በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

በአንድ ጥቅጥቅ ያለ ጫካ ውስጥ ቆሞ መንገዱ ወደ የት እንደሚወስድ ለመናገር መሞከር እጅግ ከባድ ነው። ምክንያቱም ወደፊት ለማየት የምንችለው ጥቂት እርምጃ ዎች ብቻ ስለሆነ ነው። ነገር ግን ከተራራ ጫፍ ላይ ቆመን የአንድን መንገድ አቅጣጫ ብናጠና ያ መንገድ ወደ የት እንደሚወለደን መመልከት እጅግ ቀላል ነው። ስለ መንፈስ ቅዱስ በምናደርገው ጥናት ወደ የት እንደምንሄድ ለመረዳት ትምህርታችን ወደ የት እንደሚወስደን በአጭሩ መረዳት ያስፈልገናል። ስለ መንፈስ ቅዱስ ጥናታችንን የምንጀምረው የምንመለከታቸውን ዋና ዋና እውነቶች በሰፊው በመቃኘት ይሆናል። ይህም የጥናት መጽሐፋችን እንዴት እንደተዋቀረ ለመመልከት ያግዘናል። 

«መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?» የሚል ጥያቄ እናነሣለን። እካላዊ ህልውና የሌለው ኃይል ብቻ ነውን? ወይስ ሕያው የሆነ አካል ያለው ህልውና የሥላሴ ሦስተኛው አካል ነው? ቀጥላን መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን፥ በአራቱ ወንጌላት በኢየሱስ ሕይወት ውስጥ የታየውና በሐዋርያት ሥራ የሚያስተምረውን በአጭሩ እንቃኛለን። ሰማያቋርጥ ተከታታይነት እየተገለጠ እንደሚመጣ ታሪክ ከመጀመሪያው ጀምሮ መጽሐፍ ቅዱስን እየቀጠልን ስናነብ ስለ መንፈስ ቅዱስ የበለጠ እየተማርን እንሄዳለን። ከዚያ በመቀጠል የመንፈስ ቅዱስን አገልግሎት ከፋፍለን እንመለከተዋለን። ክርስቲያኖች ባልሆኑ ሰዎች መካከል እንኳ ስላለው ተግባር እናያለን። እያንዳንዱን የዳነውን ሰው ደግሞ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወዳለ ግንኙነት እንዴት እንደሚመራው እንመለከታለን። ቀጥለን አንድን ክርስቲያን ክርስቶስን ወደ መምሰል እንዲያድግ በሕይወቱ የሚሠራበትን፥ ክርስቶስ እያንዳንዳችን እንድንሠራ የሚፈልጋቸውን ነገሮች፥ በክርስቲያን ውስጥና በክርስቲያን አማካኝነትየሚሠራበትን በርካታ የተለያዩ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች እንመለከታለን። ከዚያ በመቀጠል የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች በተለይ ደግሞ በቤተ ክርስቱያን ውስጥ የተለያዩ ውዝግቦች የሚያስነሡትን ማለትም ሰልሳን የመናገር፥ የፈውስና የትንቢት ስጦታዎችን እንመለከታለን። ጥናታችንን የምናጠቃልለው በየዕለቱ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እንዴት መመላለስ እንደምንችል በመመልከት ይሆናል። 

ጥያቄ፡– ያለፈውን አንቀጽ አንብብ። በዚህ መጽሐፍ በምንመለከታቸው እያንዳንዱ ዋና ርእሶች እግዚአብሔር እንዲያስተምርህ ጸልይ። 

ዛሬ መንፈስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር ሥራዎች በሙሉ እንዴት አስፈላጊና ጠቃሚ እንደሆነ እንመለከታለን። ዛሬ በዓለም ላይ መንፈስ ቅዱስ ስላለው ሁለት ዋና ተግባራት በአጭሩ እንጠቅሳለን። 

ጥያቄ፡- ስለ መንፈስ ቅዱስ ላታስብ ወደ አእምሮህ የሚመጣው አሳብ ምንድን ነው? መንፈስ ቅዱስ ምን ይመስላል? ምን ለመሥራት ይሞክራል? 

እንደ ክርስቲያኖች አብዛኛው የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀታችን ስለ እግዚአብሔር እብና ደኅንነታችንን ስለዋጀው ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ስለ መንፈስ ቅዱስ ማንነትና ምን እንደሚሠራ ለማሰብ የምንወለደው ጊዜ በጣም አነስተኛ ነው። ይህም ሆኖ መጽሐፍ ቅዱስን ስጥንቃቄ ብናጠና በእያንዳንዱ የእዲስ ኪዳን ገጽ ላይ ስለ መንፈስ ቅዱስ እናነባለን። የመጽሐፍ ቅዱስ ተቀዳሚ አትኩሮት ባይሆንም እንኳ ለላ መንፈስ ቅዱስ የተጠቀሱ እውነቶች ከመጽሐፍ ቅዱስ ዋና ትምህርቶች ሁሉ ጋር እጅግ ክመጣመራቸው የተነሣ መንፈስ ቅዱስ እግዚእብሔር በሚሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ውስጥ ገቢራዊ ተሳትፎ አለው። 

ለምሳሌ፡- በአዲስ አበባ የምትኖር ሆነህ አንድ ቆንጆ ባለ 10 ፎቅ ሕንነ ተመላክትህ እንበል። – ይህን ሕንፃ ማን ሠራው? ከየት ተገኘ? እንዴት ህልውና ሊያገኝ ቻለ? ሕንፃውን እንደገነቡ የምናስባቸው በርካታ የተለያዩ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ። ሕንፃውን በአእምሮው በመቅረጽ ስሕንፃው ሥራ መጨረሻ መካተት አለባቸው ብሎ ያሰባቸውን ነገሮች በሙሉ ጨምሮ ሕንፃውን በወረቀት ላይ ያሰፈረው የንድፍ መሐንዲሱ (አርክቴክቱ) ይኖራል። ባንድፍ መሐንዲሱ የተሠራው ነገር በሙሉ በታሰበው መንገድ በሥራ ላይ መዋሉን የሚያረጋግጥ የሕንፃ ሥራ ተቋራጭ ይኖራል። በመጨረሻ ሥራውን በመሥራት ሕንፃው ተግባራዊ እንዲሆን የሚያደርጉት ግንበኞች፥ አናፂዎች የኤሌክትሪክ ሠራተኞች ወዘተ… ይኖራሉ። 

ይህ መግለጫ ሥላሴዎች እግዚአብሔር አብ፥ እግዚአብሔር ወልድና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እንዴት እብረው እንደሚሠሩ ለማሳየት ጥሩ ምሳሌ ነው። መጽሐፍ ቅዱስን በቅርበት ስንመረምር ማናቸውንም ዋና የሚባሉ ተግባራት ሥላሴ አብረው እንደሚሠሩት ያሳየናል። እግዚአብሔር አብ እንደ ንድፍ አውጪው መሐንዲስ ሆኖ ምን እንደሚፈጸም ይወስናል። እግዚአብሔር ወልድ የእግዚአብሔር አብ ዕቅድ ይፈጸም ዘንድ የበላይ ተቆጣጣሪ ሆኖ እንደሚመለከተው ተቋራጭ ነው። መንፈስ ቅዱስን ደግሞ የእግዚአብሔር አብና የእግዚአብሔር ወልድን ዓላማና ዕቅድ ወደ እውነታ የሚተረጉም የሕንፃው ሠራተኛ ሆኖ እንመለከተዋለን። መንፈስ ቅዱስ ለሕንፃው ሥራ እንደ ተቆጣጣሪ በመሆን በሠራተኞች ማለትም በእግዚአብሔር ልጆች አማካኝነት የሚያከናውናቸው ሌሎች የእግዚአብሔር ሥራዎችም አሉ። 

ጥያቄ፡- የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። ዘፍ 1፡1-2 እና ቆላ. 1፡16-17፤ ሉቃስ 1፡35 እና ዮሐ 3፡16፤ ዮሐ 6፡35-40 እና ቲቶ 3፡3-7። እነዚህ ጥቅሶች ሥላሴዎች አንድ ነገር በመፈጸም እብረው እንዴት እንደሚሠሩ ምን ያሳዩናል? 

የሥላሴ አካላት በሙሉ ያልተሳተፉበት የእግዚአብሔር ሥራ ምናልባት አይኖር ይሆናል። ክሥላሴ አካላት አንዳቸው ለአንድ ሥራ ተቀዳሚ ኃላፊነት የሚወስዱ ቢሆንም እንኳ (ለምሳሌ ለኃጢአታችን የሞተው ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው) የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶችን ሁሉ በአንድነት ስናጣምራቸው የቀሩትም የሥላሴ አካላት እንደተሳተፉበት እናየላን። 

ሥላሴዎች የእግዚአብሔርን ዕቅዶች ለመፈጸም እንዴት እንደ ሠሩ ሦስት ምሳሌዎችን እንመልከት። 

1. የመፍጠር ሥራ፡- መጽሐፍ ቅዱስን በምናጠናበት ጊዜ እንደምንመለከተው እያንዳንዱ የሥላሴ አካል በመፍጠር ሥራ ተካፍሏል። በዘፍ 1፡1 እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን እንዲፈጠረ ተገልጾልናል። በቆላ. 1፡16-17 ፍጥረታት ሁሉ የተፈጠሩት የእግዚአብሔር ልጅ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ እንመለከታለን። እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን በፈጠረበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመፈጸም በመዘጋጀት በውኃ ላይ እንደ ርግብ ሰፍፎ እንደነበር ተነግሮናል (ዘፍ 1፡2)። 

2. የክርስቶስ መወለድ፡ ዮሐ 3፡16 እግዚአብሔር አብ ልጁን ኢየሱስን ወደዚህች ምድር እንደላከው ይነግረናል። ነገር ግን ዘላለማዊ ልጁ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስን በተአምራዊ መንገድ የሰው ሥጋ ይለብስ ዘንድ ድንግል ማርያም እንድትፀንስ ያደረገው ደግሞ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ እናነባለን (ሉቃስ 1፡35)። 

3. የአማኝ ድነት (ድነት (ደኅንነት))፡– ድነት (ድነት (ደኅንነት))ን የሰጠን የትኛው የሥላሴ አካል ነው? ሦስቱም ናቸው። እግዚአብሔር አብ፥ እግዚአብሔር ወልድና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ተካፋይ ነበሩ። እግዚአብሔር አብ፤ የሚያምኑትን ለኢየሱስ ክርስቶስ እንደሰጠ ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ አንዳቸውም እንዳይጠፉ እንደሚጠብቃቸው (ዮሐ 6፡35-40) ተጽፎአል። ነገር ግን ከኃጢአት ያጠባንና ያነጻን ደግሞ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ተነግሮናል (ቲቶ 3፡3-7)። 

እያንዳንዱ የሕይወታችን ክፍል የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ማኅተም አለው። የፈጠረን፥ ያበጃጀንና እከላዊ ህልውናችንን የዕጣን ቤተሰባችንን፥ እገራችንን፥ ዜግነታችንን ወዘተ… የመረጠ እርሱ ነው (መዝ (139) በእድገታችን ወቅት እየተከባከበን እርሱ የሚፈልገውን ዓይነት ሰው እንድንሆን የሕይወታችንን ልዩ ልዩ ሁኔታዎች ያደራጀልን መንፈስ ቅዱስ ነው (ዮሐ 5፡16)። በኃጢአት ሞቶ ወደ ነበረው ልባችን መጥቶ በመሥራት ክርስቶስ ለደኅንነታችን ያደረገውን ጥሪ እንድንሰማ ያደረገ በዚህም በኢየሱስ እንድናምን ልባችንን ያነሣሣና የእግዚአብሔር ልጆች እንሆን ዘንድ ያስቻለንም መንፈስ ቅዱስ ነው (ዮሐ 5፡26፤ 16፡6~1)። ኃጢአትን እንድናሸንፍ በየዕለቱ የሚያስፈልገንን ኃይል የሚሰጠን፥ (ሮሜ 8፡13) ኢየሱስ ክርስቶስን እንድናገለግል ስጦታዎችን የሚሰጠን፥ ክርስቶስን ወደ መምሰል እንድንለወጥ የሚረዳንና እግዚአብሔር ወደ ቤቱ ወደ መንግሥተ ሰማየት እስከሚወስደን ድረስ የሚጠብቀን እራሱ መንፈስ ቅዱስ ነው። አሁን የያዝነውን እኛነታችንን ያበጀው ከሥላሴ አካላት አንዱ የሆነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነው። አመስኑት! እወቁት! 

ጥያቄ፡– ከእግዚአብሔር የተቀበልካቸውን በረከቶችህን ዘርዝር። ይህን ፍቅር ያሳዩህንና በረከቶችህን የሰጡህን እያንዳንዱን የሥላሴ አካላት ለማመስገን ጊዜ ውሰድ። 

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

1 thought on “በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ”

  1. ጌታ ዘመን አገልግሎታችሁን ይባርክ አጠቃላ ይ በሚትሰጡት መንፈሳዊ ትምህርት ተጠቃሚ ነኝ

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading