለ ሰጠንና ለራሱ ወስኖ ስላስቀመጠን፣ እኛ በፈለግነው ጊዜ ወደ እርሱ ዘንድ ቀርበን ልናመልከውና ልንጸልይ መቻላችን ነው። በዚህ አኳኋን እግዚአብሔር በፊቱ በሰጠን የቅድስና ስፍራና አክብሮት ወደ እርሱ ዘንድ ቀርበን እንድናመልከው ብርታትን እናገኛለን።  2. እውነተኛ አማኞች ሁሉ በክርስትና ሕይወታቸው ውስጥ በየጊዜው በበለጠ ወደ ተሻለ ቅድስና ደረጃ ይጓዛሉ።  ጥያቄ፡- ዕብ 10፡14 አንብብ። ሀ) የኢየሱስ መሥዋዕትነት ለዘላለም ምን አደረገልን? ለ) አሁንና እዚሁ ምን እየተደረገልን ነው?  ጥያቄ፦ 1ኛ ተሰ. 4፡3 አንብብ። የእግዚአብሔር ፈቃድ ለእኛ ምንድን ነው?  ጥያቄ- 1ኛ ጴጥ. 1፡14-16 አንብብ። ሀ) እግዚአብሔር ምን እንድናደር ጠራን? ለ) እግዚአብሔር ምንን እንዳናደርግ ጠራን? ሐህ ይህንንስ በምን ምክንያት እናደርጋለን? ማንም በእውነት እንደገና የተወለደ ሰው በእግዚአብሔር ፊት የቅድስና ስፍራን በማግኘቱ ብቻ አይረካም። በእውነት ከልባቸው ኢየሱስን እንደ ግል መድኃኒታቸው አድርገው የሚያውቁት በየዕለቱ በሚያደርጉትና በሚያጋጥማቸው ሁሉ የበለጠ ቅዱሳን ለመሆን ፍላጎታቸው ነው። ይህ የቅድስና ስፍራ በሕይወታችን ውስጥ በተግባር ወደሚገለጥና ወደሚያድግ ቅድስና ይመራናል። ዕብ 10፡14 አንድ መሥዋዕት የሚቀደሱትን ሁሉ ፍጹማን አደረገ ይላል። ይህ ጥቅስ የተሰጠንን የቅድስና ስፍራና እንደዚሁም በሕይወታችን ውስጥ በተሞክር የሚታየውን አዳጊ የሆነ ቅድስና ይገልጻል። የኢየሱስ ብቸኛ መሥዋዕትነት በእግዚአብሔር ፊት ስፍራችንን ፍጹም

ቅድስና  Read More »