በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ሞናርካዊነት ወይም ስባልዮሳዊነት 

This entry is part 25 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

አስተምህሮ ምንድን ነው? 

የክርስቶስ አስተምህሮ አስፈላጊነትና ድነት (ደኅንነት) 

የክርስቶስ መለኮታዊነት 

ኢየሱስ ሁሉን ቻይ እና ሁሉን የሚገዛ ነው

ኢየሱስ ሁሉን አዋቂ ነው 

ኢየሱስ በሁሉም ቦታ ይገኛል 

የኢየሱስ ባሕርይ አይለዋወጥም 

ኢየሱስ ሕይወትን ይሰጣል 

ኢየሱስ ተሰግዶለታል

ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ገልጾአል ፤ ኢየሱስ ይቅርታን መስጠት ይችላል 

ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ሥልጣን አለው 

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ዓይነት ባሕርይ እንዳለው ገለጸ 

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ተቀብሏል 

የክርስቶስ አምላክነት በቆላስይስ 1፡15-20 

የኢየሱስ ክርስቶስ ሰብአዊነት 

ኢየሱስ ፍጹም ሰው መሆኑን እንዴት እናውቃለን? 

የኢየሱስ ሰብአዊ ስሜቶች 

ኃጢአት አልባው የኢየሱስ ሰብአዊነት 

የኢየሱስ ከድንግል መወለድ 

ተሠገዎ በዮሐንስ 1 

ስለ ተሠገዎ በፊልጵስዩስ ምዕራፍ 2 

ስለ ተሠገዎ በዕብራውያን ምዕራፍ 2 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኢቢዮናውያን 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኖስቲካዊነት

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ሞናርካዊነት ወይም ስባልዮሳዊነት 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ አርዮሳዊነት 

ተሠገዎ፥ ክፍል 2 

ክርስቶስ «አንድ ባሕርይ» አለው የሚለው አስተምህሮ በኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስለ ክርስቶስ ተሠገዎ ያላት ምሥጢረ እምነት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ስለ ክርስቶስ ባሕርይና አካል ያላቸው እምነት

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ውስጥ የተገለጠባቸው መልኮችና ምሳሌዎች

በብሉይ ኪዳን ውስጥ የያህዌ መልአክ (ቅድመ- ተሠገዎ የክርስቶስ መገለጥ)

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ዘመን ሲገለጥ (ቅድመ-ተሠገዎ)

በብሉይ ኪዳን የክርስቶስ ተምሳሌቶች

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

መሢሑ ኢየሱስ

መሢሑ እንደ ንጉሥ 

መሢሑ እንደ ካህን 

መሢሑ እንደ ነቢይ 

መሢሑ እንደ መድኅን 

ኢየሱስ የሰው ልጅ 

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለ መሆኑ በብሉይና በወንጌላት ውስጥ 

የእግዚአብሔር ልጅ መለኮታዊ ነው። 

በጳውሎስና በዮሐንስ መጻሕፍት ውስጥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መገለጹ 

ኢየሱስ እንደ ጌታ 

የክርስቶስ መቀባት

ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ምሳሌያችን 

ኢየሱስ እና የእግዚአብሔር መንግሥት

የኢየሱስ ሞት 

የክርስቶስ ከፍ ከፍ ማለት (ዕርገት)

የኢየሱስ ዕርገት (ከፍ ከፍ ማለት) 

ኢየሱስ አሁን ያለው ባሕሪና አገልግሎቱ

ክርስቶስ እንደ መካከለኛና እንደ አማላጅ 

የደኅንነት አስፈላጊነት- ሰዎች ኃጢአተኛ በሆነ ባሕርይ ተወለዱ ማለት ምን ማለት ነው?

ኃጢአት ከየት መጣ? 

የኃጢአት ውጤት፡- ሞት 

ሁላችንም ከአዳም ኃጢአት በደልን ወርሰናል

ሁሉም ሰው የኃጢአት ተግባርን ፈጽሟል 

ኃጢአት በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ 

ሕፃናት በእርግጥ ኃጢአትን ለመሥራት ከደረሱበት ጊዜ በፊት የኃጢአት በደለኞች ይባላሉ? 

አንዳንዱ ኃጢአት ከሌላው የባሰ ነውን? 

ይቅርታ የማይደረግበት ኃጢአት ምንድን ነው? 

የደኅንነት ትርጉም፡- ከኃጢአትና ከኃጢአት ውጤቶች ሁሉ መዳን 

የእግዚአብሔር ቅዱስነት የኃጢአትን መሥዋዕት ይሻል፡- የብሉይ ኪዳን ምሳሌ 

ኢየሱስ ለኃጢአት ፍጹም የሆነ መሥዋዕት ሆነ፦ የአዲስ ኪዳን መፈጸም

የኢየሱስ ሞት የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቁጣ ለማርካት (ለማብረድ) የቀረበ መሥዋዕት ነው። 

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀን 

ኢየሱስ የራሱ ሰዎች እንድንሆን ከኃጢአት ዋጀን

የኢየሱስ ሞት በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን አስገኝቷል- ክፍል አንድ 

ኢየሱስ በሞቱ በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን ተቀዳጅቷል – ክፍል ሁለት 

ወደ ደኅንነት መድረሻው መንገድ – የእግዚአብሔር ምርጫና የእግዚአብሔር ጥሪ 

እግዚአብሔር ለጥቂቶች ምሕረቱን ሊሰጥ ይመርጣል 

እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ የመረጣቸውን አበክሮ ይጠራቸዋል። 

ስለ እግዚአብሔር ምርጫና ለደኅንነት ስለሚያደርገው ጥሪ ጥያቄዎች 

የመዳኛ መንገድ፡- ንስሐ እምነትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ 

ወደ እግዚአብሔር መመለስ ወይም «መለወጥ» 

እምነት ከታዛዥነት ጋር እንዴት ይዛመዳል? 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 1 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 2 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር የመተባበር በረከቶች ምንድን ናቸው? 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር መተባበር ማለት ምን ማለት ነው? 

ጽድቅና ይቅርታ፥ ክፍል አንድ 

ጉዲፈቻ (የማደጎ ልጅ) 

ቅድስና 

የደኅንነት በረከቶች – እንከብራለን ሲባል ምን ማለት ነው?  

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫ እና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 1 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 2 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 3 

ደኅንነትን የመቀበል ጥያቄ፣ እምነትና ጥምቀት  

ቅዱስ ቁርባንን መቀበል፥ ደኅንነት ያስገኛል? 

የሚሞቱ ሕፃናት ይድናሉ? 

ለመሆኑ በመጨረሻው ሰዎች ሁሉ ይድናሉ ወይ? 

ሰዎች የክርስቶስን መልእክት ሳይሰሙ ሊድኑ ይችላሉ? 

በጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ኢቢዮናዊነት ከተወገዘ በኋላ የእግዚአብሔርን እንድነት የሚያስጠብቅ የመሰለ የሐሰት ትምህርት ተነሣ። እነዚህ ቡድኖች «ሞናርካዊነት» በተባለ አስተምህሮ ያምኑ ነበር። እነርሱም እግዚአብሔር አንድ በመሆኑ ላይ አጥብቀው አጽንኦት ይሰጡ ነበር። ነገር ግን እነዚህ ቡድኖች የሚያታግል ጥያቄ ነበራቸው፡ ጥያቄያቸው እግዚአብሔር አንድ ከሆነ ኢየሱስ በምን አኳኋን እግዚኣብሔር ሊሆን ይችላል? የሚል ነበር። ከእነዚህ አንዱ የሞናርካዊነት ቡድን ደግሞ ከኢቢዮናውያን ጋር የሚመሳሰል ትምህርት ያስተምሩ ነበር። እነርሱም ኢየሱስ ሰው ነበር፥ ነገር ግን ጻድቅ የሆነ ሰው ነበር። ስለሆነም እግዚአብሔር ይህን ጻድቅ ሰው (ኢየሱስን) በጥምቀቱ ጊዜ ወስዶ በተለየ መንገድ ተገለገለበት ይላሉ። ቤተ ክርስቲያን ኢቢዮናውያንን በተቃወመችበት መንገድ መልስዋን በመስጠት ትምህርታቸው ሐሰተኛ መሆኑን አጋልጣለች። ነገር ግን ሁለተኛ ዓይነት ሞናርካዊነትም ነበር። ይህ ቡድንም በእግዚአብሔር አንድነት ላይ አጽንኦት ነበረው። እነዚህም አንድ እግዚአብሔር ብቻ አለ፥ ይህም እግዚአብሔር በተለያዩ አካላት አማካይነት ራሱን ገልጧል ይላሉ። እነርሱም አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር ራሱን እንደ አብ፥ በሌላ ጊዜ ደግሞ እንደ ወልድ፥ በሌላ ጊዜ ደግሞ ራሱን እንደ መንፈስ ቅዱስ ገለጠ ብለው ያስተምራሉ። ስለዚህ እነዚህ ቡድኖች ኢየሱስ እግዚአብሔር በመሆኑ ላይ ቢስማሙበትም፥ ነገር ግን ከእግዚአብሔር አብ ጋር አንድ አካል ነው ይሉ ነበር። የዚህ ሐሰት ትምህርት ዋናው መምህር ሳባልዮስ የተባለ ሰው ነበር። ከዚህ የተነሣ አንዳንድ ጊዜ ትምህርቱ ሳባልዮሳዊነት ተብሎ ይጠራል። 

ጥያቄ፡- ሀ) ሞናርካውያን ዋና ትኩረት ይሰጡዋቸው የነበረው ምንን ነበር? ለ) ሰባልዮስ ስለ አብ፥ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ምን ነበር? 46ኛ ጥያቄ፡- ማቴዎስ 3፡13-17 28፡19-20፥ እንዲሁም 2ኛ ቆሮንቶስ 3፡14 አንብቡ። በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ የሳባሊዮስ ትምህርቶች ሐሰት መሆናቸውን የሚያጋልጥ ምን አላቦች ታያላችሁ? 

ሞናርካውያን ሁሉ በእግዚአብሔር ኣንድነት ላይ አጽንኦታቸውን ያደርጋሉ። ማለትም እግዚአብሔር አንድ ብቻ ነው ይላሉ። ብዙዎቹ የሳባሊዮስን አስተምህሮ በመከተል፥ እግዚአብሔር አንድ ሲሆን፥ ራሱን ግን በተለያዩ አካላት ወይም አምሳል ገልጧል በማለት ያምናሉ። ይህን ሲሉ አንዱ እግዚአብሔር አንዳንድ ጊዜ እንደ ኣብ፥ በሌላ ጊዜ እንደ ወልድ፥ እንዲሁም በሌላ ጊዜ ደግሞ እንደ መንፈስ ቅዱስ ራሱን ገልጧል ማለታቸው ነው። ሳባሊዮስ ያስተማረው ራሱን በተለያዩ ሦስት መንገዶች የገለጠ አንድ እግዚአብሔር ብቻ አለ ብሎ ነበር። በአዲስ ኪዳን ውስጥ የሚገኙ አያሌ ጥቅሶች የሳባሊዮላ አስተምህሮ ሐሰት መሆኑን ያረጋግጣሉ። ኢየሱስ – በጥምቀቱ ጊዜ ውኃው ውስጥ ቆሞ ሳለ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወርዶ ሲያርፍበት፥ ከሰማይ ደግሞ የእግዚአብሔር ድምፅ ሲመጣ ተሰምቶአል። ከዚህ ጥቅስ እንደምንረዳው እግዚአብሔር አንዳንድ ጊዜ በአብ፥ ሌላ ጊዜ በወልድ እንዲሁም ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ በተለያየ ሁኔታ የሚገለጥ እንዳይደለ ግልጽ ነው። ሁሉም የሥላሴ አካላት በአንድ ጊዜ በተለያዩ ሁኔታዎች ይገለጣሉ። በሁለቱም በማቴዎስ 28፡19-20 እና በ2ኛ ቆሮንቶስ 13፡14፤ አብ፥ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ሁሉም አንድ አምላክ የሆኑ ራሳቸውን የቻሉ አካላት መሆናቸው ተገልጾአል። ስለዚህ የሳሳሊዮስ አስተምህሮ መጽሓፍ ቅዱሳዊ ባለመሆኑ በጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን መሪዎች ዘንድ ተወግዟል። 

ጥያቄ፡- ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ የሳባሊዮስን አስተምህሮ የተከተለ ምን የሐሰት ትምህርት ታውቃላችሁ? 

ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ የሳባሊዮስን የሐሰት ትምህርት የሚከተሉ ቡድኖች «የሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን» አማኒያን የሚባሉ አሉ። «የሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን» ሳባሊዮስ እግዚአብሔር አንድ ብቻ ነው፤ እርሱም አንዳንድ ጊዜ እንደ አብ፥ በሌላ ጊዜ እንደ ወልድ፥ እንዲሁም ደግሞ እንደ መንፈስ ቅዱስ ራሱን ይገልጣል ብሎ ያለውን የስሕተት ትምህርት በቀጥታ ይከተላሉ። ከእነዚህ ቡድኖች መካከል አንዳንዶቹ ስሜታዊ የሆኑ ዝማሬዎችን ስለሚያሰሙና እምነታቸውንም በዚሁ ስሜት ስለሚያስፋፉ በጣም ተቀባይነት አግኝተዋል። ስለዚህ ብዙ ሰዎች እነዚህ ቡድኖች ትክክለኛች ናቸው፤ ምክንያቱም የሚታይባቸው ደስታና የመንፈስ ግለት ይህን ይመሰክራል ይላሉ። ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ እንደሚያስተምረን እግዚአብሔር አብ፥ እግዚአብሔር ወልድና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሦስት አካላት እንጂ የአንድ አምላክ ልዩ ልዩ መገለጫዎች አይደሉም። የሳባሊዮስ አስተምህሮት ሐሰት መሆኑ ቢታወቅም ቤተ ክርስቲያን የሥላሴን አስተምህሮ በተመለከተ በማያሻማ ሁኔታ ጥርት ያለ ግንዛቤና አቋም እንዲኖራት በማድረግ በኩል ረድቷታል። በዚህ መሠረት የሥላሴ ኣስተምህሮ እግዚአብሔር አንድም ሦስትም ነው የሚል ጽኑ አቋም ያዘ።

ምንጭ፡- “አስተምህሮ ክርስቶስና ደኅንነት”፤ ጽሑፍ፣ በዶ/ር ስቲቭ ስራውስ፤ ትርጉም በኃይሉ ልመንህ

አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኖስቲካዊነት በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ አርዮሳዊነት 

1 thought on “በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ሞናርካዊነት ወይም ስባልዮሳዊነት ”

  1. On Fri, Feb 11, 2022, 9:18 PM ወንጌል በድረ-ገፅ አገልግሎት wrote:

    > tsegaewnet posted: ” በጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ኢቢዮናዊነት ከተወገዘ በኋላ የእግዚአብሔርን እንድነት
    > የሚያስጠብቅ የመሰለ የሐሰት ትምህርት ተነሣ። እነዚህ ቡድኖች «ሞናርካዊነት» በተባለ አስተምህሮ ያምኑ ነበር። እነርሱም
    > እግዚአብሔር አንድ በመሆኑ ላይ አጥብቀው አጽንኦት ይሰጡ ነበር። ነገር ግን እነዚህ ቡድኖች የሚያታግል ጥያቄ ነበራቸው፡
    > ጥያቄያቸው እግዚአብሔር አንድ ከሆነ ኢየሱስ በምን አኳኋን እግዚኣብሔር ሊሆን ይች”
    >

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading