የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

ጥያቄ፡- ሀ) የሙሉ ወንጌል መጋቢ ወይም ወንጌላዊ የሆነን ሰው በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ስለሚፈጸመው ሁለተኛ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ማስረጃ የሆኑ ጥቅሶችን እንዲነግርህ ጠይቅ። ለ) ለእነዚህ ጥቅሶች የሚሰጠውን ማብራሪያ (ትርጉም) አድምጥ። ሐ) እነዚህን ጥቅሶች የምንረዳባቸው ሌሎች መንገዶች የትኞቹ ናቸው? መ) የትኛውን ትርጉም ትመርጣለህ? ለምን?  ጰንጠቆስጤ በሆኑትና ባልሆኑት መካከል ያለው የትርጉም ልዩነት ከየት መጣ። በመሠረቱ የጰንጠቆስጤ የሥነ መለኮት ትምህርት የተመሠረተው የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍን በሚረዱበት ሁኔታ ላይ ነው። የጰንጠቆስጤ ክርስቲያኖች የሐዋ. ምዕራፍ 2፣ 8፣ 10ና 19 ያሉት አሳቦች ክርስቲያኖች ሁሉ ሊያልፉበት የሚገባ የድነት (ደኅንነት) ሁለት ደረጃዎች ናቸው ይላሉ። የመጀመሪያው የድነት (ደኅንነት) ደረጃ ሲሆን፥ ሁለተኛው ደግሞ ለአገልግሎት አዲስ ኃይል መቀበል ነው። እነዚህ ሁለት ደረጃ ዎች እንድ ሰው በሚያምንበት ጊዜ ወዲያውኑ ሊፈጸሙ ይችላሉ። ሆኖም ግን ኃይልን መቀበል ብዙ ጊዜ የሚፈጸመው አንድ ሰው ክርስቲያን ከሆነ በኋላ ነው። የኢየሱስ ክርስቶስ ልምምድንም ይጠቅሳሉ። የተወለደው በመንፈስ ቅዱስ ነበር። ሆኖም ግን መንፈስ ቅዱስ በኃይል የወረደበት በሚጠመቅበት ጊዜ ነበር። ይህ በመንፈስ ቅዱስ መወለድና ለአገልግሎት በመንፈስ ቅዱስ መቀባት ሁለት ደረጃ ለእነርሱ የተለመደ የማንኛውም ክርስቲያን ልምምድ መሆኑን ያመለክታል። እነዚህ የጰንጠቆስጤ ክርስቲያኖች ወደ ራሳቸው ልምምድም በማመልከት እዚህ ሁለት ደረጃዎች ማንኛውም ክርስቲያን ሊያልፍባቸው የሚገቡ ናቸው ይላሉ። ለብዙዎቹ መንፈስ ቅዱስ ሕይወታቸውን አስደናቂ በሆነ መንገድ የለወጠበት የተለየ ጊዜ አላቸው። የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትንና የመንፈስ ቅዱስ ሙላትን አንድ ልምምድ አድርገው ይመለከታሉ።  ይህ ሁለተኛው በረከት ወይም የመንፈስ ቅዱስ ቅባት የሚፈጸመው እንዴት ነው? ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች እንደሚያምኑት በአዲስ ኪዳን በኢየሱስ በቀደሙት ደቀ መዛሙርትና በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ደግሞ እንደ ጳውሎስ ባሉ ሰዎች ሕይወት የሚታይ ወጥ የሆነ ምሳሌ አለ። ይህም በመጀመሪያ የሕይወት ለውጥ ይኖራል። ቀጥሎ ጸሎት ከዚያም እራስን ፈጽሞ መስጠትና በመጨረሻም የመንፈስ ቅዱስ ስጦታን ለመቀበል መጠበቅን ያካተተ ሂደት ነው። መቶ ሃያዎቹ ደቀ መዛሙርት በኢየሱስ አመኑ። ከዚያም በጸሎትና መንፈስ ቅዱስን ለመቀበል በጉጉት በመጠባበቅ በኢየሩሳሌም ቆዩ። ሳውልም (ጳውሎስም) ሆነ የመቶ አለቃው (የሐዋ. 10) መንፈስ ቅዱስን ከመቀበላቸው በፊት ጸሎት መደረግ ነበረበት። ስለዚህ የጰንጠቆስጤ ክርስቲያኖች ይህን ልዩ የሆነ በረከት እንቀበል ዘንድ ካስፈለገን በጸሎት አንዳንድ ጊዜም በተራዘመ ጸሎት ልንፈልገው ይጠበቅብናል ይላሉ። በተጨማሪ እግዚአብሔር መንፈሱን ለእኛ እስኪልክ ድረስ በከፍተኛ ጉጉት መጠባበቅ አለብን ይላሉ። እንደ እነርሱ አመለካከት፡ መንፈስ ቅዱስ እንዲወርድባቸው በግል ጥረታቸው የሚያስገድዱት ሳይሆን በእምነት ላለመቀበል የሚፈጽሙት ድርጊት ነው።  ለካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ይህ ሁለተኛ በረክት የሚረጋገጠው እንዴት ነው? መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ ላይ በኃይል መውረዱን የሚያውቁት እንዴት ነው? ኢየሱስ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታን ሊሰጠን በርካታ ነርች እንደሚፈጸሙ ይናገራሉ።  1. በሳውዲው ሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔር ህልውና በከፍተኛ ደረጃ የሚሰማ ይሆናል። መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን የሚያስወድድ ክፍተኛ ፍቅርን ይሰጣል።  2. መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ለመሆኑ ግልጽ የሆነ ማረጋገጥ በሰው ልብ ውስጥ ይቀመጣል።  3. የሚያስፈነድቅ ደስታ ከሰው ልብ ውስጥ እየገነፈለ ይወጣል።  4. የክርስቶስ አካል ከሆኑት ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር የኅብረትና የአንድነት መንፈስ የጠበቀ ይሆናል።  5. ብዙ ጊዜ ደግሞ በልሳናት የመናገር ስጦታ ይሰጣል። በካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች እምነት በልሳን መናገር እርስ በርስ ወይም ከማያምኑ ሰዎች ጋር የምንነጋገርበት ቋንቋ ከመሆን ይልቅ ከእግዚአብሔር ጋር የምንግባባበት ነው። ስልሳን የሚናገር ሰው ብዙ ጊዜ ምን እንደሚናገር አያውቅም። ይልቁኑ በእርሱ ምትክ ስለ እርሱ ሆኖ ለእግዚእብሔር የሚናገረው መንፈስ ቅዱስ ነው። (በወደፊት ትምህርታችን ይህንን በበለጠ በጥልቀት እንመለከታለን) በአእምሮ ሳይሆን በመንፈስ መጸለይና መዘመርን ያጠብቃሉ። ብዙ ክርስቲያኖች በተለይ በጸሎት ጊዜ በጸጥታ ስልሳናት የሚናገሩትና በልሳናት በዜማ የሚዘምሩት ለዚህ ነው። ይህን ማድረጋቸው በመንፈስ የመጸለያቸውን ሁኔታ ያነሣሣል።  እነዚህ ሁሉ በአጠቃላይ ስሕተት ባይሆኑም እንኳ የሚከተሉት ልንመልሳቸው የሚገቡን ጥያቄዎች ናቸው። ) መጽሐፍ ቅዱስ እንደ «ሁለተኛ በረከት» ያለ ልምምድ መኖሩን ያስተምረናልን? እና 2) ይህ በረከት በልሳናት መናገርን ያጠቃልላል? ወይስ ማጠቃለል አለበት ብሎ መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል? የካሪዝማቲክ ክርስቲያናዊ ሥነ መለኮት እንደ ግዴታ ለሚያስቀምጣቸው ሁላተኛ በረከትና በልሳን መናገር በመልእክቶች ውስጥ ድጋፍ የሚሰጥ በቂ መረጃ አይገኝም። የሥነ መለኮት ትምህርታቸው በሙሉ የሚመነጨው ከሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ላይ ነው። ይህ መጽሐፍ ደግሞ ከብሉይ ኪዳን ወደ አዲስ ኪዳን የተደረገውን ሽግግር የሚያሳይ ነው።  ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች እምነታቸውን ለመደገፍ የሚጠቀሙበትን የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ በዝርዝር ከመመልከታችን በፊት የሚጠቀሙበት መጽሐፍ ምን እንደሚያስተምር እንቃኝ።  ጥያቄ፡ ሀ) የሚከተሉትን ጥቅሶች አጥና። የሐዋ. 1፡5፥ 2፡4፥ 38-39፥ 4፡8፤ 31፤ 6፡3፥ 5፥7፤ 55፤ 8፡14-17፤ 9፡17-18 (22፡16)፤ 10፡44-47 (11፡5-17)፤ 13፡9፥ 52፤ 19፡1-7 አንብብ። ለ) በሚከተሉት ርእሶች ሠንጠረዥ በመሥራት መልሶቹን ከተዘረዘሩት ጥቅሶች ወስደህ ሙላባቸው። (1) ለመንፈስ ቅዱስ ተግባር የተሰጠ ስም (2) መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉበት ጊዜ (ሐ) በልሳን ተናግረዋልን? (መ) እጅ በመጫን ጸሎት ተደርጓልን? የመንፈስ ቅዱስ አጠቃላይ ገጽታ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ  1. ብዙ የጴንጠቆስጤ አማኞች ሉቃስ ጥምቀት፥ መሞላት፥ መቀበልና መውረድ የሚሉትን ቃላት የተጠቀመው በዓይነቱ እንድ የሆነ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎትን ለመግለጽ ነው፤ ይህም አንድ አማኝ ከዳነ በኋላ የአገልግሎት ኃይልን . የሚጎናጸፍበት ነው ይላሉ። ጰንጠቆስጤ ያልሆኑ ክርስቲያኖች ይህ የተለያዩ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት አገልግሎቶችን የሚያመለክት ሆኖ እንዳንዶቹ አገልግሎቶች በአንድ ጊዜ የሚፈጸሙ ሊሆኑ አይችሉምን? ይላሉ። ሉቃስ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለመግለጥ የተለያዩ ቃላትን እንደተጠቀመ የሚያሳይ አይሆንምን? አንዳንድ ጰንጠቆስጢዎች ሁለት ዓይነት መሞላት በሐዋርያት ሥራ ውስጥ እንዳለ ይታያቸዋል። ከድነት (ደኅንነት) በኋላ የሚጀምር የመጀመሪያ ጊዜ መሞላትና ከዚያ በየጊዜው የሚመጣ መሞላት ነው ይላሉ።  2. ከእነዚህ የመንፈስ ቅዱስ ሥራዎች አንዳንዶቹ በድነት (ደኅንነት) ወቅት የተፈጸሙ ቢመስሉም ብዙ ጰንጠቆስጤዎች ግን እነዚህ ሰዎች በሙሉ የመንፈስ ቅዱስን ጥምቀት የተቀበሉት ከድነት (ደኅንነት) በኋላ ነው በማለት ይናገራሉ። አንዳንዶች መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉት ከድነት (ደኅንነት) በኋላ ስለሆነ ደንቡ ይህ ነው ይላሉ። በሐዋ. 2 ላይ የምናገኛቸው አዲስ ክርስቲያኖችና በሐዋ 10 ላይ የተጠቀሰው ቆርኔሌዎስ በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀታቸውና በደኅንነታቸው መካከል ጥቂትም ቢሆን ጊዜ ነበር ይላሉ። ጳውሎስ ዳግም የተወለደው በደማስቆ መንገድ ሲሆን መንፈስ ቅዱስን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀበላው ቀን ከሦስት ቀን በኋላ ነበር ይላሉ። ሆኖም ግን እነዚህን ክፍሎች እንዳሉ ስንመረምራቸው እነዚህ ሰዎች የተጠቀሱትን የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች የተቀበሉት በሚድኑበት ጊዜ ነበር። በሚቀጥለው ሳምንት ይህን ክፍል በጥልቀት እናጠናዋለን።)  3. አብዛኛዎቹ የጰንጤቆስጤ ክርስቲያኖች ስልሳናት ላለመናገር ባልተጠቀሱባቸው ቦታዎችም በልሳናት መናገር እንደነበር ያምናሉ። ጳውሎስ በኋላ በልሳናት ይናገር ስለነበር (1ኛ ቆሮ. 14፡18) በመንፈስ ቅዱስ በሚጠመቅበት ጊዜ ተናግሯል ይላሉ። በሐዋ. 4፡3 ላይ ሰዎቹ «የእግዚአብሔርን ቃል በግልጥ ተናገሩ» የሚለው ቃል በልሳናት መናገርን የሚያመለክት አሳብ ነው ብለው ያምናሉ። በሐዋ. 8 ላይ የሰማሪያ ሰዎች መንፈስ ቅዱስ መቀበላቸው በማስረጃ ነት በሌሎች ሦስት ቦታዎች ስለታየ በእነዚህ ቦታዎችም መኖር ነበረበት ይላሉ። ሆኖም ግን በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ እነዚህ ሰዎች በልሳን ተናገሩ አይልም። እንደገና በልሳናት መናገር ከታየባቸው ሦስት ግልጽ ሁኔታዎች ሌላ ክፍሎቹን እንዳሉ በምናነባቸው ወቅት በልሳናት መናገር እንዳልነበረ እንገነዘባለን። ስለዚህ የሚባል ነገር ካለ በልሳናት ስለ መናገር ምንም ነገር አለመጠቀሱ ነው።  4. ብዙ የጰንጠቆስጤ ክርስቲያኖች የሐዋ. 2፡38 በክርስቲያን ልምምድ ውስጥ ስላሉ ሦስት ተከታታይ ደረጃ ዎች የሚያስተምር ነው የሚል ግንዛቤ አላቸው። መጀመሪያ ንስሐ መግባት፥ ከዚያም መጠመቅ፥ በመጨረሻም መንፈስ ቅዱስን መቀበል ናቸው። መጽሐፉ ግን ሁለት ትእዛዞችን ብቻ ይሰጣል። ‹ንስሐ ግቡና ተጠመቁ›፥ ከዚያም የተስፋ ቃል ይከተላል። ‹ትቀበላላችሁ› {የወደፊቱን የሚያመላክት})። ተስፋው የመጀመሪያዎቹን ሁላት ትእዛዞች መፈጸምን በቀጥታ የሚከተል ነው። ክፍሉን በግልጽ ስናነብ የሚያመለከቱን ንስሐ የገቡና የተጠመቁ መንፈስ ቅዱስን መቀበላቸውን ነው። በተጨማሪ ጥምቀት ለድነት (ደኅንነት) አስፈላጊ መሆኑን ክፍሉ እያስተምርም። ሐረጉ በዚህ መልክ መተርጎም ይችላል። ‹ንስሐ ግቡ ከኃጢአታችሁ ይቅር መባል የተነሣም ተጠመቁን። የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ንስሐ በመግባት ለተገኘ ውስጣዊ ምሕረት ውጪአዊ ምልክት ነው። በኢየሱስ ማመናቸው ትክክለኛ

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት) Read More »

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

2. የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት  መንፈስ ቅዱስ እያንዳንዱን ክርስቲያን ማደሪያ ስለማድረጉ ጉዳይ አናሳ ልዩነቶች ያሉ ቢሆንም ልዩነቱ እየሰፋና እያደገ የሚመጣው ወደ መንፈስ ቅዱስ የማጥመቅ አገልግሎት ስንገባ ነው። በሥነ መለኮት ትምህርታቸው ካሪዝማቲክ ያልሆኑት፥ የመንፈስ ቅዱስ የማጥመቅ አገልግሎት እያንዳንዱ ሰው ወደ ክርስቶስ መጥቶ በሚድንበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በልቡ ከሚፈጽማቸው ሥራዎች አንዱ ነው ብለው ያስተምራሉ። ይህ አገልግሎት መንፈስ ቅዱስ ወደ እያንዳንዱ አዲስ ክርስቲያን ልብ ውስጥ መጥቶ ማደሩን ከዚያም እያንዳንዱን ክርስቲያን የክርስቶስ አካል በሆነችው ዓለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መጨመሩን ያካትታል። ለካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ግን ይህ መንፈስ ቅዱስ በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ የሚሠራው የተለየ ሥራ ሲሆን ብዙ ጊዜ የሚፈጸመው ከዳኑ በኋላ ነው። ይህ ልዩና አንድ ጊዜ የሚፈጸም ሁለተኛው በረከት ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ልዩ በሆነ ኃይል ወደ ክርስቲያኑ ሕይወት ይመጣና በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ሕይወትን መኖር እንዲችል ያደርገዋል። መጽሐፍ ቅዱስ ከእነዚህ ሁለት አመለካከቶች የትኛውን ይደግፋል?  አዲስ ኪዳንን በምንመለከትበት ጊዜ ስለ መንፈስ ቅዱስ (ጥምቀት) በቀጥታ የጠቀሰባቸው ቦታዎች በጣም ጥቂት ሆነው እናገኛቸዋለን። ኢየሱስ ምድራዊ አገልግሎቱን በጀመረበት ወቅት መጥምቁ ዮሐንስ ለሕዝቡ ኢየሱስ በመንፈስና በእሳት እንደሚያጠምቅ ተናገረ (ማቴ. 3፡11)። ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርት አንድ ቀን መንፈስ ቅዱስ በሕይወታቸው ለመኖር እንደሚመጣ ቢነግራቸውም ወደ ሰማይ ከማረጉ በፊት ከተናገረው በቀር ሌላ በየትም ስፍራ ይህን አገልግሎት ጥምቀት ብሎ አልጠራውም። በሐዋ. 1፡5 ላይ ብቻ በመንፈስ ቅዱስ እስኪጠመቁ ድረስ በኢየሩሳሌም እንዲቆዩ አሳስቦአቸዋል። ወመንፈስ ቅዱስ በደቀ መዛሙርቱ ላይ በወረደ ጊዜ ግን በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ እንጂ ተጠመቁ አልተባለም (የሐዋ. 2፡4)። በሐዋርያት ሥራ 2 ላይ የመንፈስ ቅዱስ በሰው ልብ ውስጥ ማደር የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ሙላት በአንድ ጊዜ ስለ ተፈጸመ የማንኛውም ክርስቲያን ልምምድ ስእነዚህ ምዕራፎች የተገለጸውን ስለመከተሉ እነዚህን ጥቅሶች በማስረጃነት እንዳናቀርብ መጠንቀቅ አለብን። በቀረው የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ጥምቀት የሚለው ቃል ለውኃ ጥምቀት እንጂ ለመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት አገልግሎት አልዋለም። ሆኖም ግን በአዲስ ኪዳን ውስጥ በድነት (ደኅንነት)፥ በውኃ በመጠመቅና መንፈስ ቅዱስን በመቀበል መካከል እጅግ የቀረበ ዝምድና አለ። (ቲቶ 3፡5 ተመልከት።) ውጫዊ ሥርዓት የሆነው የውኃ ጥምቀት የኃጢአት መታጠብን ብቻ ሳይሆን መንፈስ ቅዱስ መቀበልንም ያሳያል።  ታዲያ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት የሚያመላክተው ምንድን ነው? ስለ መንፈስ ቅዱስ የማጥመቅ ሥራ የተጠቀሰው ጥቂት በመሆኑ ይህን የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት ለመረዳት ስለ መንፈስ ቅዱስ የሚያወሳውን ሰፊ የአዲስ ኪዳንን ትምህርት መረዳት አለብን። «የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት» አንድ ሰው በሚድንበት ጊዜ ስለሚፈጸሙ ሁለት የተያያዙ የመንፈስ ቅዱስን አገልግሎቶች ለማመልከት የተጠቀሰ ነው።  1. የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ ክርስቲያን በልቡ እንዲኖር የሚሰጠውን የመንፈስ ቅዱስ ህልውና የሚያመለክት ነው።  የአዲስ ኪዳን ትምህርት ይህ መሆኑን የምናምንባቸው ምክንያቶች ቀጥለው ተዘርዝረዋል።  ሀ. የብሉይ ኪዳን ተስፋ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ለእግዚአብሔር ሰዎች በሙሉ እንደሚሰጥ ነው። ኢሳ. 32፡15፤ 44፡3፤ ሕዝ 36፡25፥ 27፤ 39፡28-29ና ኢዩ 2፡28። እነዚህ ጥቅሶች ሁሉም መንፈስ ቅዱስ በእግዚአብሔር ሰዎች ሁሉ ላይ እንደሚፈስስ ይናገራሉ።  ለ. መጥምቁ ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረው ትንቢት ሰዎችን ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ እንደሚያጠምቅ ነበር (ማር. 1፡8)። ይህ የኢየሱስ አገልግሎት ሰዎችን ከኃጢአታቸው ከሚያጥብበት? አገልግሎቱ ጋር የተቆራኘ ነው። ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ሲናገር የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ ‹የእግዚአብሔር በግ› መሆኑን እና በመንፈስ ቅዱስ የሚያጠምቅ መሆኑን ገለጸ (ዮሐ 1፡29፥ 33)። ስለዚህ ኢየሱስ ለሚያምኑት ሁሉ የሚሰጠው ሁለት ዋና አገልግሎቶች ሰዎችን ከኃጢአታቸው ማንጻትና በመንፈስ ቅዱስ ማጥመቅ ናቸው።  ሐ. ኢየሱስ መንፈስ ቅዱስን እንደሚሰጥ ተስፋ የሰጠው አንዱን ከሌላው ሳይለይ ለደቀ መዛሙርት በሙሉ ነው (ዮሐ 14፡16-18፤ የሐዋ. 1፡5፡8)። ኢየሱስ ሲናገር መንፈስ ቅዱስ ስጦታ እንጂ በጥረታቸው የሚያገኙት ነገር እንዳይደለ ገልጿል። የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ኢየሱስ በጰንጠቆስጤ ዕለት መንፈስ ቅዱስን ሲሰጥ ደቀ መዛሙርትን በመንፈስ ቅዱስ ከማጥመቅ ጋር አንድ ዓይነት ነገር ነበር ያደረገው ብለው ያስባሉ። እነዚህ ጸሐፊዎች ለክርስቲያኖች ይሰጣል ብለው ያሰቡት የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ እንደሚያጠምቃቸው ቃል ከገባው የተለየ እንደነበር የሚያመለክት ነገር ፈጽሞ የለም።  መ. ሐዋርያት ኢየሱስ የጀመረው አዲስ ኪዳን እነዚህ ሁለት ዋና ስጦታዎች ማለትም ድነት (ደኅንነት)ና መንፈስ ቅዱስን እንደሚያጠቃልል ተረድተው ነበር። ጳጥሮስ በጰንጠቆስጤ ዕለት መንፈስ ቅዱስ ከወረደባቸው በኋላ በሰበከው ስብከት ሰዎችን እንዲያምኑ ሲያነሣሣቸው እናያለን። በእምነታቸውም ሁለት ዋና ዋና ስጦታዎች እንደሚቀበሉ ተናገረ። የመጀመሪያው የኃጢአት ይቅርታ ሲሆን፥ ሁለተኛው በእምነታቸው ምክንያት መንፈስ ቅዱስን እንደሚቀበሉ ነው (የሐዋ. 2፡38)። የመጀመሪያዎቹን የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ሁለት ምዕራፍች በጥንቃቄ ብናጠና «የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ተስፋ» (የሐዋ. 1፡4፤ 2፡33፥ 39)፥ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት (የሐዋ. 1፡5) እና «የመንፈስ ቅዱስ መፍሰስ» (የሐዋ 2፡17፥ 33) የሚያመለክቱት ክርስቲያኖች ስለሚቀበሉት መንፈስ ቅዱስ ነው። ለዚህ ነው ቆርኔሌዎስ መንፈስ ቅዱስን እንዴት እንደተቀበለ ሲናገር ጴጥሮስ የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ መቀበልና በመንፈስ ቅዱስ መጠመቅ ብሎ የተናገረው (የሐዋ. 11፡16-17)።  ሠ. ሐዋርያትም የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ለተወሰኑ ሰዎች ሳይሆን ለክርስቲያኖች ሁሉ መሆኑን ተረድተው ነበር። በብሉይ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ የሚወርደው በተወሰኑ ሰዎች ላይ እንደ ነበር ተመልክተናል። በአንዳንድ መሪዎች ላይ ሲወርድ በሌሎች ላይ አይወርድም ነበር። የሚመጣው ለተወሰነ ጊዜ ስለነበር የእግዚአብሔር ዓላማ ሊጠናቀቅ ወይም ሰውዬው ከፍተኛ ኃጢአት ሲያደርግ ትቶት ይሄድ ነበር። በኢዩኤል 2፡28 ላይ ግን እግዚአብሔር መንፈሱ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ እንደሚሆን አንድ ተስፋን ሰጠ። ሁሉ የሚለው ቃል በምድር የሚኖሩቱን ሁሉ የማያምኑ ሰዎችንም ጭምር የሚያጠቃልል ሳይሆን የእግዚአብሔር ቤተሰብ አባል የሆኑትን ሰዎች በሙሉ ለማለት ነው። መንፈስ ቅዱስ ዕድሜ፥ ፆታ፥ ሥራ፥ ዘር ሳይለይ በሰዎች ሁሉ ላይ ስለመውረዱ የሚናገር ነው። ስጳንጤቆስጤ ዕለት ጰጥሮስ ሲሰብክ ይህ የተስፋ ቃል መፈጸሙን በመግለጽ፥ አሁን የሚያምን ሁሉ እግዚአብሔር በኢዮኤል በኩል የሰጠውን የተስፋ ቃል ሊቀበል ይችላል አለ። ኢየሱስን በሚያድን እምነት የሚቀበሉ ሁሉ የመንፈስ ቅዱስን ተስፋ ቃል ይቀበላሉ (የሐዋ. 2፡38-39)።  ረ. በጰንጠቆስጤ ዕለት ሦስት ሺህ ሰዎች ሊያምኑና ሲጠመቁ በመንፈስ ቅዱስ ላለ መጠመቃቸው የተነገረ ቃል የላም። ሆኖም [ጴጥሮስ በስብከቱ መንፈስ ቅዱስ በሁላቸውም ላይ እንደሚወርድ ተናግሮ ስለነበር] መንፈስ ቅዱስን እንደተቀበሉ እናምናለን። አንዳንዶች ተቀበሉ ሌሎች ደግሞ እልተቀበሉም ተብሎ የተነገረ ቃል የለም። ወይም ደግሞ በሌሎች ደቀ መዛሙርት እንደሆነ ሦስቱ ሺህ ሰዎችም የእሳቱ ነበልባል በላያቸው ላይ እንደነበረና በልሳን እንደተናገሩ አልተጠቀሰም። ይልቁኑ . ያመኑትና የተጠመቁት ሁሉ ሳመኑበት ቅጽበት መንፈስ ቅዱስን እንደተቀበሉ እንድናምን እንገደዳለን። ከተወሰነ ጊዜ በኋላ መንፈስ ቅዱስን ተጠባብቀው እንዳገኙ የሚናገር ቃል የለም። በእርግጥ 120 ዎቹ ሰዎች መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉት በመጀመሪያ ካመኑ በኋላ ነበር። (ይህ የሆነበት ምክንያት እነርሱ ቀደም ብለው አምነው ስለነበርና መንፈስ ቅዱስ ደግሞ እስከ ጰንጠቆስጤ ቀን ድረስ ገና ስላልተሰጠ ነበር።) ሦስቱ ሺህ ሰዎች ግን መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉት እንዳመኑ ነበር። ለ120 ዎቹ ሰዎች መጀመሪያ አምነው ከዳኑ በኋላ ቆይተው መንፈስ ቅዱስን መቀበላቸው ልዩ ሁኔታ ነበር። ሦስቱ ሺህ ሰዎች መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉበት መንገድ እግዚአብሔር በዘመናት ሁሉ ለሰው ልጅ የሚጠቀምበት መንገድ ነው። ይኸውም መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉት ባመኑበት ቅጽበት መሆኑ ነው።  2. የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት አሱን ክርስቲያን ዓለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን ወደሆነችው ወደ ክርስቶስ አካል ይጨምራል። በአብዛኛው ጊዜ ‹ጥምቀት› የሚለው ቃል በአዲስ ኪዳን ክፍሎች የተጠቀሰው የውኃ ጥምቀትን ለማመልከት ቢሆንም ስለ መንፈስ ቅዱስ ጥምቀት በግልጽ የተጠቀሰበት ሌላ ስፍራ እለ። በ1ኛ ቆሮ. 12፡3 «አንድ አካል እንድንሆን ተጠምቀናል» የሚል ቃል እናገኛለን። ከዚህ ጥቅስ የሚከተሉትን እውነቶች መመልከት እንችላለን።  1. ጳውሎስ የሚናገረው የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች በሙሉ በመንፈስ ቅዱስ እንደተጠመቁ ነው። እንዳንድ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች እንዳልተጠመቁ የሚያመለክት ነገር የለም። የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት በክርስቲያን መንፈሳዊነት ላይ የሚመሠረት ስለመሆኑም የተነገረ ነገር የላም። የቆሮንቶስን አማኞች ሁኔታ ብናጠና ቤተ ክርስቲያኒቱ ንጹሕና ቅዱስ አልነበረችም። በክርስቲያኖች መካከል ክፍፍሎች ነበሩ። አንዳንዶቹ

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት) Read More »

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

(ማስታወሻ፡- ለሚቀጥሉት በርካታ ትምህርቶች የሚሆኑት መረጃዎች በአብዛኛው የተገኙት የኤስ አይ ኤም ሚሲዮናዊና የኢቫንጀሊካል ሥነ መለኮት ኮሌጅ ዳይሬክተር ክሆነው ከስቲቭ ስትራውስ የክፍል መማሪያ ማስታወሻ ሲሆን የተጠቀምኩባቸውም በእርሱ ፈቃድ ነው።)  አዲስ ኪዳን ስለ ሁለቱ አገልግሎቶች ማለትም ስለ መንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ላለ መንፈስ ቅዱስ ሙላት የሚያስተምረውን ትምህርት ግልጽ ለማድረግ በሁሉም የአዲስ ኪዳን ክፍሎች ውስጥ የሚገኙ ትምህርታችን ማየት አለብን። በመጀመሪያ አዲስ ኪዳን በአጠቃላይ የሚያስተምረውን በመመልክት እንጀምርና ቀጥሎ ለጰንጠቆስጤ የሥነ መለኮት ትምህርት ምንጭ በሆነው በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ላይ እናተኩራለን።  ጥያቄ፡- የሚክተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። የሐዋ. 2፡42። 5፡24፤ 1ኛ ጢሞ. 4፡13፤ 2ኛ ጢሞ 3፡16። መጽሐፍ ቅዱስ ለምናምነውም ሆነ ለምናስተምረው ትምህርት ማዕከላዊ መሆን እንዳለበት እነዚህ ጥቅሶች እያንዳንዳቸው ምን ያስተምሩናል?  በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተለይም በፍጥነት በምታድግ ቤተ ክርስቲያን እጅግ አደገኛ ከሆኑ ነገሮች አንዱ ብዙ ክርስቲያኖች በእግዚአብሔር ቃል ጥልቅ መሠረት የሌላቸው መሆኑ ነው። እምነታቸውና ተግባራቸው የሚመነጨው ከእግዚአብሔር ቃል አይደለም። ነገር ግን ከባሕላቸው፥ ከቤተ ክርስቲያን ወግና ልምድ ወይም በቪዲዮ ከተመለከቱትና በቴፕሪኮርደር ከሰሙት ነው።  ጥያቄ፡ ይህ ነገር በቤተ ክርስቲያን ሲፈጸም እንዴት እንዳየህ ግለጽ።  ይህ በጣም አደገኛ የሆነው ለምንድን ነው? በአዲስ ኪዳን በተደጋጋሚ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሐሰተኛ አስተማሪዎችና ሐሰተኛ ትምህርት እንደሚኖር ተነግሮናል (ለምሳሌ፡- የሐዋ. 20፡29-31)። የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት አብዛኛዎቹ የተጻፉት የተሳሳቱ አሳቦችንና የተሳሳቱ ትምህርቶችን ለመዋጋት ነው። ለምሳሌ– የገላትያ መጽሐፍ የተጻፈው የእይሁድ ሕጎችን በአሕዛብ ክርስቲያኖች ላይ ለመጫን የጣሩትን ለመዋጋት ነበር። 1ኛ ቆሮንቶስ የተጻፈው ክርስቲያኖችን በልሳናት ከመናገር ጋር የተያያዘውን ሐሰተኛ አካሄድ ጨምሮ የተለያዩ ኃጢአቶቻቸውን፥ የተሳሳቱ ትምህርቶቻቸውንና ልምምዳቸውን እንዲያስተካክሉ ለማቅናት ነበር። ጸሐፊዎቹ ስተው የሄዱትን ክርስቲያኖች ይመለሱና ይስተካክሉ ዘንድ ቸርነት የሞላበት ተግሳጽ የሰጡ ቢሆኑም፥ በግልጽና በድፍረት ለእውነት ቆመዋል። እውነትን ለፍቅር ብለው ለመለወጥ ፈቃደኛ አልነበሩም። (ፍቅርን ያጎድላላል ብለው እውነትን ከመናገር ዝም አላሉም።) ስምምነት ከመጣ በማለት ዛሬ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የማይመስል ነገርን ቢጠየቁ በዘመናችን የመጽሐፍ ቅዱሳቸውን ትምህርት እንደሚያቃልሉ እንደ ብዙዎች አይደለም።  የወንጌልን እውነት ከመጠበቅ ይልቅ ከሌላው ክርስቲያን ጋር ወይም ከሌላው ቤተ ክርስቲያን ጋር ሰላምን መጠበቅ ይመርጣሉ። የቅናት መንፈስና ሌላውን ክርስቲያን በንግግር ማጥቃት ትክክል አይደለም። እውነትን ለማወቅና ትምህርቶችን ሁሉ በእግዚአብሔር ቃል እውነት መርምሮ መፈረጅ ግን እግዚአብሔር ከእኛ የሚጠብቀው ነገር ነው። የቤርያ ክርስቲያኖች የተመሰኑት ማናቸውንም አዲስ ትምህርት ከእግዚአብሔር ቃል ጋር የሚስማሙ መሆናቸውን ሳያረጋግጡ ለመቀበል ፈቃደኞች ስላልነበሩ ነው (የሐዋ. 17፡11)። ማንኛውም ክርስቲያን የእግዚአብሔርን ቃል በተለየ መንገድ በመረዳቱ ከእኔ ጋር ባይስማማ ግድ የለኝም። በኢትዮጵያ ላለች ቤተ ክርስቲያን ችግሯ የሚመነጨው መጽሐፍ ቅዱስን ለእምነታቸው ዋና መለኪያ ለማድረግ፥ እና ሌሎች ደግሞ አዳዲስ እምነቶችን ከመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት አኳያ እንዲመረምሩ ከማይፈቅዱ ሰዎች ነው። ጳውሎስ ጢሞቲዎስን ሲመክረው «የእውነትን ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሳፍር ሠራተኛ እንዲሆን ይነግረዋል (2ኛ ጢሞ 2፡15)። ይህን በአእምሮአችን አድርገን የሚቀጥሉትን ሦስት ቀናት ስለ መንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ስለ መንፈስ ቅዱስ ሙላት ምን እንደሚያስተምር ለማወቅ መጽሐፍ ቅዱስን እናጠናለን።  ጥያቄ፡- ሀ) አሳባቸው ወይም ልምምዶቻቸው በእግዚአብሔር ቃል ብርሃን እንዲመረመር የማይፈልጉ ሰዎችን በምሳሌነት ጥቀስ። ለ) ይህ አደገኛ የሚሆነው ለምንድን ነው? ሐህ ለእምነቶችና ለልምምዶች የእግዚአብሔር ቃል መመዘኛ የማይሆን ከሆነ ሌሎች ምን መመዘኛዎች ይኖራሉ? ሐህ እነዚህ መመዘኛዎች ምን ያህል አስተማማኝ ናቸው?  የእኔ አመለካከት እምነታችሁ ላይ የሚያደርገውን ተጽእኖ ለመገደብ ስላ እነዚህ ሁለት የመንፈስ ቅዱስ ሥራዎች የሚናገሩ የአዲስ ኪዳን ዋና ዋና ክፍሎችን በጥንቃቄ በመመልክት ትጀምሩና አዲስ ኪዳን ስለ እነዚህ ጉዳዮች ምን እንደሚያስተምር ላራላችሁ ለመወሰን ትሞክራላችሁ።  1. የመንፈስ ቅዱስ በሰው ልብ ማደር  ጥያቄ፡– መንፈስ ቅዱስ በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ስለመኖሩ የሚናገሩትን የሚከተሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አንብብ። ዮሐ 7፡37-39፤ ሮሜ. 8፡9፤ 1ኛ ቆሮ. 6፡19፤ ቲቶ 3፡5-6። በእነዚህ ጥቅሶች በእያንዳንዳቸው፡- ሀ መንፈስ ቅዱስ ላላቸው ሁሉ ሊሰጣቸው ቃል የተገባላቸውን በረከቶች ዘርዝር። 2) ክእነዚህ ጥቅሶች መንፈስ ቅዱስ የሚሰጠው ለጥቂት ክርስቲያኖች ወይም ለሁሉም ላለመሆኑ ምን ማስረጃ አለ? 3) እነዚህ ጥቅሶች መንፈስ ቅዱስ ስለሌላው ሰው በግልጽ የሚናገሩት አሊያም የሚጠቁሙት ነገር ምንድን ነው? 4) መዝገበ ቃላት በቤትህ ካለ ስለ መንፈስ ቅዱስ በሰው ልብ ውስጥ የማደር አገልግሎት ምን እንደሚል በአጭሩ አቅርብ።  2. የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት  ጥያቄ፡- በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ስለሚሆነው የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት የተጻፉትን የሚከተሉትን ጥቅሶች አንብብ። ማቴ. 3፡11፤ የሐዋ. 1፡5፤ 2፡1-4፤ 16-21፥ 33፥38-39፤ 11፡15-17፤ 1ኛ ቆሮ. 12፡13። ሀ) ለእነዚህ ጥቅሶች በሙሉ የሚከተሉትን ጥያቄዎች መልስ። ) እነዚህ ጥቅሶች ስለ መንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ምን ይላሉ? 2) እነዚህ ጥቅሶች የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት መቼ እንደሚሆን ይናገራሉ? ሰው በሚድንበት ጊዜ ወይስ ከዳነ በኋላ? 3) በመንፈስ ቅዱስ የሚጠመቁ ክርስቲያኖች ሁሉ ናቸው ወይም አንዳንድ ክርስቲያኖች ብቻ? 4) የግሡን ጊዜ ልብ በል። ቃሉ የሚያመላክተው የወደፊትን፥ ያላፈን ወይስ ሁልጊዜ ተደጋግሞ የሚፈጸምን ድርጊት ነው? 5) የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ልናደርገው የታዘዝነው ነገር ነው ወይስ እንደ ስጦታ የተደረገልን ነገር ነው? ሊ አዲስ ኪዳን ስለ ክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ያለውን አመለካከት በአጭሩ ጻፍ። ህ የመንፈስ ቅዱስ ጥመቀት ዓላማ ምንድን ነው? 2) ጥምቀቱ የሚካሄደው መቼ ነው? 3) የመንፈስ ቅዱስን ጥምቀት የሚቀበል ማን ነው? 4) የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትን የምንቀበለው እንዴት ነው? 5) የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት የሚረጋገጠው በምንድን ነው? የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ማረጋገጥ ይህ ብቻ ነውን? አስረዳ። 6) የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ካለህ ስላ መንፈስ ቅዱስ ጥምቀት አገልግሎት ምን እንደሚል በአጭሩ ጻፍ።  3. የመንፈስ ቅዱስ ሙላት  ጥያቄ፡– መንፈስ ቅዱስ በክርስቲያን ሕይወት ስላለው የሙላት አገልግሎት የሚናገሩትን የሚከተሉትን ጥቅሶች አንብብ። የሐዋ. 2፡11፤ 4፡8፣ 31፤ 9፡17፤ 13፡8–11፤ ኤፌ. 5፡8። ሀ) ለእያንዳንዱ ጥቅስ የሚከተሉትን ጥያቄዎች መልስ። ህ ስለ መንፈስ ቅዱስ ሙላት እነዚህ ጥቅሶች ምን ይላሉ? 2) እነዚህ ጥቅሶች መንፈስ ቅዱስ የምንሞላው መኝ ነው ይላሉ? ሰው በሚድንበት ወቅት ወይስ ከዳነ በኋላ? 3) በመንፈስ ቅዱስ የሚሞሉ እንዳንድ ክርስቲያኖች ናቸው ወይስ ሁሉም? 4) የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (አገልግሎት በክርስቲያን ሕይወት እንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ብቻ የሚፈጸም ወይስ በተደጋጋሚ የሚሆን ነው? ስለ መንፈስ ቅዱስ ሙላት ብቸኛ የሚናገረውን የግሥ ጊዜ ስታጤን፥ የሚያመለክተው የወደፊት፥ ያላፈ ወይስ ተደጋጋሚ ድርጊትን ነው? 6) በመንፈስ ቅዱስ እንድንሞላ ታዘናል ወይስ እንዲሁ የሚደረግልን ነገር ነው?  ለ. አዲስ ኪዳን ክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ ሙላትን ስለሚያገኝበት ሁኔታ በሚያስተምረው ትምህርት ላይ ያለህን አመለካከት አጠር አድርገህ ጻፍ። ) የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ዓላማ ምንድን ነው? 2) ክርስቲያን መንፈስ ቅዱስን የሚሞላው መቼ ነው? 3) የመንፈስ ቅዱስ ሙላትን ማን ይቀበላል? 4) ሰዎች የመንፈስ ቅዱስ ሙላትን የሚቀበሉት እንዴት ነው? 5) የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የሚረጋገጠው እንዴት ነው? ይህ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ማረጋገጥ ነውን? 6) የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት በቤትህ ካለ ስለ መንፈስ ቅዱስ ሙላት አንብብና የተረዳኸውን አሳጥረህ ጻፍ።  ጥያቄ፡- የመንፈስ ቅዱስን በሰው ልብ ማደር፥ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀኛንና የመንፈስ ቅዱስ ሙላትን አወዳድር። ሀ) ተመሳሳይ የሆኑት እንዴት ነው? ለ) የሚለያዩትስ እንዴት ነው? ሐህ በእያንዳንዳቸው መካከል ያለውን ልዩነት በአንድ ዐረፍተ ነገር አጣቃለህ ጻፍ።  ቃላት ልዩ ነገሮች ናቸው። ዘወትር የምንጠቀምባቸው ሊሆኑ ያሉንን አሳቦች ለሌሎች ለማካፈል የምንጠቀምባቸው ዋነኛ መንገድ ናቸው። ሆኖም ግን ቃላት ጠቃሚ የሚሆኑት በምንጠቀምባቸው ጊዜ በትርጉማቸው የምንስማማ ከሆነ ነው። የሚናገሩት ነገር ለሌሎች ሰዎች የሚገባቸው እየመሰላቸው ብዙ ጊዜ አንድ ቃልን ይጠቀማሉ። ነገር ግን ሌሎች ሰዎች ስለ ቃሉ ያላቸው መረዳት ሙሉ በሙሉ የተለየ ስለሆነ ወደ አድማጮቹ የሚደርሰው ተናጋሪዎች ሊሉት የሚፈልጉት ነገር አይደለም። ስለዚህ አንድን ነገር በግልጽ ለማስረዳት ከፈለግን የሚሰሙን ሁሉ የምንጠቀምበትን ቃል ባሰብነው መንገድ መረዳታቸውን ማረጋገጥ አለብን።  ብዙ ክርስቲያኖች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስላሉ እውነቶች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ) Read More »

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች በክርስቶስ ወንድሞቼና እህቶቼ ናቸው። አንድ ቀን በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት አብረን ኢየሱስን እናመልካለን። ነገር ግን «እውነትን በፍቅር…» (ኤፌ. 4፡5) እንድንይዝ ስለተነገረን በፍቅር መንፈስ የካሪዝማቲክ ሥነ መለኮት ትምህርት በሚከተሉ ሰዎች ላይ ያለኝን አሳሳቢ ነገር እገልጻለሁ። ሕይወታችን መጽሐፍ ቅዱስ ለሚያስተምራቸው ትምህርቶች የተገዛ እንዲሆን ሁላችንም ለእውነት ሊገደን እንደሚገባ አምናለሁ። በአሁኑ ጊዜ በየቤተ ክርስቲያናችን የምናያቸው ልምምዶች የመጡት እውነትን ለማወቅና በእውነት ለመኖር ከመነጨ ፍላጎት ሳይሆን በሌሎች አደገኛ ምክንያቶች ነው። አብዛኛው ስጋቴ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች በሚያስተምሩት ነገር ሳይሆን ምንም ዓይነት መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት በሌላቸው በየቤተ ክርስቲያኑ ተዘውትረው በሚታዩ ሚዛን-የለሽ ልምምዶች ላይ ነው። አንድ በሙላት የተገነዘብኩት ጉዳይ ሁሉም ቤተ ክርስቲያኖች በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ሚዛን ያጡ መሆናቸውን ነው። አንዳንድ እብያተ ክርስቲያናት የእግዚአብሔርን ቃል በማጥናት ላይ ብቻ ስለሚያተኩሩ ሕይወት ያለው እምልኮ ስለማቅረብ ደንታ እይሰጣቸውም። በእርግጥ ቀጥሎ የሚጠቀሱት እንዳንዶቹ ነገሮች አጠቃላይ አሳቦች ስለሆኑ ለሁሉም ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች የሚሠሩ ናቸው ማለት አይደለም። ሆኖም ግን አጠቃላይ አሳቦች የአንድን ሥነ መለኮት ትምህርት መሠረታዊ ባሕርይ ለመረዳት ይጠቅሙናል። በኢትዮጵያ ውስጥ አክራሪ ጫፎች እየተከሰቱ ባሉበት በአሁኑ ጊዜ እራሳቸውን ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ብለው የሚጠሩትም ሆኑ ካሪዝማቲክ ያልሆኑት በእምነታቸው በተግባራቸው ሚዛናዊ መሆን አለባቸው። ቀጥሎ በአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች አብያተ ክርስቲያናት ይታያሉ ብዬ የማምነውን ደካማ ጎኖች እዘረዝራለሁ።  1. ካሪዝማቲክ የሆኑም ሆኑ ያልሆኑት ክርስቲያኖች መንፈሳዊ ትዕቢት በማሳየት አዝማሚያ ላይ ናቸው። ካሪዝማቲክ ያልሆኑት እመለካከታቸው እጅግ ትክክልና መጽሐፍ ቅዱሳዊ እንደሆነ በመናገር ትምክህታቸውን ይገልጣሉ። ነገር ግን ካሪዝማቲክ የሆኑት ክርስቲያኖች ደግሞ የተላየ አዝማሚያ የሚያሳዩ ይመስላል። ይኸውም መንፈሳዊ ለመሆንና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ለመመላለስ ካላቸው ፍላጎት የተነሣ እነርሱ በሚያደርጉት ዓይነት መንገድ መንፈሳዊ አካሄዳቸውን ለመግለጽ የማይሹትን በንቀት ማየት ነው። በልሳናት የማይናገሩትን፥ በቤተ ክርስቲያን እምልኮ ጊዜ በማጨብጨብና በእልልታ የማይሳተፉትን በሚጸልዩበት ጊዜ እጆቻቸውን ለማንሣት «ሃሌሉያ» እያሉ የማይጮኹትን መንፈስ ቅዱስ የላቸውም በማለት ይንቋቸዋል። በመካከላቸው ያለውን ልዩነት ከመቀበል ይልቅ ክርስትናን እነርሱ በሚገልጡበት መንገድ እንዲቀበሉ ካሪዝማቲክ የሆኑት ካሪዝማቲክ ባልሆኑት ላይ ከፍተኛ ግፊት ያደርጋሉ። ይህ ዝንባሌ ብዙውን ጊዜ እያንዳንዱ ክርስቲያን መንፈሳዊ ሆኖ ለማየት እንፈልጋለን በሚል ቋንቋ የተለበጠ ቢሆንም፥ እንኳ እውነቱ ግን፥ ሌሎች መንፈሳዊ እንዳልሆኑ እነርሱ ግን ምን ያህል መንፈሳዊ እንደሆኑ ለማሳየት የሚደረግ ጥረት የመንፈሳዊ ትዕቢት ምልክት ነው። ኢየሱስ ስለዚህ ዝንባሌ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ «አትፍረዱ…ይፈረድባችኋል» ብሏል (ማቴ. 7፡1-2)። በአንድ ሰው ልብ ውስጥ በእርግጥ ምን እየሆነ እንዳላ ደግሞም መንፈሳዊ መሆንና ያለመሆኑን ለማወቅ ስለማንችል በራሳችን የመንፈሳዊነት መመዘኛ በሌሎች ላይ እንዳንፈርድ መጠንቀቅ አለብን።  2. በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚታዩ አንዳንድ ስሜታዊ የሆኑ የአምልኮ ልምምዶች እውነተኛ የእምነት ወይም የአምልኮ መግለጫ ሳይሆኑ ሌሎችን የመቅዳትና በሌሎች ፊት መንፈሳዊ ሆኖ የመታየት ዘይቤዎች ናቸው። እግዚአብሔርን በማምለክ ላይ ከማተኮርና ለእኛ ጤናማ በሚመስለን መንገድ አምልኮአችንን ከመግላጽ ይልቅ ትኩረታችን የሚጎላው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሌሎች ሰዎች ስለ እኛ ምን ያስባሉ ሰሚለው ላይ ነው። አንድ ሰው «ሃሌሉያ» ብሎ ከጮኸ የሚቀጥለው ሰው የበለጠ መጮህ አላበት። እንዲት ሴት እጇን ካነሣች ሌላኛዋ ደግሞ መንፈሳዊ ሆና ለመታየት ክመጀመሪያይቱ ሴት ቀድታ ይህንኑ ማድረግ አለባት። አንዱ የመዘምራን ጓድ መዝሙሩን በማሸብሸብና በስግደት ካሳረገ የሚቀጥለውም መንፈሳዊ ለመምሰል ይህንኑ ማድረግ እንዳለበት ያስባል። ኢየሱስ ይህንን «ግብዝነት» ብሎ የጠራው ሲሆን ምናልባትም ሃይማኖተኛ የሆኑ ሰዎችን ከከሰሰባቸው ኃጢአቶች ይህ ዋነኛው ነበር (ማቴ. 6፡1-18)። አንዳንድ ጊዜ ካሪዝማቲክ ያልሆኑ ክርስቲያኖች አምልኮ ካሪዝማቲኮች በሚያደርጉት መንገድ ካልተፈጸመ በቀር መንፈሳዊ መስሎ አይታያቸውም።  3. የልባቸውን ስሜት ስለሚጠብቁ አምልኮአቸው በአመዛኙ ከልብ ሙላት ከሚፈስስ ትክክለኛ ስሜት የመነጨ አይደለም። ይልቁኑ በልዩ ዘዴዎች የሚቀሰቀስ ነው። አእምሮ መሥራት እስኪሳነውና ስሜት ብቻ እለኪጦዝ ድረስ መዝሙሮች በድግግሞሽ ይዘመራሉ። ማምላክ የምንችለው ስለምንዘምረው መዝሙር አእምሮአችን በንቃት በሚሠራበትና በቃሉ ትርጉም ሐሤትን በምናደርግበት ሁኔታ እንደሆነ አምናለሁ። ሰባኪዎች የሕዝብን ስሜት ለማነሣሣት ያሉትን ዘዴዎች በሙሉ ይጠቀማሉ። ከእነዚህም ጥቂቶቹ ሃሌሉያ ማስጮኽ፥ ለቅሶና ታላላቅ ስሜት ቀስቃሽ ድርጊቶች ናቸው። ይህ ነገር ዘላቂ የሆነ ውጤት ስለማምጣቱ እጠራጠራለሁ። ምክንያቱም ስሜቱ ሲጠፋ እግዚአብሔር የሚፈልገውን ነገር ለማድረግ ያለው መነሣሣት አብሮ ይጠፋል። አእምሮአቸውና ስለ እግዚአብሔር ያላቸው እውቀት የሚረጋጋ ሊሆን ሲገባው ስሜታቸው ካልተጋጋለ ኃጢአትን እንዳደረጉ ወይም ሰይጣን እንዳደናቀፋቸው ያስባሉ። ብዙዎችም እምነታቸውን ይተዋሉ። አንድ ሰው በእግዚአብሔር ቃል ላይ ካልተመሠረተ ስሜቱ የሚያዛልቀው ከእምነት እስከሚወድቅ ድረስ ብቻ ነው። በሮሜ 8፡5-8 ጳውሎስ በመንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ በመንፈስ ፍላጎት ላይ አእምሮአቸውን እንደሚያደርጉ ይናገራል። አእምሮአችን በመንፈስ ቁጥጥር ሥር መዋል አለበት።  4. ብዙ የካሪዝማቲክ አማኞች በመካከላቸው የመንፈስ ቅዱስ ህልውና የመኖሩን መጠን ሊያዩት በሚፈልጉት ተአምራት መጠን ይለኩታል። ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ በተአምራት ላይ ተአምራትን እየጨመረ ብዙ ተአምራት እንዲሠራ ይፈልጋሉ። የፈውስ አገልግሎት ስብሰባዎችን በማዘጋጀት በዚያ ስብሰባ የተገኙትን ሁሉ ተፈውሳችኋል ይላሉ። አስደናቂ ነገር በመካከላቸው ሲፈጸም የማየት ጉጉታቸው እንደ አደንዛዥ ዕፅ ሱስ ይሆንባቸዋል። ከቀላል በሽታ ሰዎች ሲፈወሱ ባለፈው ባዩት ነገር ደስ ብሎአቸው ከሆነ በዚህ ዓመት ደግሞ ሽባ የሆኑ ሰዎች እንዲፈወሱ ይፈልጋሉ። በየዓመቱ አዲስና ልዩ የሆነ ነገር ለማየት ያላቸው ፍላጎት ይጨምራል። እናም ብዙ ክርስቲያኖች ታላላቅና የበለጠ አስደናቂ የሆነ ተአምራት ይጠብቃሉ። የሚጠበቀው ተአምራት እንደታሰበው ካልተፈጸመ ችግሩ የሰውዬው እምነት ማጣት ወይም የኃጢአት መኖር ነው በማለት ይደመድማሉ። እግዚአብሔር ተአምራትን እነርሱ በሚያያዙት መንገድ እንዲሠራ ይፈልጋሉ። መሪዎችን ከሌላው መሪ የበለጠና የላቀ ተአምራት እያደረጉ እንደሆነ በመናገር ሌሉችን መሪዎች ለማጣጣል ይሞክራሉ። የሚያሳዝነው ነገር አንዳንዶቹ ተአምራት ለመሥራት ኃይል እንዳላቸው ለሕዝቡ ላማሳየት ማታለያ ዘዴን ሁሉ መጠቀማቸው ነው።  5. ስለ እጋንንት ህልውና ከሚገባው በላይ ትኩረት ይሰጣሉ። ከቤተ ክርስቲያን አጋንንትን ያስወጣሉ። ራሳቸው ያመጡአቸው ሁሉ እንኳ የአጋንንት ስሕተት እንደሆኑ በመቁጠር እንዲወገዱ ያዛሉ። ሰይጣን ወደ ገሃነም እንዲጣል ክርስቲያኖች ሲጸልዩ ሰምቼአለሁ። ሥልጣን ሁሉ የእርሱ የሆነ ኢየሱስ እንኳ እንደዚህ አልጸለየም። ሰይጣን ወደ ገሃነም የሚጣለው በመጨረሻው ዘመን ብቻ ነው። እግዚአብሔር የሰይጣንን ተግባር እንዲቋቋምልን መጸለይ ብንችልም እርሱንም ሆነ ሌሎች አጋንንትን ወደ ገሃነም የመጣል ሥልጣን የላንም። ያዕቆብ እንኳ ለኃጢአት ሁሉ ተጠያቂው ሰይጣን ነው አላለም፤ በራሳችን ክፍ ምኞትና ፍላጎት የተነሣ ኃጢአት እንደምንሠራ አስተምሮአል (ያዕ. 4፡1-3)።  6. ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ብዙ ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል ቸል የሚሉና ለትክክለኛ አተረጓጐም እምብዛም የማይቆረቆሩ ናቸው። እውነትን ላማወቅና በእውነት ላመኖር ያላቸው ፍላጎት አነስተኛ ነው። የሚማሩት የሚያምኑትና የሚያደርጉት ነገር ሁሉ ግልጽ ከሆነው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ጋር ይጣጣም እንደሆነ ለማረጋገጥ መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናት አይፈልጉም። መንፈስ ቅዱስ ያስተምረናል በሚል ፈሊጣቸው ብዙዎች መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት አይገቡም። መንፈስ ቅዱስ ከሚሰጣቸው እንዱ የማስተማር ስጦታ እንደሆነ ይዘነጋሉ። ነገሮችን ሁሉ ይዳኙበት ዘንድ መጽሐፍ ቅዱስን እንደ ዋነኛ መለኪያ ካልተጠቀሙ በስተቀር እውነት የሆነውን ካልሆነው ለመለየት አንዳችም መንገድ አይኖራቸውም። እንዲህ ከሆነ ደግሞ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ማንኛውንም ነገር ማድረግ የተፈቀደ ነው ማለት ነው። ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ከሆነ ልንጠቀምበት፥ ልናጠናው ደግሞም እውነቶች በሙሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ሊመዘኑ ይገባል። ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ከእግዚአብሔር ዘንድ «መገለጥ። አገኘን ይላሉ። የተቀበሉት መገለጥ ግን በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘን የማይስማማ ሆኖ ይገኛል። ይህ ለእነርሱ ግድ አይሰጣቸውም። ምክንያቱም የእነርሱ መገለጥ ከተጻፈው ከእግዚአብሔር ቃል ጋር አንድ ነው ብለው ስለሚያምኑ ነው። ይህ ማለት ክርስቲያን እውነቱ ምን እንደሆነና ሐሰቱ የቱ እንደሆነ የሚመዝንበት ምንም መንገድ የለውም ማለት ነው። እንደታዘዝነው መናፍስትን መመርመር አንችልም (1ኛ ዮሐ 4፡1)፥ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፥ ይህ ዝንባሌ እየተለወጠ እንደሆነ አምናለሁ። የእግዚአብሔርን ቃል የሚያጠኑ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ቁጥር እየጨመረ ነው። በመሆኑም ከዚህ ቀደም ከነበራቸው አቋማቸው እየተላሳላሱ ነው።  ጥያቄ፡– የካሪዝማቲክ ሥነ መለኮት ትምህርትን የሚያስተጋቡ የአንዳንድ ሰዎችን ዝንባሌ እና ሚዛን-አልባነት እንዴት ታቀርባለህ?  ይህ አባባል እጅግ አጠቃላይ እንደሆነና አጠቃላይ የሆኑ ነገሮች በሚነጋገሩበት ጊዜ ደግሞ ስሕተቶቹ

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች Read More »

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

የካሪዝማቲክ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ላሉ የእምነት ክፍሎች በሙሉ የተጫወተው ሚና በመልካምነቱ እጅግ የሚበዛ እንደሆነ ጥርጥር ሊኖር አይችልም። ዓለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን ካሪዝማቲክ ከሆኑት ክርስቲያኖች ላገኘችው ጥቅም የምስጋና ባለ ዕዳ ናት። በዓለም ዙሪያ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ያደረጉት በጎ ተጽእኖ ቀጥሎ ተዘርዝሮአል።  1. ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ከጌታ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ንቁ የሆነ ሕያው ግንኙነት እንድናደርግ አትኩሮታችንን አድሰውልናል። ለቤተ ክርስቲያንና ለግላሰብ ክርስቲያኖች አደገኛ ከሆኑ አዝማሚያዎች ዋናው በመንፈሳዊ ሕይወት እየቀዘቀዙ መሄድ ነው። በቅዝቃዜያችን እያደግን በሄድን ቁጥር የክርስትና ማዕከል የምናውቀውና የምናምነው ሳይሆን ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነት መሆኑን እንዘነጋለን። ትውፊታችንን፥ የቤተ ክርስቲያን ልምምዶቻችን ወይም ኢኮኖሚያዊ እድገታችንን በመሳሰሉት ላይ እናተኩራለን። ከእነዚህ ነገሮች የትኞቹም በራሳቸው መጥፎ አይደሉም ነገር ግን የእምነታችን ማዕከል አይደሉም፤ የካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ኢየሱሳን በሙሉ ልባችን እንዴት መውደድ እንዳለብንና ከኢየሱስ ጋር ባለን ኅብረት በየቀኑ እንዴት መመላለስ እንዳለብንና ጥሩ ምሳሌ ሆነውናል። በልባችንና በቤተ ክርስቲያናችን የኢየሱስ ህልውና እንዲሰማንና እንደ እንግዶች ሳይሆን እንደ እግዚአብሔር ወዳጆች መመላለስ እንዳለብን ያስተምሩናል።  2. የሕይወት ንጽሕና በመፈለግ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች መልካም ምሳሌዎቻችን ናቸው። ብዙ ጊዜ ከክርስቲያኖች ብዙዎቻችን እግዚአብሔርን የኃጢአት ባሕርያችንን አሸንፈን እንድንኖር እንደሚያስችለን አንተማመንበትም። መንፈስ ቅዱስ እነዚህን የኃጢአት ልማዶቻችንን እሸንፈን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ኑሮ እንድንኖር ኃይል እንደሚሰጠን ከመተማመን ይልቅ ለባሕሪዎቻችን ምክንያት ሰጪዎች እንሆናለን። ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ግን መንፈስ ቅዱስ በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ህልውናውን የሚያሳውቀው ኃይልን በመስጠት ነው ብለው ያስተምራሉ። መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ስለሚኖር የእግዚአብሔር ኃይል በውስጣችን አለ ማለት ነው። ይህ ኃይል መኖሩ የሚረጋገጥበት እንድ መንገድ የኃጢአትን ኃይል በማሸነፋችን ነው። ይህ ኃይል ኃጢአትን ለማሸነፍ ብቻ ሳይሆን ለመመስከርና ለማምለክም ያግዘናል።  3. ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች በአምልኮአቸው ስሜታቸውን ለመግለጥ አይፈሩም። እግዚአብሔር የአእምሮ ብቻ ሳይሆን የስሜት ሰዎች አድርጎ እንደፈጠረን ያምናሉ። በአምልኮአቸው ወቅት ሳይነኩ ማለፍን እይፈልጉም። ለእግዚአብሔር ያላቸውን አምልኮ ለማነሣሣት ስሜቶችን እንደ መሣሪያ ይጠቀማል። ደስታቸውን በነፃነት ይገልጣሉ። ይህም የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን በምንም ዓይነት መንገድ እስከማንገልጽ ድረስ፥ ለሜቶቻችንን ይህ ነው በማይባል ቁጥጥር ሥር አምቀን ከምንይዝ ከብዙዎቻችን ሁኔታ የሚቃረን ነው።  4 ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ትኩረታችንን በጸሎት አስፈላጊነት ላይ እንድናደርግ አድርገዋል። ስለ ጸሎት ዓይነትና መልክ እጅግ አይገዳቸውም፤ ይልቁኑ ጸሎት የክርስትና እምብርት መሆኑን ይገነዘባሉ። ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት የምናደርግበት መንገድ ነው። የኃይል ምንጭ ነው። ለብዙዎች በልሳናት መናገር ይህን ያህል የመንፈስ ቅዱስ ህልውና ማረጋገጥ አይደለም። ይልቁኑ የአምልኮና የጸሎት ሕይወታቸውን ለማጠናከር መሣሪያ አድርገው ይጠቀሙበታል። ምስጋናቸውንና ለእግዚአብሔር ያላቸውን አምልኮ ለመግለጽ ከሁሉ የተሻለ መንገድ እንደሆነ ያምናሉ።  5. ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች አምልኮን አድሰውታል። አብያተ ክርስቲያናት ትርጉማቸውን ወዲያው የሚያጡ የአምልኮ ዘይቤዎችን በመፍጠር ሥርዓት አድርገው ይከተሉአቸዋል። በዚህም አምልኮ ከመድረቁ የተነሣ ሕይወትና ትርጉም ያጣል። እነርሱ ግን አዳዲስ፥ ሕይወት የሞላባቸውን ዝማሬዎች በማከል፥ በተላይ ስሜቶቻቸውን ጨምሮ ሁለመናቸውን ለአምልኮ በመስጠት የእሑድ የእምልኮ ፕሮግራሞች መሆን እንደሚገባቸው አድርገው ከሥረ መሠረታቸው እድሰዋቸዋል። ስለ እግዚአብሔር በርካታ እውነቶችን በመማር አንኳር ፍሬ ነገሮችን ከማየት ይልቅ መሆን እንደሚገባው እሑድ ጠዋት የምንሰበሰብበት ዋና ዓላማ እግዚአብሔርን ለማመስገን መሆኑን በትክክል ይጠቀሙበታል።  6. እያንዳንዱ ክርስቲያን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መሳተፍ ያለበት መሆኑን በማጉላት የአትኩሮት አቅጣጫችንን እንደገና እንድናስተካክል እድርገዋል። ብዙ አብያተ ክርስቲያናት የቤተ ክርስቲያንን ሥራ በሙሉ የመሥራት ኃላፊነት የሰባኪው፥ የወንጌላዊውና የመዘምራኑ ነው በሚል ወጥመድ ውስጥ ይወድቃሉ። እነርሱ ግን መንፈስ ቅዱስ ለእያንዳንዱ ክርስቲያን የሰጠው ስጦታ እንዳለ ስለሚያምኑ ይህን ስጦታውን በንቃት ተግባራዊ ለማድረግ እያንዳንዱ ክርስቲያን በአገልግሎት መሳተፍ እንዳለበት አጥብቀው ያስተምራሉ።  7. ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች በመስጠት ቸርነትን አጐልብተዋል። ብዙ ባሕላዊ ክርስቲያኖች ለእግዚአብሔር ለመስጠት የሚያቅማሙ ሲሆኑ ቢሰጡም እንኳ ለሥርዓት ያህል እጅግ ከፍተኛ በሆነ ጥንቃቄ በማስላት የገቢያቸውን አንድ እሥረኛ (እሥራት) በማቅረብ ብቻ ነው። ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ግን ታላቅ ደስታቸውንና ምስጋናቸውን ለመግለጽ በጸጋ ስትልቅ ቸርነት ይሰጣሉ።  8. ስለ ሰይጣንና አጋንንት ህልውና እውነታና ከእነርሱም ጋር ስለምናደርገው መንፈሳዊ ጦርነት አብያተ ክርስቲያናት በንቃት እንድንገነዘብ የካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ረድተውናል። እነዚህን ኃይላት ለማሸነፍ በሚችለው በክርስቶስ ኃይል ላይ አትኩሮት ያደርጋሉ።  9. ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ሁሉም የእምነት ክፍሎች መንፈስ ቅዱስ ማን እንደ ሆነና በክርስቲያን ሕይወት ላይ እንዴት ተጽዕኖ እንደሚያደርግ እንዲመረምሩ አስገድደዋል። የካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች የመንፈስ ቅዱስን ጉዳይ ሰአትኩሮት እንድንመለከት በሕይወታችንና በአገልግሎታችን የሚሠራውን ሥራ እንደንመረምር እስኪነግሩን ድረስ ብዙ ክርስቲያኖች ይህ የሥላሴ አካል በሕይወታችን ላይ ስላለው ሚና ግድ አልነበረንም። ሆኖም ግን በትምህርታቸው ምክንያት ሁላችንም «መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ምን ይላል? ሕይወት የሞላበትና ኃይል ያለው እምነት ይዤ ለመኖር የመንፈስ ቅዱስን ህልውና በምን ላረጋግጥ እችላለሁ?» የሚሉ ጥያቄዎች ለመጠየቅ ተገደድን።  ጥያቄ፡- ሀ) እነዚህ ዘጠኝ ነገሮች እንዴት የአንተ ሕይወትና የቤተ ክርስቲያንህ አምልኮ አካል እንደሆኑ ግለጥ። ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች Read More »

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

1. ማንኛውም ክርስቲያን ልምምድ ውስጥ ሁለት ደረጃዎች አሉ። የመጀመሪያው፥ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ መቀበል ነው። አብዛኛዎቹ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች የመጀመሪያው ደረጃ ሰውን ክርስቲያን ያደርገዋል በማለት ያስተምራሉ። አብዛኛዎቹ እንደሚያስተምሩት መንፈስ ቅዱስ በዚህ ጊዜ በተወሰነ ደረጃ በዚያ ሰው ሕይወት ውስጥ ያድራል። ይህ አንዳንድ ጊዜ «ለድነት (ደኅንነት) በመንፈስ መወለድ» ተብሎ ይጠራል። ሆኖም ቀን ይህ የመጀመሪያ ደረጃ የተሟላ አይደለም በማለት ያስተምራሉ።  ሁለተኛው ደረጃ ፥ «የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት» ሲሆን፥ ይህ ማለት መንፈስ ቅዱስ ለአንዴና ለመጨረሻ በሆነ መንገድ በኃይል በመምጣት ለአገልግሎት ይቀባዋል ማለት ነው። ይህ ድርጊት በበርካታ የተለያዩ ስሞች የተጠራ ሲሆን አንዳንዶች በመንፈስ መሞላት ይሉታል። ሌሎች ደግሞ «የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ» ይሉታል። በአንድ ወቅት «በመንፈስ መቀባት» ተብሎ ተጠርቷል። መንፈስ ቅዱስ ወደ አንድ ሰው ሕይወት የመምጣቱ ዋና ምልክት በልሳን መናገር ነው። የመንፈስ ቅዱስ ህልውና በልሳናት በመናገር የሚረጋገጥ ቢሆንም የመንፈስ ቅዱስ ተቀዳሚ ዓላማ ክርስቲያኖች ለእግዚአብሔር መኖር ይችሉ ዘንድ በኃይል ማስታጠቅ ነው። ለአንዳንድ ክርስቲያኖች ይህ ድርጊት ልክ በሚድኑበት ቅጽበት የሚፈጸም ቢሆንም ብዙ ጊዜ ግን ከዳኑ በኋላ የሚፈጸም ነው። (ማስታወሻ፡- በአሁኑ ወቅት በልሳን መናገር ለሁሉም ክርስቲያኖች የግድ መሰጠት ያለበት ስጦታ እንዳልሆነ የሚያምኑ የበሰሉ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ቢኖሩም በልሳናት የመናገር እስፈላጊነት የብዙ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች የተለመደ ትምህርት ነው)።  2. መንፈስ ቅዱስ በአሁኑ ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የመኖሩ ክስተት በ1ኛ ቆሮ 12፡8-10 በተዘረዘሩት የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች የሚረጋገጥ ነው ይላሉ። የቤተ ክርስቲያን ጤናማ ሕይወት እንደ ፈውስ ተአምራትና መገለጥ በመሳሰሉ ነገሮች መረጋገጥ አለበት።  ጥያቄ፡- ሀ) ይህንን ትምህርት በአብዛኛው የኢትዮጵያ ከተሞች በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሲሰጥ ያየኻው እንዴት ነው? ለ) ከዚህ ትምህርትና እንቅስቃሴ ለአብያተ ክርስቲያናት የወጡ መልካም ናቸው ብላህ የምታስባቸውን ነገሮች ዘርዝር። ሐ) የዚህ አዲስ እንቅስቃሴ ትምህርቶች ነባቤተ ክርስቲያን ያስከትላሉ የምትላቸው ስጋቶች ምን ምን ናቸው?  ጰንጠቆስጤ ወይም ካሪዝማቲክ ያልሆኑ አብያተ ክርስቲያናት «የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት» አንድ ሰው በክርስቶስ አምኖ በሚድንበት ወቅት ወዲያውኑ የሚፈጸምና አማኙን ወደ ክርስቶስ አካል የሚጨምር ድርጊት እንደሆነ ያስተምራሉ። ሰው በሚድንበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በልቡ ውስጥ መኖር መጀመሩና የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት በአንድነት የሚከናወኑ ናቸው። ከዚህ ሌላ ካሪዝማቲክ ያልሆኑት በልሳናት የመናገርና ተአምራታዊ የመንፈስ ቅቶለ ስጦታዎች ሚና ላይ ልዩነት ያሳያሉ። አንዳንዶቹ እነዚህ ስጦታዎች ለመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን ብቻ የነበሩ፥ ሐዋርያት ሊሞቱና አዲስ ኪን ሲፈጸም ቀርተዋል ብለው ያምናሉ (1ኛ ቆሮ. 13፡8 ተመልከት)። ሌሎች ደግሞ እዚህ ለጦታዎች ዛሬም ቢሆን ለክርስቲያኖች ይሠራሉ ይላሉ። ነገር ን በልሳናት መናገር ከመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች አንደኛው ብቻ ነው። በአዲስ ኪዳን ከተጠቀሱት ከሌሎች የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች በተለየ ሁኔታ ለመንፈስ ቅዱስ ህልውና ማስረጃ አይሆንም። ካሪዝማቲክ ያልሆኑት ክፍሎች ከመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ይልቅ በገላ. 5፡22 ላይ በተጻፉት የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች ላይ ያተኩራሉ። ካሪዝማቲክ የሆኑ አብያተ ክርስቲያናት በመንፈስ ቅዱስ በማምለክ ላይ ሲያተኩሩ፥ ካሪዝማቲክ ያልሆኑት የእግዚአብሔርን ቃል በማወቅና በእርሱ በመኖር ላይ ያተኩራሉ። ካሪዝማቲክ ያልሆኑትን አብያተ ክርስቲያናት ለካሪዝማቲኮች የሚያስጨንቃቸው ነገር የትምህርታቸው መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት እነስተኛ መሆን ነው።  ካሪዝማቲክ የሆኑትም ሆነ ያልሆኑት በታማኝነት እግዚአብሔርን ለማስደሰት እንደሚናፍቁ መገንዘብ አስፈላጊ ነው። አንዱ ከሌላው የሚያንስ ወይም የሚበልጥ መንፈሳዊ የመሆን ጉዳይ አይደለም። ይልቁኑ ጉዳዩ ሁለቱም ቡድኖች የተለያዩ የሥነ መለኮት አመለካከት፥ በተለየ መንገድ መጽሐፍ ቅዱስን መረዳት፥ በተለይ ደግሞ ሰው ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ለሚኖረው ኅብረት የተለየ አመለካከት አላቸው ማለት ነው። እውነታውን ከተመለከትን አንዱ ቡድን ሌላውን የሚያስተምረው በርካታ ነገር አለው። ሁለቱም ቡድኖች ሚዛናቸውን በመጠበቅ ትልቅ ችግሮች ውስጥ እንዳይወድቁ እርስ በርስ መጠባበቅ ይችላሉ። ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ልምምጻቸውን መጽሐፍ ቅዱስ ከሚያስተምረው ትምህርት ጋር ጎን ለጎን ለማስኬድ ይችሉ ዘንድ እምነቶቻቸውን በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ላይ ለማድረግ ማተኮር አለባቸው። ካሪዝማቲክ ያልሆኑት ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስን ሕያው በሆነ መንገድ በመለማመድ እግዚአብሔርን በማምለክ ከተራ የሃይማኖት ሥርዓት እንዲድኑ በዚህ አቅጣጫ አትኩሮት ማድረግ አለባቸው።  ጥያቄ፡- ሀ) ከእነዚህ ሁለት የሥነ መለኮት ትምህርት ቡድኖች የትኛው ውስጥ ትካተታለህ? ይህ የሆነው ለምን ይመስልሃል? ለ) ሁለቱም ቡድኖች በቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ እድገት ውስጥ ሚዛናዊ የሆነ ነገር እንዲኖር አስተዋጽኦ ሊያደርጉ የሚችሉበትን መንገድ በምን ሁኔታ ታየዋለህ? ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው? Read More »

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

በትምህርት 5 እንደጠቀስነው ሁላችንም የመረዳት ችሎታችን እውነትን ወደ አንድ አቅጣጫ ያዘነበለ ነው። ስለ ዝሆን ከፊል የሆነ መረዳት እንደ ነበራቸው እንደ አራቱ ዓይነ ስውራን እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የእምነት ትምህርቶች ላይ ሁላችንም ያላን መረዳት ከፊል ብቻ ነው። ይህ የሆነበትንም ምክንያት ተመልክተናል። ባሕላዊ መሠረታችን የመጣንበት ቤተ ክርስቲያን ዕድሜያችን በጥቅሉ በአማኞች ሕይወት ውስጥ የሚሆነውን የመንፈስ ቅዱስ ሥራ የምንረዳበትን ሁኔታ ይወስናሉ። ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት በጥልቀት የምንመለከተው ጰንጠቆስጤ የሆኑ ክርስቲያኖችና ያልሆኑት በብርቱ የማይስማሙባቸውን ሁለት የመንፈስ ቅዱላ ሥራዎች ነው። እነርሱም «የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት» እና «የመንፈስ ቅዱስ ሙላት» ናቸው።  ጥያቄ፡- ሀ) በመካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያንና በቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን መካከል ያሉትን አንዳንድ የሥነ መለኮት ትምህርት ልዩነቶችን ግለጽ። ለ) በቃላ ሕይወት ቤተ ክርስቲያንና በሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን መካክል ያሉትን አንዳንድ የሥነ መለኮት ትምህርት ልዩነቶች ግለጽ። ሐ) እነዚህ እብያተ ክርስቲያናት በሚያምኑትና በሚለማመዱት ነገር መሠረታዊ ልዩነቶች የሚታዩት ለምን ይመስልሃል? መ) በቤተ ክርስቲያን ታሪክና ተግባር ላይ የሚካሄድ ጥናት እሁን ያሉትን መሠረታዊ የእምነት ትምህርቶች ተግባር ለመመርመር የሚረዳው ለምንድን ነው?  አብዛኛዎቹ የቤተ ክርስቲያን የእምነት ክፍሎች የተፈጠሩት መሪዎቻቸው እንዳንድ እውነቶችን የሚረዱበት መንገድ ከሌሎች የተለየ በመሆኑ ነው። እነዚህን እውነቶች በሥዕላዊ መግላማችን (ትምህርት 5 ተመልከት) ሁለተኛ ክፍል ውስጥ የሚገኙ ናቸው። ይህ ማለት የደኅንነታችንን ጉዳይ የማይነኩና መጽሐፍ ቅዱስ ግልጽ ትምህርት የሚሰጥባቸው ናቸው ማለት ነው። ማርቲን ሉተር ክካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ወጥቶ የሉተራውያንን ቤተ ክርስቲያንን (መካነ ኢየሱስ) የጀመረበት ምክንያቱ የክርስትና እምነት መሠረታዊ ትምህርት ላይ በተለይ ደግሞ በድነት (ደኅንነት) ጉዳይ ላይ ልዩነት ስለተፈጠረ ነው። ላለመገንጠሉ ምክንያት የሆነው በዚያን ወቅት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ግልጽ ከሆነው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ድነት (ደኅንነት) ፈቀቅ ማለት ነበር። በዚህ ሁኔታ መለያዩቱ የመጣው በዋና መሠረታዊ የክርስትና ትምህርት ማለትም በሥዕላዊ መግላማችን በውስጠኛ ክፍል ነበር። ስለሆነም ይህ መለየት እውነተኛውን እምነት ለመጠበቅ ተዚ ነበር። ፕረስቢቴሪያውያን ከሉተራውያኑ ተለይተው ሲወጡ መነሻው በጣም አናሳ በሆነ መሠረታዊ የእምነት ትምህርት ጉዳይ ማለትም እግዚአብሔር ሰውን የሚያድነው እንዴት ነው የሚል ነበር። የጰንጠቆስጤ አብያተ ክርስቲያናት ጰንጠቆስጤ ካልሆኑት ተለይተው የወጡበት ዋና ምክንያት አንዳንድ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶችን በመረዳት ላይ በተፈጠረ ልዩነት ነበር። እነዚህ ልዩነቶች ጴንጠቆስጤ ወይም ካሪዝማቲክ የሆነ የሥነ መለኮት ትምህርት ባላቸውና በሌላቸው መካከል ከፍተኛ ውዝግብን አስከትሏል። ጰንጠቆስጤ (ካሪዝማቲክ) የሥነ መለኮት ትምህርትን በሚከተሉት ዘንድ የሚታየው ክርክር ያተኮረው በመንፈስ ቅዱስ ሙላትና በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት መካከል ያለውን ልዩነት በመረዳት ላይ ነው።  (ማስታወሻ፡- ጰንጠቆስጤ የሚለው ስም የመጣው ከሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 2 ሲሆን በመንፈስ ቅዱስ በደቀመዛሙርት ላይ በኃይል የወረደበት ቀን ነው። ጰንጠቆስጤ የሚለው የግሪክ ቃል ትርጉም አምሳ ማለት ሲሆን የሚያመለክተው አይሁድ ከመቅሰፍቱ ያመለጡበት አምሳኛውን ቀን መታሰቢያ የሚያከብሩትት በዓል ነው።) በኢትዮጵያ ይህ ቃል «ጴንጤ» ተብሎ በእህጽሮት የሚጠራ ሲሆን አንዳንድ ሰዎች በሥነ መለኮት ትምህርታቸው ጴንጠቆስጤ የሆኑትንም ሆነ ያልሆኑትን የወንጌል አማኞች በሙሉ ለማንጓጠጥ ተግባር ይጠቀሙበታል። «ካሪዝማቲክ» የሚለው ቃል ደግሞ የመጣው «የጸጋ ስጦታ» ከሚለው የግሪክ ቃል ሲሆን የሚያመለክተውም በ1ኛ ቆሮ. 12 ላይ የሚገኙትን መንፈስ ቅዱስ ለክርስቲያኖች የሚሰጠውን መንፈሳዊ ስጦታ ነው። ይህ ቃል በአዲስ ኪዳን የሚገኙ መንፈሳዊ ስጦታዎች በሙሉ በተላይ በልሳን መናገርንና ፈውስን ጨምሮ በዚህ ዘመን ለሚገኙ ክርስቲያኖችም ያገለግላሉ የሚለውን የሥነ መለኮት አሳብ ያንፀባርቃል። «ካሪዝማቲክ» የሚለው ቃል በዋና ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆነው (እንደ መካነ ኢየሱስና ቃለ ሕይወት ባሉ) ስለ መንፈስ ቅዱስ ከላይ የተሰጠውን አመለካከት የሚያንጸባርቁ ሰዎችን ያጠቃልላል። ጰንጠቆስጤ የሚለው ቃል ግን ብዙ ጊዜ እንደ ሙሉ ወንጌል ላሉ ቤተ ክርስቲያኖች ሲሆን እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት በእነዚህ ትምህርቶች ላይ በመመሥረት የራሳቸውን የእምነት አቋም የመሠረቱ ናቸው። ሆኖም ግን በተለምዶ አጠቃቀም ካሪዝማቲክ የሚለው ቃል በተለይ የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮትን ለሚከተሉ ሁሉ በስሩት ያገለግላል።  ጰንጠቆስጤ (እንደ ሙሉ ወንጌል ያሉ) ና ጰንጠቆስጤ ባልሆኑ (እንደ መካነ ኢየሱስና ቃለ ሕይወት ባሉ) አብያተ ክርስቲያናት ያለውን የሥነ መለኮት ትምህርት የመረዳት ልዩነት ለመገንዘብ ታሪካዊ አነሣሡን መመልከት እጅግ ጠቃሚ ነው። ስለዚህ በዛሬው ትምህርት የጰንጠቆስጤ የሥነ መለኮት ትምህርት ታሪክና እንደ ሙሉ ወንጌል ያሉ አብያተ ክርስቲያናት እንዴት እንደተቆረቆሩ እንመለከታለን። ከዚያም መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የማጥመቅና የመሙላት ሥራዎች ምን እንደሚል እንመለከታለን። በሚቀጥለው ሳምንት የጴንጠቆስጤ ሥነ መለኮት ትምህርት መሠረት በመሆን የሚያገለግሉትን ዋነኛ ክፍሎች ለመመልከት ወደ ሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ እንመለሳለን።  ከመቶ ዓመት በፊት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚሰጡ ትምህርቶች በመንፈስ ቅዱስ ላይ ያላቸው ትኩረት አነስተኛ ነበር። ይልቁኑ የተለያዩ የእምነት ” ክፍሎች (መካነ ኢየሱስና ቃለ ሕይወትን የመሳሰሉ ቤተ ክርስቲያናት የወጡባቸው) ያተኮሩት ሰው እንዴት እንደሚድን፥ በሥላሴ ህልውና፥ ሰው እንዴት መጠመቅ እንዳለበት፥ ቤተ ክርስቲያን ከመንግሥት ጋር ስላላት ግንኙነት፥ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ወዘተ… አስመልክቶ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በሰፈረው ሥነ መለኮታዊ መሠረታዊ የእምነት ትምህርት ላይ ነበር። በእነዚህ ጉዳዮች ላይ በተፈጠረ ልዩነት እንደ ሉተራን፥ ባፕቲስት፥ ፕርስቢቴሪያን፥ ሜተዲስት የመሳሰሉት ዋና ዋና የእምነት ክፍሎች ተቆረቆሩ። ከርስቲያኖች በመንፈስ ቅዱስ አካላዊ ህልውና ሁልጊ ያመኑ ቢሆንም የትምህርታቸው ዋና አትኩሮት እርሱ አልነበረም።  በታሪክ አኳያ ስንመለከተው እብዛኛዎቹ የእምነት ክፍሎች የሚያስተምሩት መንፈስ ቅዱስ ወደ ክርስቲያን ሕይወት የሚመጣው ክርስቶስ ኢየሱስን እንዳመነ ወዲያውኑ ነው የሚል ነው። በመንፈስ ቅዱስ ላይ በሚሰጡት በዚሁ ትምህርታቸው «ከመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች። ይልቅ «በመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች» ላይ ያተኩራሉ። የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ልዩ በሆነ መንገድ በሕይወታቸው ከመለማመድ ይልቅ በመንፈሳዊ እድገት ላይ ያተኩራሉ። (ማስታወሻ፡— በሌሎች ክርስቲያኖች ዘንድ አመርቂ ተቀባይነት ሳይኖራቸው፥ ስለ መንፈስ ያስተማሩና የመንፈስን ድንቅ እሠራሮች ይሹ የነበሩ አንዳንድ ክርስቲያኖች በዘመናት መካከል ሁልጊዜ ተከስተዋል) ብዙ ጊዜ ትምህርታቸው እጅግ ትንሽ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ስለነበረው ትምህርታቸውና ልምምዳቸው እብዛኛው ክርስቲያን ከተቀበለው ያፈነገጠ ነበር።  ከመቶ ዓመት ወዲህ ግን ይህ ሁኔታ መለወጥ ጀመረና በመንፈስ ቅዱስ ላይ የሚሰጠው ትምህርት አብያተ ክርስቲያናትን ሁሉ አጥለቀለቀ። እነዚህም ትምህርቶች አዳዲስ የእምነት ክፍሎችን ከማስገኘታቸውም በተጨማሪ ቀድሞ በነበሩ የእምነት ክፍሎችም ላይ ተጽዕኖ አሳደሩ። እነዚህን ለውጦች ለመረዳት 50 ዓመታት በታሪክ ወደ ኋላ ሄደን ጆን ዌስሊ የተባለውን ሰው ታሪክ መመልከት ያስፈልገናል።  የዘመናዊው የጰንጠቆስጤ ሥነ መለኮት ትምህርት መሠረት ከ50 ዓመት በፊት የሚኖር (የነበረ) እግዚአብሔርን የሚፈራ ታዋቂ ወንጌላዊ ወደ ነበረው ጆን ዌስሊ ታሪክ የሚወስደን ነው። በአገልግሎቱ በእንግሊዝና በአሜሪካ የሚኖሩ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ሕይወት ተነክቷል። በአገልግሎቱ የተቆረቆረው የእምነት ክፍል ‹ሜተዲስት› የእምነት ክፍል ይባላል። ለጆን ዌስሊ ትምህርት እጅግ መሠረታዊው አሳብ ክርስቲያን በክርስትና ሕይወቱ በሁለት ዋና ልምምዶች ያልፋል የሚለው ነው። በመጀመሪያ፥ የድነት (ደኅንነት) ልምምድ ውስጥ ያልፋል። ይህ ክርስቲያኖች ሁሉ በኢየሱስ ክርስቶስ ሲያምኑ የሚፈጸም ነው። መንፈስ ቅዱስ በክርስቲያኖች ሕይወት ውስጥ ለመኖር የሚመጣውም በዚህ ጊዜ ነው። ሁለተኛው ልምምድ ደግሞ፥ (ሁለተኛ በረከት› በመባል ይታወቃል። ጆን ዌስሊ በብዙ ጸሎት የእግዚአብሔር ኃይል (በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛው የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት በመባል የሚታውቀው) በክርስቲያን ላይ ይወርዳል ብሎ ያስተምር ነበር። በዚያን ጊዜ ክርስቲያን በፍጹም ቅድስና ለመኖር ይችላል። መንፈስ ቅዱስ በአንድ ድርጊት የተሳሳቱ ውስጣዊ እሳቦችን በሙሉ ፈጽሞ በማስወገድ ሰው የተፈጠረለትን ታላቅ ቅድስና ያጎናጽፋል። ይህ ሁለተኛ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጅማሬ ከቁጥጥር ያላፈ ለቅሶ ወይም የሳቅና የደስታ ጩኸት የመሳሰሉ ታላቅ ስሜታዊ ድርጊቶችን ያካትታል።  ኋላም በ1901 ዓም በአሜሪካ የሚኖር የሜተዲስት ሰባኪ ስሙ ቻርልስ ፍክላ ፓርሃም ይባል የነበረ በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ያስተምር ነበር። እርሱና ተማሪዎቹ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍን ሊያጠኑ አንድ ሰው መንፈስ ቅዱስን የመቀበሉ አንድ ማስረጃ በልሳን መናገሩ ነው ብለው እመኑ። በልሳን የመናገር ስጦታ ለመጀመሪያዎቹ ደቀ መዛሙርት ከተሰጠ ከዚያም በኋላ ላሉ ክርስቲያኖች ሁሉ መሰጠት አለበት ይሉ ጀመር። በዚህ ዓይነት የጰንጠቆስጤ የሥነ መለኮት ትምህርት

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ Read More »

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

በኤፌ. 1፡3–14 ጳውሎስ እግዚአብሔር በሰማያዊ ስፍራ ባለ መንፈሳዊ በረከት ሁሉ ክርስቲያኖችን ስለባረከን ያመሰግናል። ባለፉት ሁለት ቀናት ትምህርት በዳንንበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በርካታ በረከቶችን ሕይወትን የሚለውጡ በረከተችን፥ ተአምራዊ በረከቶችን እንደሰጠን እይተናል። ስለሆነም እግዚአብሔር እንድናመሰግነው መፈለጉ የሚያስገርም አይሆንም። ወደ ክርስቶስ በእምነት ስተመለስንበት ቅጽበት መንፈስ ቅዱስ ስለሰጠን በረከቶች በሙሉ አብረን እግዚአብሔርን ከማመስገን ሌላ ምንም ማለት አንችልም።  ጥያቄ፡- የሚከተሉትን ጥቅሶች አንብብ። 2ኛ ቆሮ. 1፡22፤ 5፡5፤ ኤፌ. 1፡13፤ 4፡30፤ ዮሐ 1፡12፤ ሮሜ 8፡13-17፤ ገላ. 4፡5-7፤ 1ኛ ቆሮ. 12፡13። ሀ) አንድ ሰው ገና በሚድንበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ክርስቲያን በሆነው ሰው ውስጥ ስለሚሠራቸው ሥራዎች እነዚህ ጥቅሶች የሚሰጡትን እውነቶች ዘርዝር። ለህ እያንዳንዱ በረከት ስለያዛቸው ነገሮች አጭር መግለጫ ጻፍ።  1. የመንፈስ ቅዱስ ማኅተምና መያዣ (2ኛ ቆሮ. 1፡22፤ 5፡5፤ ኤፌ. 1፡13፤ 4፡30)። በጥንት ጊዜና ዛሬም በኢትዮጵያ ማኅተም በጣም ጠቃሚ ምልክት ነው። የባለቤትነት ምልክት ሆኖ የሚያገለግል ሲሆን፥ አንድ ሰው በአንድ ነገር ላይ ማኅተም ሊያደርግ የዚያ ነገር ባለቤት መሆኑን ያሳያል። (መጻሕፍት ላይ ስማችንን ስንጽፍ የእኛ መሆናቸውን እንደምናመለክተው ዓይነት ማለት ነው።) ደግሞም አንድ ድርጅት ለመንግሥት ወይም ለሌላ ድርጅት በሚልከው ማንኛውም ኦፊሴላዊ ደብዳቤ ላይ እንደሚጠቀምበት ሁሉ፥ ማኅተም የሕጋዊ ሰነዶችን ትክክለኛነት የሚያረጋግጥ ነው። ደብዳቤው ሳይከፈት እንዲደርስ በፓስታው እፍ ማኅተም እንደምናሳርፍ ሁሉ፥ አንድ ሰነድ ያልተለወጠና ሕጋዊ ስለመሆኑ ማኅተም በምልክትነት ያገለግላል። መያዣ ደግሞ የመጨረሻው ክፍያ በሚካሄድበት ጊዜ ሙሉ ባለቤትነት ላይ እንደሚደረስ ዋስትና የሚሰጥ ነገር ነው።  በአዲስ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ ማኅተም እንደሆነ ወይም በአማኙ ላይ ማኅተም የሚያደርግ እንደሆነ ተነግሮናል። ማኅተም የሚደረግበት አማኙ ነው። ማኅተም አድራጊው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን በመጠቀም በሆነ መንገድ እያንዳንዱን ልጁን ያትምበታል። በእግዚአብሔር ማኅተም የሚደረግበት ማን ነው? በአዲስ ኪዳን ውስጥ ክርስቲያኖች ማኅተም እንደተደረገባቸው በተጻፈባቸው ቦታዎች ሁሉ ማኅተሙ የተደረገባቸው ክርስቲያኖች በሙሉ ናቸው። አንዳንድ ክርስቲያኖች ብቻ ማኅተም እንደተደረገባቸው የሚያመለክት ነገር የለም። የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች እንኳ ያ ሁሉ ችግር በቤተ ክርስቲያናቸው እያላ በእግዚአብሔር እንደታተሙ ተጽፎአል። በተጨማሪ ክርስቲያን ይታተምበት ዘንድ እንዲያደርገው የተጠየቀው አንዳችም ትእዛዝ የለም። ለምሣሌ፡- ይታተም ዘንድ መጸለይ የለበትም። ስለዚህ አንድ ሰው በኢየሱስ በሚያምንበት ወቅት ወዲያውኑ መንፈስ ቅዱስ እንደሚያትመው ማሰብ እንችላለን። መንፈስ ቅዱስ በተጨማሪ አሁን በከፊል ሐሴት ለምናደርግባቸውና ወደ መንግሥተ ሰማያት ስንደርስ በሙላት የእኛ ስለሚሆኑት በረከቶች የሚያረጋግጥልን መያዣችን በመሆንም ይሠራል።  አዲስ ኪዳን በመንፈስ ቅዱላ ታትመናል፤ እርሱ ዋስትናችን ነው፤ ሊል ምን ማለቱ ነው? በዚህ የመንፈስ ቅዱስ ተግባር ውስጥ ሦስት ድርጊቶች የተጠቃለሉ ይመስላል።  በመጀመሪያ፥ የባለቤትነት አሳብ አለበት። ማኅተሙ የእግዚአብሔር መሆናችን ማረጋገጥ ነው።  በሁለተኛ ደረጃ ፥ የሥልጣን አሳብ አለው። እንድ ማኅተም ያለው ደብዳቤ ማኅተም ያደረገበትን አካል ሥልጣን የያዘ እንደሆነ፥ ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ ማኅተም በእኛ ላይ መኖሩ የንጉሥ ልጆች ከመሆናችን የተነሣ የእግዚአብሔር ሥልጣን እንዳለን የሚያሳይ ምልክት ነው።  በሦስተኛ ደረጃ ፥ የእግዚአብሔርን ተስፋዎች በሙሉ እንደምንቀበል ማኅተሙ ዋስትና ነው። የእግዚአብሔር ንብረቶች እንደምንሆን ዋስትና የሚሰጥ ነው። በእግዚአብሔር ተስፋ የተገባልንን በረከቶች በሙሉ በተለይም ደግሞ የዘላለም ድነት (ደኅንነት) ተስፋ እንደምንቀበል የሚያረጋግጥ ነው። ብዙ ክርስቲያኖች እንደሚያምኑት ወደ መንግሥተ ሰማይ እስክንደርስ እግዚአብሔር እንደሚጠብቀን ከእውነተኛ እምነት ተሳስተን እንዳንወድቅ እንደሚከልለን የሚያረጋግጥ ዋስትና ነው። እግዚአብሔር የመንፈስ ቅዱስን ማኅተም አንድ ጊዜ ካደረገብን በኋላ ወድቀን ደኅንነታችንን እንድናጣና ከዘላላም ሽልማታችንም እንድንቀር የሚያደርገን እንዳችም ነገር የለም።  ጥያቄ፡– መንፈስ ቅዱስ የሚያትመን የመሆኑ እውነት ዛሬ እንዴት ሊያበረታታን ይገባል?  2. መንፈስ ቅዱስ በእግዚአብሔር ቤተሰብ ውስጥ የልጅነት መብት ሰጥቶናል (ዮሐ 1፡12፤ ሮሜ 8፡13-17፤ ገላ. 4፡5-7)። ከአዲስ ኪዳን አስደናቂ እውነቶች አንዱ በዳንንበት ወቅት እግዚአብሔር ጠላቶቹ የነበርነውን እኛን ልጆቹ ማድረጉ ነው። ይህ ሂደት ማደጎነት ወይም ልጅነትን መቀናጀት ይባላል። በጥንት ጊዜ ሮማውያንና ግሪኮች ልጅ ያልወለዱ ወላጆች የሌላን ሰው ልጅ ወይም የባሪያን ልጅ እንኳ ሰመውሰድ በሕግ የራሳቸው ልጅ ያደርጉ ነበር። ወደ ቤተሰቡ የተጨመረው የማደጎ ልጅ ወዲያውኑ በሥጋ እንደተወለደ እንደማንኛውም ልጅ ሕጋዊ መብቶችን በሙሉ ያገኛል።  ምንም ልዩነት አይደረግበትም። እነዚህ ወላጆች በሥጋ የወለዱት ልጅ ቢኖራቸው የመውረስ ሙሉ መብት እንዳለው ሁሉ ይህም ልጅ ይኖረዋል።  በዳንንበት ቅጽበት መንፈስ ቅዱስ እኛን ወስዶ በእግዚአብሔር ቤተሰብ ውስጥ ያስቀምጠናል። የእግዚአብሔር ልጅ በመሆን የሚገኝ መብት፥ ደረጃ ግዴታዎች በሙሉ ይሰጡናል። ይህ የልጅነት ስፍራችን ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ግንኙነቶች ሙሉ በሙሉ ይለውጣል። ክዚህ ቀደም በፍርሃት ከእግዚአብሔር ርቀን እንዳልነበርን አሁን ግን በሙሉ ልብ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንችላለን። መንፈስ ቅዱስ ያለማቋረጥ የእግዚአብሔር ተወዳጅ ልጆች መሆናችንን ያሳስበናል። ትንሽ ልጅ ምድራዊ አባቱን «አባዩ» ብሎ እንደሚጠራ ከእግዚአብሔር ጋር እጅግ በቀረበ መንገድ እንድንነጋገር ያስችለናል። በልጅነታችን በእግዚአብሔር ተስፋ የተገቡልንን ዘላለማዊ በረከቶች በሙሉ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር እንደምንወርስ ቃል ገብቶልናል። ነገር ግን ይህ መብት ከግዴታዎች ጋር አብሮ የሚመጣ ነው። እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ መንገድ በመኖር የቤተሰቡን ስም እንዳናጎድፍ መጠንቀቅ አለብን። ልጅ ወላጆቹን እንደሚታዘዝ ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ የመታዘዝ ግዴታ አለብን።  ጥያቄ፡– እውነተኛ አማኝ ከሆንክ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ። ሀ) እግዚአብሔርን እንደ አባት ብትቆጥርና እንደ ፈጣሪ ብቻ ብትቆጥር ከእርሱ ጋር የሚኖርህ ግንኙነት የሚለወጠው በምን በምን መንገድ እንደሆነ በዝርዝር ግለጽ። ለ) እግዚአብሔር አባትህን ምን ያህል እንደምትወደው ለመግለጽ ጊዜ ውሰድ።  3. የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት (1ኛ ቆሮ. 12፡13)። ይህን የጥናት መጽሐፍ በጻፈው ሰው አመለካከት መንፈስ ቅዱስ አንድን ሰው የማጥመቅ ሥራው የሚፈጸመው ሰውዬው በዳነ ጊዜ ከመቅጽበት ነው። አዲሱን አማኝ የክርስቶስ አካል በሆነችው ጽንፈ ዓለም ቤተ ክርስቲያን የመጨመር ተግባር የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ነው። ከየትኛውም ነገድ ይምጣ ምንም ዓይነት ፆታ ይኑረው ምንም ዓይነት ማኅበረሰባዊ አቋም ይኑረው የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት የዳነውን ሰው ወስዶ በክርስቶስ አካል ውስጥ እኩል ደረጃ ያለው አባል ያደርገዋል። በክርስቲያኖች መካከል ውዝግብ ከሚያስነሡ ጉዳዮች እንዱ ይህ በመሆኑ ወደፊት ባሉ ትምህርቶች በጥልቀት እንመለከተዋለን።  ጥያቄ፡- ከ 1ኛ እስከ 4ኛ ቀን ያሉ ትምህርቶችን ከልስ። ሠንጠረዥ አብጅ። በመጀመሪያው ክፍል ውስጥ አንድ ሰው ክርስቲያን በሚሆንበት ወቅት መንፈስ ቅዱስ የሚፈጽማቸውን ተግባራት በሙሉ ዘርዝር። በሁለተኛው ክፍል ይህ በረከት ምን ማለት እንደሆነ አጭር ገለጻ ጻፍ። በሦስተኛው ክፍል ውስጥ ደግሞ እንደ እግዚአብሔር ልጅነትህ ይህ በረከት ለምን ለአንተ ጠቃሚ እንደሆነ ግላጽ።  አንድ ሰው በሚድንበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ የሚፈጽማቸውን አገልግሎቶች የዘረዘርን ቢሆንም እንኳ ከእነዚህ አብዛኛዎቹ አገልግሎቶች ተወራራሽ መሆናቸውን ማስታወስ ይገባናል። እንዲያውም አንዳንድ የሥነ መለኮት ሊቃውንት እነዚህ ሁሉ የዘረዘርናቸው የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች በጥቅሉ የሚያመለክቱት አንድን ሁኔታ ነው ብለው ያምናሉ። መጽሐፍ ቅዱስ የሚለው አንድ ሰው በሚድንበት ጊዜ ከእግዚአብሔር አብና ከእግዚአብሔር ወልድ ልዩ ስጦታ ይቀበላል ብለው ያምናሉ። ይህ ስጦታ የመንፈስ ቅዱስ በሰው ልብ ውስጥ መኖር ወይም ማደር ነው። የዚህ የመንፈስ ቅዱስ ማደር ወይም መኖር በተለያዩ መንገዶች ይገለጻል። እነዚህም «የመንፈስ ቅዱስ ተለፋ»፥ «የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ»፥ «የመንፈስ ቅዱስ ዘር»፥ «የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት»፥ በመንፈስ ቅዱላ ልጅ የመሆን ሂደት»፥ ወዘተ… ናቸው። እነዚህ ሁሉ ነገሮች ግን አንድ ናቸው። ስለዚህ በእነዚህ አገልግሎቶች መካከል ከፍተኛ ልዩነት እንዳንፈጥር መጠንቀቅ አለብን። ከሁሉ የሚሻለው አመለካከት ይህ እያንዳንዱ አገልግሎት የአንዱ የመንፈስ ቅዱስ ህልውና የተለያየ ገጽታ መሆኑን መቀበል ነው።  ከመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ትምህርት በስተቀር ክርስቲያኖች ሁሉ እነዚህ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች በአዲሱ አማኝ ሕይወት ውስጥ የሚፈጸሙ እንደሆኑ ይስማማሉ። የሚያሳዝነው ነገር ግን ትኩረት የምናደርገው በአንድ ወይም በሁለት አገልግሎቶች ላይ ብቻ መሆኑ ነው። ሰመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ወይም በተወሰኑ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች ላይ ማተኮር በሥነ መለኮት ትምህርታችን ሚዛናዊነትን ያሳጣናል። መንፈስ ቅዱስ ስለሚያከናውናቸው ስጦታዎች እንደ በልሳን መናገር፥ ፈውስ፥ ተአምራትና መገለጥ ያላችሁ እምነት ምንም ይሁን፥ ነገር ግን ከተእምራት ሁሉ የበላይ በሆነው ማለትም የአዲስ ልደት ተአምር ላይ እንድታተኩሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3 Read More »

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

ብዙ ጊዜ የድነት (ደኅንነት)ን ጉዳይ እንደቀላል ሂደት እናቀርበዋለን። ነገር ግን ትናንትና እንዳየነው በጣም የተወሳሰበ ነው። እግዚአብሔር ከሚያደርጋቸው ታላላቅ ተአምራት አንዱ ሲሆን አፈጻጸሙም በፀጥታና በማይታይ መንገድ ነው። ሆኖም ግን ለዘላለም የሚዘልቅ ውጤት ያለው ብቸኛ ተአምር ነው። ሌሎች ተአምራት በሙሉ (እንደፈውስና በልሳን መናገር የመሳሰሉት ጊዜያዊ ጥቅም ነው ያላቸው። በዘላለም ሕይወታችን ላይ ግን ሚና የላቸውም። ትናንትና እንዳየነው ድነት (ደኅንነት) ታላላቅ ለውጦችን ያመጣል። በሕይወታችን የተደረጉት እነዚህ ለውጦች በጥቅል «ዳግም ልደት» ይባላሉ።  ጥያቄ፡ የሚከተሉትን ክፍሎች አንብብ። ዮሐ 1፡12፤ 3፡5-8፤ 1ኛ ቆሮ. 6፡11፤ 2ኛ ቆሮ. 1፡21፤ 5፡17፤ 1ኛ ዮሐ 2፡20፣ 26-27፡፡ ሰው በሚድንበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ስለሚሠራቸው የተለያዩ ሥራዎች እነዚህ ጥቅሶች ምን ያስተምሩናል?  1. መንፈስ ቅዱስ ለክርስቲያን አዲስ ሰማያዊ ልደት ይሰጠዋል፡- በአጠቃላይ አዲስ ፍጥረት ያደርጋቸዋል (ዮሐ 1፡12፤ 3፡5-8፤ 2ኛ ቆሮ. 5፡17)። እግዚአብሔር በሕይወታችን ጥገናዊ ለውጥ አያደርግም። እንዳረጀ ልብስ አይደርስብንም። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አዲስ ያደርገናል። ወደዚህ ዓለም ተወልደን በመጣንበት ጊዜ አዲስ እንደነበርን ሁሉ መንፈሳዊ ልደት የሆነው ሁለተኛ ልደታችንም ሙሉ በሙሉ አዲስ ያደርገናል። ስለዚህ አዲስ ልደት በርካታ እውነቶች አሉ።  በመጀመሪያ፥ ወዲያውኑ የሚሆን (ቅጽበታዊ) ነው። ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛችን እንደተቀበልን ወዲያውኑ ይፈጸማል። ኢየሱስን እንደ ብል አዳኛችን የምንቀበልበት ሂደት ረጅም ቢሆንም በቅጽበት የእግዚአብሔር ልጆች የምንሆንበት የተወሰነ ጊዜ በእግዚአብሔር ዓይን ፊት አለ። የሰይጣን ልጆች የነበርን ቢሆንም እንኳ ወዲያውኑ የእግዚአብሔር ልጆች እንሆናለን። በግሪክ ቋንቋ ይህ ሂደት የማይደገም የመንፈስ ቅዱስ ፍጹም ተግባር ነው። የሂደቱ ውጤት ቀን አንድ ጊዜ ከተጀመረ በኋላ ይቀጥላል።  በሁለተኛ ደረጃ ፥ ይህ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ አዲስና ልዩ የሆነ ልማት ቢሰማንም ባይሰማንም የሚሆን ነው። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በአንድ ወይም በሌላ መንገድ በሕይወታችን ታላቅ ለውጥ መደረጉን ከመንፈሳችን ጋር ያረጋግጥልናል። አንዳንድ ጊዜ የለውጡ ውጫዊ ፍሬዎች ለመታየት ጊዜ ይወስዳሉ።  ይህ አዲስ ልደት ሰማያዊ የሆነ አዲስ ተፈጥሮን ይሰጠናል። ይህ ሰማያዊ ተፈጥሮ ከኃጢአት ነፃ ሆነን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ተግባር እንድንፈጽም የማድረግ ችሎታ አለው። በመንፈሳዊ ብስለት እንድናድግና ክርስቶስን እንድንመስልም ያደርገናል። በዚህ አዲስ ተፈጥሮ ልባችን የመንፈስ ቅዱስ ዙሩን ወይም ቤተ መቅደስ ይሆናል። እግዚአብሔርንም ደስ የሚያሰኝ ፍሬ እንድናፈራ ያደርገናል።  ጥያቄ፡- ሀ) ይህን አዲስ ልደት የተለማመድከው መቼ ነበር? ላ) በሕይወትህ ለውጥ ያመጣው በምን መንገድ ነበር?  ጥያቄ፡- ሀ) አንድ ክርስቲያን ኃጢአት ሲያደርግ መንፈስ ቅዱስ ትቶት ይሄዳል የሚል ትምህርት ክርስቲያን ሲያስተምር ሰምተህ ታውቃለህን? ለ) ያስተማሩትን ግለጽ። ሰው ኃጢአትን በሚያደርግበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ትቶት እንደሚሄድ ለማረጋገጥ የተጠቀሙት ጥቅስ ምን ነበር? ሐ) አንተ ስለዚህ ጉዳይ ምን ታምናለህ? ለምን?  2. መንፈስ ቅዱስ ወደ ክርስቲያን ሕይወት ይመጣና ማደሪያው ያደርገዋል፡- የአዲስ ኪዳንን ዘመን ክብሉይ ኪዳን የተለየ የሚያደርገው ዋናው የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ይህ ነው። አንድ ሰው በልሳን ካልተናገረ በስተቀር መንፈስ ቅዱስ ወደ ሕይወቱ ለመግባቱ ማስረጃ የላንም የሚሉ አንዳንድ ክርስቲያኖች አሉ። ይሁንና ካሪዝማቲክ የሆኑትንም ይሁን ያልሆኑትን አካትቶ የብዙ ክርስቲያኖች አጠቃላይ አስተሳሰብ እንድ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በሚያምንበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ወደ አዲሱ የእግዚአብሔር ልጅ ልብ በመምጣት ማደሪያውን በዚያ ያደርጋል የሚል ነው። ጥቂት ቆይተን እንድ ሰው ከዳነ በኋላ መንፈስ ቅዱስ «ወሙሉ» ክርስቲያን እንዲሆን ማድረግ ስለሚገባው ነገር ያሉትን የአመለካከት ልዩነቶች እንመለከታለን። መንፈስ ቅዱስ በእያንዳንዱ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ እንደሚኖር የሚያስረዱ ሦስት ዋና ማረጋገጫዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሉ።  ሀ. መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ የሌለው ሁሉ ከእግዚአብሔር ኦይደለም ይላል (ሮሜ 8፡9 ተመልከት)። ይሁዳ ስለ ዘባቾች ሲናገር፡ ሐሰተኛ አስተማሪዎች መንፈስ ስላሌላቸው ከእግዚአብሔር አይደሉም ብሏል (ይሁዳ 19)። በአዲስ ኪዳን ውስጥ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ከተጠቀሱት አንዳንድ ልዩ ሁኔታዎች በስተቀር አንድ ሰው አማኝ ሆኖ መንፈስ ቅዱስ ስለሌለው እግዚአብሔር እንዲሰጠው መጸለይ ያስፈለገበት ጊዜ አልነበረም። (ማስታወሻ፡— በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ ክፍሎች አንድ ሰው መንፈስ ቅዱስ ሳይኖረው ክርስቲያን ሊሆን እንደሚችል የሚያስተምሩ ቢመስሉም፥ እነዚሁ ክፍሎች መንፈስ ቅዱስ የሌላቸው ክርስቲያኖች ሊኖሩ መቻላቸውን እንደማያስተምሩ ቆይተን እንመለከታለን።) ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት በውስጣቸው ለዘላለም እንደሚኖር ለደቀ መዛሙርት ነግሮአቸዋል (ዮሐ 14፡16-18፤ ማቴ. 28፡20)። ኃጢአት መንፈስ ቅዱስ ትቶን እንዲሄድ የሚያደርግ ከሆነ ኢየሱስም ትተን ይሄዳል ማለት ነው። ደግሞም አልዳንም ማለት ነው። ምክንያቱም መዳን ማለት መንፈስ ቅዱስን ማግኘት ማለት ነው። መንፈስ ቅዱስ የሌለው ማንኛውም ሰው አልዳነም።  ለ. መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ስጦታ ስለመሆኑ ሁልጊዜ የተነገረ ነው። (ዮሐ 7፡37-39፤ የሐዋ. 11፡16-17፤ ሮሜ 5፡5፤ 1ኛ ቆሮ. 2፡12፤ 2ኛ ቆሮ. 5፡5)። እነዚህን ጥቅሶች በሙሉ በቅርበት ብንመረምራቸው የሚያሳዩት መንፈስ ቅዱስ ለአንዳንዶች በአድልዎ የሚሰጥ ለሌሎች ክርስቲያኖች ደግሞ የሚከላከል እንዳልሆነ ነው። መንፈስ ቅዱስ ከእግዚአብሔር የሚሰጥ ስጦታ እንጂ ለጸሎት ወይም ለመልካም ሥነ ምግባር የሚሰጥ ሽልማት አይደለም።  ሐ. ኃጢአትን በሚያደርጉ ክርስቲያኖች ሕይወት መንፈስ ቅዱስ መኖሩን እንደማይተው ተነግሮአል። ይህ አንዳንዶች ኃጢአት ስለሠሩ መንፈስ ቅዱስ እንዳይተዋቸው ከሚጸልዩበትም ሆነ፥ በኃጢአት ምክንያት መንፈስ ቅዱስ ክርስቲያንን ሊተው ይችላል ብለው ከሚያስተምሩ ሰዎች ትምህርት ተቃራኒ .. ነው። በ1ኛ ቆሮ. 6፡19-20 በብዙ ኃጢአት ስለተቸገሩ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ጳውሎስ ሲናገር መንፈስ ቅዱስ እንደሚገኝ ጠቅሷል። (ማስታወሻ፡- የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች በመክፋፈል ይኖሩ ነበር፤ በመንፈስ ትዕቢት ተሞልተው ነበር፤ በዝሙት የሚኖር ክርስቲያን በመካከላቸው ነበር።  አንዳንድ ክርስቲያኖች ሌሎች ክርስቲያኖችን ለፍርድ ቤት ይከሱአቸው ነበር።) ጳውሉላ መንፈስ ቅዱስ ትቶአቸው እንዳይሄድ ይጸልዩ ዘንድ እላዘዛቸውም። ይልቁኑ መንፈስ ቅዱስ በውስጣቸው ስለሚኖር አኗኗራቸውን እንዲለውጡ ወቀሳቸው። ኃጢአት መንፈስ ቅዱስ በኃይል እንዳይሠራና ሕይወታችንን ሙሉ በሙሉ እንዳይቆጣጠር ሊያግድ ይችላል። ኃጢአት መንፈስ ቅዱስን ያሳዝናል (ኤፌ. 4፡30፤ 1ኛ ተሰ 5፡19)። ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን ክሕይወታችን አያባርርም።  ስለዚህ የአዲስ ኪዳን ግልጽ ትምህርት እንደሚያሳየው በየትኛውም ስፍራ በማንኛውም ባሕል የሚኖር ማንኛውም አማኝ መንፈስ ቅዱስ በውስጡ አለው። ኃጢአት የመንፈስ ቅዱስን ህልውና አያስቀርም። ሆኖም ግን ኃጢአት ከሕይወታችን የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ሊወስድ እንደሚችል እንመለከታለን። ኃጢአት በመንፈስ ቅዱስ ሙላት» ላይ ተጽእኖ ያደርጋል።  ጥያቄ፡- ሀ) ከላይ የቀረቡት ምክሮች ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ብዙ ክርስቲያኖች ከሚያስተምሩት በምን ይለያሉ? ለ) የትኛውን አመለካከት ትመርጣለህ? ለምን?  3. መንፈስ ቅዱስ ክርስቲያንን ያጥባል (1ኛ ቆሮ. 6፡11)። በአዲስ ኪዳን ዘመን መጀመሪያ አካባቢ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ ካመነ በኋላ ወዲያውኑ ይጠመቅ ነበር። የማመን ተግባርና የጥምቀት ሥርዓት በአንድ ጊዜ ይፈጸም ስለነበር በአንዳንድ ጥቅሶች እጅግ ተቆራኝተው ቀርበዋል። በሕዝቡ እእምሮና በትምህርቱ ይህ ሥርዓት በጥምቀት የኃጢአትን ታጥቦ መወገድ የሚያመላክት ነበር። ነገር ግን ጥምቀት ሰውን የሚያድነው ነገር አልነበረም። ይህ መንፈስ ቅዱስ የሚያደርገውን ውስጣዊ ማንጻት የሚያሳይ ውጫዊ ምላሴ ነበር። አዲስ ኪዳን የጥምቀት ሥርዓት በራሱ ሰውን እንደሚያድን በየትም ስፍራ አያስተምርም። መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ የሚያስተምረው መንፈሳዊ መንጻትን የሚያስገኝልን በኢየሱስ ላይ ያለን እምነት እንደሆነና ሰውን በመኮነን የእግዚአብሔር ፍርድ በላዩ እንዲሆን የሚያደርገው አለማመን ስለመሆኑ ነው።  በአዲስ ኪዳን ብዙ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ከልብላ ላይ ቆሻሻን እንደሚያስወግድ ውኃ ሆኖ ቀርቧል። መንፈሳዊ ቁሻሻችን የሆነውን ኃጢአታችንን አጥቦ ይጥላል። ከኃጢአት የነፃን ያደርገናል (1ኛ ዮሐ 1፡9)። የመንፈስ ቅዱስ ማንጻት ሁለት መልኮች አሉት። በመጀመሪያ፥ መንፈስ ቅዱስ በአቋም ‹ንጹሕን የእግዚአብሔር ልጆች ሆነን ወደ እግዚአብሔር ህልውና ለመግባት የሚያስችል ዘላቂ መንጻት ይሰጠናል። በ1ኛ ቆሮ. 6፡11 ጳውሎስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ማንጻት ስሚናገርበት ጊዜ የኃላፊ ጊዜን የተጠቀመው ለዚህ ነው። በሁለተኛ ደረጃ፥ በየቀኑ ከምንሠራው ኃጢአት በተደጋጋሚ የመንጻት ጉዳይም አለ። ይህንን የሚያደርገው የክርስቶስን ደም ወደ ሕይወታችን በማምጣት ነው።  4. መንፈስ ቅዱስ ክርስቲያኖችን ይቀድሳል (1ኛ ቆሮ. 6፡11)። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እጅግ ተዘውትረው ከሚጠቀሱ ቃሎች አንዱ «መቀደስ» የሚለው ቃል ነው። ብዙ ጊዜ መቀደስ የሚለው ቃል ትርጉሙ ከኃጢአት ነፃ መሆንን የሚያመለክት ቢመስለንም፥ አሳቡ ግን «መለየት» ነው። በብሉይ ኪዳን

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2 Read More »

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

ጥያቄ፡- ሀ) እንተ የመሰከርህለት ወይም ከሌላ ክርስቲያን የሰማኸው (የተአምራት ሁሉ ቁንጮ ምንድን ነው? ለ) ያንን ተአምራት ታላቅ ያደረገው ምን ነበር?  በዙሪያችን ሁሉ አስደናቂ ተአምራትን እንሰማለን። ከእዚህ ተአምራት እንዳንዶቹ ሌሎች ክርስቲያኖች ሲናገሩ የሰማናቸው ናቸው። ሌሎቹን ደግሞ እራሳችን ስለተለማመድናቸው የምናያቸው ናቸው። ብዙ ጊዜ እነዚህ ተአምራት ከበሽታዎች መፈወስን ወይም ክከፉ መናፍስት ነህ መውጣትን የሚያካትቱ ናቸው ሰዎች ክሙታን እንደተነ እንኳ እንሰማለን።  ይሁንና፡ ከሌሎች ተአምራት ሁሉ የላቀና ብዙ ጊዜ የሚሆን ሌላ ተአምር አለ። ምናልባትም ይህ ተአምር ከሁሉ አስደናቂ ነው። ይህ ተአምራት ምንድን ነው? የመንፈሳዊ ውልደት ተአምራት ነው። ድነት (ደኅንነት)ን በማግኘት የእግዚአብሔር ልጆች ስንሆን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በእውነት አስደናቂ የሆነ ተአምር ያደርጋል። መጽሐፍ ቅዱስ ከማመናችን በፊት በኃጢአታችን ምክንያት ሙታን እንደነበርን ይናገራል (ኤፌ. 2፡ህ። በድንገት ቀን ጊዜያዊ ሳይሆን ዘላለማዊ የሆነ መንፈሳዊ ሕይወት ተሰጠን ኈ(ዮሐ 3፡16)። ከዚህ ቅጽበት በኋላ የእግዚአብሔር ልጆች ሆንን (ዮሐ 1፡12)። ብዙ ክርስቲያኖች ሥጋዊ አካል ላይ የሚታይ ተአምር ለማየት ይናፍቃሉ። ይህን በማድረጋቸው ከሁሉ የላቀውን የድነት (ደኅንነት)ን ተአምር ይረሳሉ።  በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ የተገለጠውን የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በምናጠናበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ የተለያዩ አገልግሎቶች እንደነበሩት ተመልክተናል። ከእዚህ አንዳንዶቹ አስደናቂ መሆናቸውንም አይተናል። ወደፊት በልሳናት ከመናገር ጋር ስለ ተያያዘውና በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ አወዛጋቢ ስለሆነው ርእስ እንነጋገራለን። አሁን ግን የመንፈስ ቅዱስ ጥናታችንን አትኩሮት በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ላይ ማድረጉን እናበቃና አዲስ ኪዳን ስለ መንፈስ ቅዱስ የሚያስተምረውን ርእስ በርእስ እንመለከታለን። በዚህ ሳምንት ትምህርት፥ እኛን የእግዚአብሔር ልጆች ባደረገውና የተአምራት ሁሉ ቁንጮ በሆነው ተአምር ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ራሱ ስላለው ሚና እናጠናለን።  ጥያቄ፡- ሀ) የእግዚአብሔር ልጅ የሆንከው እንዴት እንደሆነ በአጭሩ ግለጽ። ለ) ከተላማመድካቸው ሌሎች ተአምራት ሁሉ ይኸኛው ለአንተ በጣም አስፈላጊ የሆነው እንዴት ነው?  ጥያቄ፡– የሚከተሉትን ጥቅሶች አንብብ። ዮሐ 3፡3-7፤ 16፡8-11፤ ቲቶ 3፡5። መንፈስ ቅዱስ ይሠራል ስለሚባለው ሥራ ዘርዝር። ሥራው ስለሚያካትታቸው ጉዳዮች አጭር ማብራሪያ ጻፍ።  አሐዱ ሥሉስ የሆነው አምላክ የደኅንነታችን ዋነኛ አከናዋኝ ነው። የእግዚአብሔር ልጆች ያደርጉን ዘንድ እያንዳንዱ የሥላሴ አካል ፍጹም በሆነ ስምምነትና አንድነት ይሠራሉ። ነገር ግን ያልዳነውንና በመንፈሱ ሙት የሆነውን ሰው ወደ አዲስ ፍጥረት በመቀየር እንደ እግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔርን ደስ በሚያሰኝ መንገድ እንዲኖር የሚያስችላውና የኃያሉ እግዚአብሔር ማደሪያ የሚያደርገው ከሥላሴ አካላት አንዱ የሆነው መንፈስ ቅዱስ ነው።  መንፈስ ቅዱስ በአንድ ሰው ሕይወት ሊሠራ፥ ከአነስተኛ ብልጭታ ተነሥቶ ይህ ነው የማይባል ኃይል እስከሚጎናጸፍ እያደር እንደሚያይል የባሕር ሞገድ ይመስላል። በዚህ አኳኋን ግላስቡ መንፈስ ቅዱስ በውስጡ አድሮ የክርስቶስ አንዱ ብልት እስከሚሆን ሥራውን በፀጥታና በእርጋታ ይጀምርና ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያድጋል። በመጨረሻ ሰውዬው በኢየሱስ ክርስቶስ ሲያምን መንፈስ ቅዱስ ወደ ከፍተኛ የተግባር እንቅስቃሴ በመሸጋገር ታላቁንና የተአምራት ሁሉ ቁንጮ የሆነውን ተአምር ይፈጽማል።  በቅድሚያ የምናጠናው በምድር ላይ ያሉ ሰዎችን በሙሉ በፀጥታና በማይታይ ሁኔታ የሚዳስሱትን ሁለት የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶችን ነው። የሥነ መለኮት ትምህርት አዋቂዎች ይህንን ሥራ «የአጠቃላይ ጸጋ» ሥራ ይሉታል። ይህ የእግዚአብሔር ልጆች ለሆኑትም ሆነ ላልሆኑት ሁሉ በረከት እንዲዳረስ መንፈስ ቅዱስ በምድር ሁሉ ላይ የሚሠራው አጠቃላይ ሥራ ነው። እግዚአብሔር ላጻድቃንና ለኃጥአን ዝናምን እንደሚያዘንብ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል (ማቴ. 5፡45)። ክርስቲያን ብንሆንም ባንሆንም ሕይወት በሙሉ የእግዚአብሔር አጠቃላይ ውጤት ነው። በብሉይ ኪዳን ላለነበረው አገልግሎት በትምህርት ሦስት ስናጠና የሁሉንም ሕይወት የሚጠብቀውና በምድር ላይ አዲስ ሕይወትንም የሚፈጥር መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ተመልክተናል። እዚህ ላይ ግን የምናተኩረው ከሰው ድነት (ደኅንነት) ጋር በሚያያዙት የአጠቃላይ ጸጋ ሁለት ገጽታዎች ላይ ይሆናል።  1. የመንፈስ ቅዱስ ኃጢአትን የመከለል ሥራ (2ኛ ተሰ. 2፡5-12 አንብብ)  በ1ኛና 2ኛ ተሰሎንቄ መጻሕፍት ጳውሎስ በመጨረሻዎቹ ቀናት የሚገለጡ እውነቶችን ያስተምራል። በትምህርቱ መካከል ላይ ስላ ዓመፅ ሰውና እርሱን ስለሚከላከለው ይነግረናል። ይህ ክፍል ለመረዳት አስቸጋሪ የሆነ ሲሆን ሊቃውንትም በአተረጓጐም ይላያዩበታል። ቢሆንም ከሁሉም የቀረበው አተረጓጐም የሚከተለው ነው።  ሀ. የዓመፅ ሰው በዚህ ክፍል ውስጥ ጳውሉላ የሚነግረን በዚህ ዓለም የሚሠራ የዓመፅ መንፈስ እንዳለ ነው። ይህ ዓመፅ በተለያዩ መንገዶች እግዚአብሐርን አለመታዘዝን ያስከትላል። አንድ ቀን ይህ ልዩ የሆነ የዓመፅ ሰው እንደሚገለጥ ጳውሉዕ ይናገራል። እርሱም በሰው ልጅ ውስጥ ያለው ክፋት ሁሉ እለስ «ገለጥ የሚሠራ ይሆናል። የሒትለር፥ የስታሊንና የመንግሥቱን ክፋት በአንድ ላይ አጠቃልሎ የያዘ ሰውን የሚመስል ይሆናል። ኃይሉን የሚያገኘው ከሰይጣን ነው። ከኃይሉ ታላቅነት የተነሣ  ብዙ ዓይነት ተአምራቶችን ያደርጋል። በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ከእውነት ወደ ክፋት ይመራቶዋል። ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ሊመጣ ን ሙሉ በሙሉ ድል ያደርገዋል። ጳውሎስ በዚህ ቦታ የሚገልጸውን፥ ዳንኤል፥ «ትንሹ ቀንድ። (ዳን 7፡8) ከላውና በራእይ መጽሐፍ ደግሞ «አውሬው» ከተባለው (ራእይ 17፡8) ጋር ስናወዳድረው ሁሉም የሚናገሩት ስለ አንድ ሰው ይመስላል። ሁሉም የሚገልጹት ዓለምን በእግዚአብሔርና በቅዱሳኑ ላይ ለመጨረሻ ጊዜ የሚያስከትተውን የመጨረሻውን የዓለም ገዢ ሐሰተኛው ክርስቶስን ነው (1ኛ ዮሐ 2፡1፥ 18)።  ለ. የዓመፅ ሰውን ከልካይ፡- ይህ ክፉ ሰው ወደ ለም መድረክ እንዳይመጣ የሚከለክለው ምንድን ነው? ጳውሎስ እንደሚናገረው እንዳይገለጥ ያገደውና የሚከላከለው አለ። ይህ ከልካይ ማን እንደሆነ የተለያዩ አሳቦች ይሰጣሉ። አንዳንዶች የሮም መንግሥት ነው ብለው ያስባሉ። ሌሎች ደግሞ ከመጨረሻው ዘመን በፊት ከዓለም የምትወሰደው ዓለም አቀፍዋ ቤተ ክርስቲያን ናት ይላሉ (1ኛ ተሰ. 4፡13-18)። ሌሎች ደግሞ እስካሁን ድረስ በብዙ መንግሥታት ውስጥ በሚገኙት ሕግና ሥርዓት ላይ ያለው እምነት ነው ይላሉ ነገር ግን በጣም የሚያሳምነው አገላለጽ የሚከተለው ነው። ይኸውም፡ ‹የሚከለክል› የሚለው ቃል የሚያመለክተው በዓለም የሰፈነው አጠቃላይ ኃጢአት እንዲወገድ የመንፈስ ቅዱስ ህልውናና ሥራ ላላሚያከናውኑት የመከልከል ተግባር ነው። ሐሰተኛ ክርስቶስ ተገልጦ ምድርን በቁጥጥሩ ሥር ከማስገባቱ በፊት መደረግ ያለበት ነገር አለ። ይኸውም በሰው ልብ ውስጥ ያለው ክፋት ያለገደብ ተላቅቆ በምድር ላይ ጥፋት እንዳይስፋፋ የሚከለክለው የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት ይገታል። . . ከዚያም እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ከምድር ላይ ይወለደዋል። በዚያን ጊዜ ታላቅ ክፋት በምድር ላይ ይገለጣል። ይህ ክፋት የሚቆመው ኢየሱስ ክርስቶስ ተመልሶ መጥቶ በሙሉ ሥልጣን በሚገዛበት ወቅት ብቻ ነው።  በዘፍ. 6፡3 እግዚአብሔር ስለ ኖህ ዘመን ክፋት ሲናገር «መንፈሴ በሰው ላይ ለዘላለም አይኖርም፥ እርሱ ሥጋ ነውና» ብሏል። ይህ የሚያሳየው ከኖህ ዘመን በፊት መንፈስ ቅዱስ የኃጢአትን መስፋፋት ለመከላከል ይሠራ እንደነበር ነው። መንፈስ ቅዱስ ኃጢአትን ይከላካል ካነበረበት መንገድ አንዱ የሰው ልጅ ሊሠራ የሚችለው ክፋት ሁሉ በምድር ላይ እንዳይታይ ዕድሜን መገደብ ነበር። «እግዚአብሔርም የሰው ክፋት በምድር ላይ እንደ በዛ፥ የልቡ አሳብ ምኞትም ሁልጊዜ ፈጽሞ ክፉ እንደ ሆነ አየ» ተብሎ ስለዚያ ጊዜ ተጽፋል። ክፋት ምድርን የሞላ ቢሆንም እንኳ መንፈስ ቅዱስ የክፋትን ተግባራዊነት ይቆጣጠር ነበር። ክፋት ራሱን የሚያጠፋ ስለሆነ በጊዜው እግዚአብሔር ባይቆጣጠረው ኖሮ ሰውን ሁሉ ባጠፋ ነበር። ኖኅና ቤተሰቡ ብቻ ሲቀሩ የሰው ልጅ ሁሉ በጥፋት ውኃ እስኪጠፋ መንፈስ ቅዱስ በዚያ ዘመን የሰዎችን ክፋት ይቆጣጠር ነበር።  አንዳንድ ሊቃውንት «የሚከለክላው» መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ የሚያስቡት ለምንድን ነው? በርካታ ምክንያቶች አሉ።  1. በ2ኛ ተሰ. 2፡7 በግሪኩ ትርጉም ‹የሚከላክለው› ለሚለው ቃል የተሰጠው ተውላጠ ስም ለሰው የሚያገለግለው «እርሱ» የሚል ቃል እንጂ ለነገር ወይም ለዕቃ የሚያገለግል አቻ ቃል አይደለም። ይህ የሚያመለክተው ከልካዩ እንደ መንግሥት፥ ሕግ ወይም ቤተ ክርስቲያን ያለ ድርጅት ሳይሆን ሰብአዊ አካል መሆኑን ነው።  2. ይህ ከልካይ ሰይጣን የዓመፅ ሰውን የእግዚአብሔር ትክክለኛ ጊዜ ከመድረሱ በፊት እንዳይልክ የመከልከል ኃይል ስላለው ከሰይጣን የላቀ ኃይል ያለው መሆን አለበት። ከሰይጣን የላቀ ኃይል ያለው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ስለዚህ ከልካዩ እግዚአብሔር እራሱ እንደሆነ ይመስላል።  3. ከልካዩን የተሰሎንቄ ክርስቲያኖች በሚገባ ያውቁት ነበር (2ኛ ተሰ. 2፡6)። ይህ ፈጽሞ በመጨረሻ ዘመን ለሚኖር ሰው የተነገረ ሊሆን አይችልም።  እዚህ የምንማረው

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1 Read More »