የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ጉባኤው እጅግ ታላቅ ነበር። እርሱን ለመስማት በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰብስበው ነበር። ያን ያህል ቁጥር ያለው ሰው የተሰበሰበት ዋና ምክንያት ግን ተአምራት ለማየት ነው። ይህ ሰው የፈውስ ስጦታ እንዳለው ይነገር ነበር። በስብከቱ መጨረሻ ላይ የታመሙ ሰዎች ሁሉ እንዲቆሙ ጠየቀ። ከአንድ በላይ በሽታ ያለባቸው ቢሆንም ፈውስን እንደሚያገኙ ነገራቸው። በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ይፈወሱ ዘንድ ቆሙ። ከዚህ በኋላ እንደ ተፈወሱ አወጀ። በጉባኤው መካክል ከአዲስ አበባ የመጣች በጠና የታመመች ሌት ነበረች። እንደ ተፈወሰች አምና ወደ ቤቷ ተመለሰች። ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ሞተች። 

እግዚአብሔር፥ ፈዋሽ እምላክ ነው። ነገር ቀን እግዚአብሔር የሚፈውሰው ከላይ በተጠቀሰው መንገድ ነውን? ሰዎች መፈወሳቸው ከተነገራቸው በኋላ ባይፈወሱ ምንድን ነው የሚሆነው? ጥፋቱ የማን ነው? መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያስተምረናል። 

ጥያቄ፡- ማቴ. 12፡ 25-28፤ ሉቃስ 1፡21 ጀምሮ፤ ዮሐ 12፡31፤ ራእይ 21፡4። እነዚህ ጥቅሶች በኢየሱስ ዘመን የተአምራት ሚና ምን እንደነበር ያሳያሉ? 

እግዚአብሔር ተአምራትን የሚሠራ አምላክ ነው። ተአምራትን ሲሠራ ነበር። ወደፊትም ተአምራትን መሥራት ይቀጥላል። እግዚአብሔር ተአምራትን ማድረጉን አቁሟል የሚሉ አንዳንድ ክርስቲያኖች ቢኖሩም እንኳ ለዚህ አባባላቸው ምንም ዓይነት መጽሐፍ ቅዱሳዊ መረጃ የላቸውም። ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ የምንመለከታቸው መረጃዎች የሚያሳዩን እግዚአብሔር ተአምራት ማድረጉን እንደቀጠለ ነው። ስለዚህ ዛሬም ቢሆን እግዚአብሔር ተአምራትን ያደርግ ዘንድ፥ ይፈውስ ዘንድ፥ ሰዎችን ከአጋንንት ነፃ ያወጣ ዘንድ፥ ወዘተ… ልንጠብቅ እንችላለን። 

ነገር ግን እግዚአብሔር ተአምራትን በብሉይ ኪዳንና በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ባደረገው ዓይነት በተዘወተረ ሁኔታ እንደሚያደርግ ማመንና መጠበቅ ትክክል አይደለም። በተጨማሪ ተአምራት ማንኛውም ክርስቲያን በፈለገው ጊዜ ሊያደርገው የሚችለው ነገር እንደሆነ ማሰብም ስሕተት ነው። ተአምራትን የማድረግ ኃይል ፈጽሞ በሰው ላይ የሚመሠረት አይደለም። የተአምራት መሠረት እግዚአብሔር ነው። ተአምራትን ያደርግ ዘንድ እግዚአብሔርን ሊያዝዘው የሚችል ማንም የለም። አንድ ሰው ሊያደርግ የሚችለው ነገር የእግዚአብሔር ተአምራት ይፈጸም ዘንድ መጠቀሚያ መሣሪያ ለመሆን እራሱን አዘጋጅተ መቅረብ ነው። ይህ ነገር ደግሞ ደረጃ በደረጃ ሊፈጸም ይገባል። ሰዎች ዛሬ በተአምራት ላይ ያላቸው በጥልቅ የመወሰድ ሁኔታ አደገኛ ነው። ለማመን ምልክትን እንደሚጠይቁ አይሁዶች ሆነናል። ኢየሱስ ከሞት የመነሣቱ እውነት ምልክት የሆነውን የዮናስን ምልክት ለማመን እምቢ እንላለን (ማቴ. 12፡39-4)። 

እግዚአብሔር በዚህ ዘመን ምንም ተአምራትን አያደርግም የሚሉትና እግዚአብሔር በእኛ ትእዛዝ ሁልጊዜ ተአምራትን ያደርጋል የሚሉ ሁለቱም አቋሞች ስሕተት ናቸው። እውነቱ ያለው በሁለቱ መካከል ነው። በልሳናት እንደ መናገርና እንደ ትንቢት ስጦታዎች የፈውስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎችም ዛሬ በቤተ ክርስቲያን የጋላ ክርክር የሚካሄድባቸው ናቸው። በሌሎች ስጦታዎች እንደሆነው ሁሉ የከረሩ አቋሞችና ከአግባብ ውጭ የሆኑ አጠቃቀሞች ሰዎች ከሚገባ በላይ እንዲሄዱ አድርገዋቸዋል። 

ጥያቄ፡- ሀ) ተአምራትን እንዴት ትተረጉመዋለህ? ለ) መለኮታዊ ፈውስን እንዴት ትተረጉመዋለህ? 

አንድ አስደናቂ ነገር ሲፈጸምልን «ተአምር ነው» እንላለን። ሕመም ሲሰማንና መድኃኒት በመውሰድ ሊሻለን እግዚአብሔር ፈወሰን እንላለን። በአንድ አንጻር ስናየው በሕይወታችን የሚፈጸሙ ነገሮች በሙሉ ተአምራት ናቸው። አካላዊ ሕይወታችን ራሱ ተአምር ነው። ሰውነታችን ከበሽታ ባገገመ ጊዜ ሁሉ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚገኝ ፈውስ ተቀበልን ማለት ነው። 

እግዚአብሔር ተአምራትን አደረገ ወይም በተአምር ፈውስን ሰጠ ስንል በእርግጥ ምን ማለታችን ነው? ተአምር የምንለው እግዚአብሔር ዓለም ትተዳደርባቸው ዘንድ የደነገጋቸውን ተፈጥሮአዊ ሕግጋት ያለፈ ነገር ሲፈጽም ነው። ይህም ማለት እግዚአብሔር በተፈጥሮአዊ መንገድ ፈጽሞ የማይቻለውን ነገር ሲያደርግ ነው። መለኮታዊ ፈውስ ማለት እግዚአብሔር በሰው ሰውነት የሚካሄደውን ተፈጥሮአዊ የእርጅናና የበሽታ ሂደት ያለፈ ነገር ሲያደርግ ነው። እግዚአብሔር በተፈጥሮአዊ መንገድ በሰውነት ውስጥ ፈውስ ሲያካሂድ በሽታውን በቅጽበት በማንሣት ሙሉ ጤንነትን ይመልሳል። ይህ የሚሆነው በሽታን ለማስወገድ እግዚአብሔር በተፈጥሮ ከሰጠው የመድኃኒት ውጤት የተለየ ነው። 

ለማያምኑም ሆነ ለሚያምኑ ሰዎች ያልተለመዱ ነገሮች ይደረጋሉ። ነገር ግን ሁልጊዜ እንደ ልዕለ-ተፈጥሮአዊ ተአምራት መታየት የለባቸውም። እግዚአብሔር የሥጋ ፈውስን የሚሰጥበት የተለመደ መንገድ በተፈጥሮአዊ ሕግጋትና ለሰው ልጆች በሰጠው ተፈጥሮአዊ ፈዋሽ መድኃኒቶች አማካኝነት ነው። ነገር ግን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስላለው ተአምራትና ፈውስ ስንነጋገር እግዚአብሔር ፍጥረታትን ለማስተዳደርና ለመምራት ከደነገጋቸው ተፈጥሮአዊ ሕግጋት ባሻገር (እግዚአብሔር) ጣልቃ ገብቶ ካላደረገው በስተቀር ፈጽሞ ሊሆን የማይችለውን ነገር ነው።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው? የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading