ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ገልጾአል ፤ ኢየሱስ ይቅርታን መስጠት ይችላል 

This entry is part 10 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

አስተምህሮ ምንድን ነው? 

የክርስቶስ አስተምህሮ አስፈላጊነትና ድነት (ደኅንነት) 

የክርስቶስ መለኮታዊነት 

ኢየሱስ ሁሉን ቻይ እና ሁሉን የሚገዛ ነው

ኢየሱስ ሁሉን አዋቂ ነው 

ኢየሱስ በሁሉም ቦታ ይገኛል 

የኢየሱስ ባሕርይ አይለዋወጥም 

ኢየሱስ ሕይወትን ይሰጣል 

ኢየሱስ ተሰግዶለታል

ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ገልጾአል ፤ ኢየሱስ ይቅርታን መስጠት ይችላል 

ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ሥልጣን አለው 

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ዓይነት ባሕርይ እንዳለው ገለጸ 

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ተቀብሏል 

የክርስቶስ አምላክነት በቆላስይስ 1፡15-20 

የኢየሱስ ክርስቶስ ሰብአዊነት 

ኢየሱስ ፍጹም ሰው መሆኑን እንዴት እናውቃለን? 

የኢየሱስ ሰብአዊ ስሜቶች 

ኃጢአት አልባው የኢየሱስ ሰብአዊነት 

የኢየሱስ ከድንግል መወለድ 

ተሠገዎ በዮሐንስ 1 

ስለ ተሠገዎ በፊልጵስዩስ ምዕራፍ 2 

ስለ ተሠገዎ በዕብራውያን ምዕራፍ 2 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኢቢዮናውያን 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኖስቲካዊነት

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ሞናርካዊነት ወይም ስባልዮሳዊነት 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ አርዮሳዊነት 

ተሠገዎ፥ ክፍል 2 

ክርስቶስ «አንድ ባሕርይ» አለው የሚለው አስተምህሮ በኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስለ ክርስቶስ ተሠገዎ ያላት ምሥጢረ እምነት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ስለ ክርስቶስ ባሕርይና አካል ያላቸው እምነት

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ውስጥ የተገለጠባቸው መልኮችና ምሳሌዎች

በብሉይ ኪዳን ውስጥ የያህዌ መልአክ (ቅድመ- ተሠገዎ የክርስቶስ መገለጥ)

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ዘመን ሲገለጥ (ቅድመ-ተሠገዎ)

በብሉይ ኪዳን የክርስቶስ ተምሳሌቶች

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

መሢሑ ኢየሱስ

መሢሑ እንደ ንጉሥ 

መሢሑ እንደ ካህን 

መሢሑ እንደ ነቢይ 

መሢሑ እንደ መድኅን 

ኢየሱስ የሰው ልጅ 

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለ መሆኑ በብሉይና በወንጌላት ውስጥ 

የእግዚአብሔር ልጅ መለኮታዊ ነው። 

በጳውሎስና በዮሐንስ መጻሕፍት ውስጥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መገለጹ 

ኢየሱስ እንደ ጌታ 

የክርስቶስ መቀባት

ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ምሳሌያችን 

ኢየሱስ እና የእግዚአብሔር መንግሥት

የኢየሱስ ሞት 

የክርስቶስ ከፍ ከፍ ማለት (ዕርገት)

የኢየሱስ ዕርገት (ከፍ ከፍ ማለት) 

ኢየሱስ አሁን ያለው ባሕሪና አገልግሎቱ

ክርስቶስ እንደ መካከለኛና እንደ አማላጅ 

የደኅንነት አስፈላጊነት- ሰዎች ኃጢአተኛ በሆነ ባሕርይ ተወለዱ ማለት ምን ማለት ነው?

ኃጢአት ከየት መጣ? 

የኃጢአት ውጤት፡- ሞት 

ሁላችንም ከአዳም ኃጢአት በደልን ወርሰናል

ሁሉም ሰው የኃጢአት ተግባርን ፈጽሟል 

ኃጢአት በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ 

ሕፃናት በእርግጥ ኃጢአትን ለመሥራት ከደረሱበት ጊዜ በፊት የኃጢአት በደለኞች ይባላሉ? 

አንዳንዱ ኃጢአት ከሌላው የባሰ ነውን? 

ይቅርታ የማይደረግበት ኃጢአት ምንድን ነው? 

የደኅንነት ትርጉም፡- ከኃጢአትና ከኃጢአት ውጤቶች ሁሉ መዳን 

የእግዚአብሔር ቅዱስነት የኃጢአትን መሥዋዕት ይሻል፡- የብሉይ ኪዳን ምሳሌ 

ኢየሱስ ለኃጢአት ፍጹም የሆነ መሥዋዕት ሆነ፦ የአዲስ ኪዳን መፈጸም

የኢየሱስ ሞት የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቁጣ ለማርካት (ለማብረድ) የቀረበ መሥዋዕት ነው። 

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀን 

ኢየሱስ የራሱ ሰዎች እንድንሆን ከኃጢአት ዋጀን

የኢየሱስ ሞት በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን አስገኝቷል- ክፍል አንድ 

ኢየሱስ በሞቱ በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን ተቀዳጅቷል – ክፍል ሁለት 

ወደ ደኅንነት መድረሻው መንገድ – የእግዚአብሔር ምርጫና የእግዚአብሔር ጥሪ 

እግዚአብሔር ለጥቂቶች ምሕረቱን ሊሰጥ ይመርጣል 

እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ የመረጣቸውን አበክሮ ይጠራቸዋል። 

ስለ እግዚአብሔር ምርጫና ለደኅንነት ስለሚያደርገው ጥሪ ጥያቄዎች 

የመዳኛ መንገድ፡- ንስሐ እምነትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ 

ወደ እግዚአብሔር መመለስ ወይም «መለወጥ» 

እምነት ከታዛዥነት ጋር እንዴት ይዛመዳል? 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 1 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 2 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር የመተባበር በረከቶች ምንድን ናቸው? 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር መተባበር ማለት ምን ማለት ነው? 

ጽድቅና ይቅርታ፥ ክፍል አንድ 

ጉዲፈቻ (የማደጎ ልጅ) 

ቅድስና 

የደኅንነት በረከቶች – እንከብራለን ሲባል ምን ማለት ነው?  

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫ እና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 1 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 2 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 3 

ደኅንነትን የመቀበል ጥያቄ፣ እምነትና ጥምቀት  

ቅዱስ ቁርባንን መቀበል፥ ደኅንነት ያስገኛል? 

የሚሞቱ ሕፃናት ይድናሉ? 

ለመሆኑ በመጨረሻው ሰዎች ሁሉ ይድናሉ ወይ? 

ሰዎች የክርስቶስን መልእክት ሳይሰሙ ሊድኑ ይችላሉ? 

ስለ ኢየሱስ መለኮታዊነት ከሚጠቀሱ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መተማመኛ ነጥቦች አንዱና ዋንኛው ኢየሱስ ስለ ራሱ ሲያስብና ሲናገር የነበረውን መመልከት ነው። ኢየሱስ የኖረበት የአይሁዳውያን ሳሕል በአንዱ አምላክ ብቻ አጠንክር የሚያምን ነበር። ብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ግርማ ሞገስ ያለው ኃይለኛና ከሰዎችም ሁሉ በላይ መሆኑን አስተምሯል። ይህ እንግዲህ ሰው አምላክ ሊሆን እንደሚችል ለመገመት የሚሳነው ባህል ነበር። የሆነ ሆኖ ኢየሱስ በዚህ ባሕል ውስጥ ያደገ ቢሆንም እርሱ እግዚአብሔር መሆኑን አስታውቋል። በአንድ አምላክ በሚያምን ባሕል ውስጥ ስለኖረም፥ ኢየሱስ በግልጽ «እኔ አምላክ ነኝ» አላለም። በዚህ ፈንታ እርሱ አምላክ መሆኑን በንግግሩና በሥራው አማካይነት በተዘዋዋሪ መንገድ ይገልጽ ነበር። ስለ አምላክነቱ በአካባቢው ለነበሩ ሰዎች ብዙ ማስረጃዎችን ሰጥቷል። ስለሆነም ኢየሱስ አምላክነቱን በባሕርይውና በተግባሩ ያረጋግጥ ነበር። 

አንዳንድ መናፍቃንና የሃይማኖት ክፍሎች የኢየሱስን አምላክነት ሲክዱም፥ በአንጻሩ ታላቅ ሰው መሆኑን፥ ነቢይነቱንና እግዚአብሔር ከፈጠራቸው ፍጥረታት ሁሉ በላይና በኩር መሆኑን ይናገራሉ። በዛሬው ጥናታችን፥ ኢየሱስ ራሱ አምላክ መሆኑን ሲገልጽ እንመለከታለን። እንግዲህ ኢየሱስን ለማክበር የሚፈልግ ሰው፥ እርሱ ስለ ራሱ ያሳወቀውንና የገለጸውን ሐቅ መቀበል አለበት። ስለዚህ ማንም ሰው በአንድ በኩል ኢየሱስን እያከበረ፥ በሌላ በኩል አምላክነቱን ሊክድ አይችልም።

ኢየሱስ ይቅርታን ሰጠ 

ጥያቄ፡ በማርቆስ ወንጌል 2፡1-22 ያለውን ታሪክ አንብቡ። ሀ) በዚህ ክፍለ ምንባብ ውስጥ ኢየሱስ አምላክነቱን ያረጋገጠባቸው ብዙ መንገዶች የትኞቹ ናቸው? ቢያንስ ሦስት መንገዶችን ፈልጉ፡ ላ) በቁጥር 5 ላይ ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ያውቅ እንደነበር የሚገልጽ ምን ተናገረ? ሐ) በቁጥር 7 ላይ የሕግ መምህራን ጥያቄ | አንሥተዋል። ለዚህ ጥያቄ መልሱ ምን ይመስላችኋል? 

ማርቆስ 2፡1-12 ኢየሱስ በብዙ ምክንያቶች እግዚአብሔር መሆኑን የሚያስገነዝብ ማረጋገጥ ነው። በመጀመሪያ፥ ኢየሱስ ሽባውን ሰው ሲፈውስ በታምራዊ ኃይሉ አምላክነቱን አሳይቷል። ሁለተኛ፥ ኢየሱስ የሕግ መምህራኑ ያሰቡት የነበረውን ያውቅ እንደ ነበር በአነጋገሩ አስገንዝቦአቸዋል። ኢየሱስ የሰዎችን አሳብና ሌሎችንም ነገሮች ሁሉ ያውቅ ስለ ነበረ እግዚአብሔር መሆኑን አሳይቷቸዋል። ሦስተኛው፡ ኢየሱስ አምላክነቱን የገለጸው ኃጢአትን ይቅር በማለት ነበር። ኢየሱስ ሽባውን ሰው ከመፈወሱ በፊት ገና እንዳየው «ኃጢአትህ ተሰረየችልህ» አለው። ይህ አነጋገር እዚያ የነበሩትን የሕግ መምህራን አስከፋ። ምክንያቱም ኃጢአትን ይቅር ለማለት የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ ያስቡ ስለነበር ነው። አዎን፥ ትክክል ነበሩ፥ ኃጢአትን ይቅር ለማለት የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ይህንንም ኢየሱስ ደህና አድርጎ ያውቅ ነበር። ስለዚህ፥ ለሽባው ሰው «ኃጢአትህ ተሰረየችልህ» ሲለው፥ በተዘዋዋሪ መንገድ «እኔ የእግዚአብሔር ሥልጣን አለኝ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ» ማለቱ ነበር። ከዚያም ኃጢአትን ይቅር የማለት ሥልጣን እንዳለው ሽባውን ሰው በመፈወስ አረጋገጠ። ስለዚህ ኢየሱስ ኃጢአትን ይቅር የማለት ሥልጣን እንዳለው በመግለጽ፥ እርሱ እግዚአብሔር መሆኑንም አረጋግጧል። 

ጥያቄ፡- ሉቃስ 7፡36-50 አንብቡ። ይህ ታሪክ በማርቆስ 2፡1-12 ካለው ጋር በምን መንገድ ይመሳሰላል? 

በሉቃስ 7፡36-50 ተመሳሳይ ታሪክ ተፈጽሟል። ኢየሱስ ስምዖን ወደ ተባለ ፈሪሳዊ ቤት እራት ተጋብዞ ነበር። እዚያም በማዕድ ላይ ሳሉ አንዲት ኃጢአተኛ ሴት ወደ ቤቱ ገብታ በኃጢአቷ እየተጸጸተች የኢየሱስን እግር በሽቶ ቀባችው። ኢየሱስም ንስሐ መግባቷንና እምነትዋን ካየ በኋላ «ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል» አላት። ልክ በማርቆስ 2 ላይ እንደተናገሩት ኢየሱስ ኃጢአትን ይቅር በማለቱ የሃይማኖት መሪዎች ተበሳጩ። ልክ በማርቆስ 2 ላይ እንደተገለጸው ኢየሱስ እግዚአብሔር ብቻ ኃጢአትን ይቅር እንደሚል ያውቅ ነበር። ነገር ግን ለሴትዮዋ ኃጢአትሽ ተሰረየልሽ በማለቱ በተዘዋዋሪ መንገድ አምላክ መሆኑን ገለጸ።

ምንጭ፡- “አስተምህሮ ክርስቶስና ደኅንነት”፤ ጽሑፍ፣ በዶ/ር ስቲቭ ስራውስ፤ ትርጉም በኃይሉ ልመንህ

አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ኢየሱስ ተሰግዶለታል ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ሥልጣን አለው 

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading