በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ጥያቄ፡- የሐዋ. 4፡5-13፤ 28-31፤ 5፡1-12፤ 29-32፤ 6፡1-10፤ 7፡51፤ 8፡1፡1-25፤ 26-29፤ 39-40 አንብብ። በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስና ከእያንዳንዱ ክርስቲያን ጋር ስላለው ንኙነት የተጠቀሱትን የተላያዩ እውነቶች ዘርዝር። 

ሀ. መንፈስ ቅዱስ በሌሎች ፊት በግልጽና በድፍረት ለመናገር የሚያስችል ኃይልና ችሎታን ሰጠ፡- በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ በተደጋጋሚ መንፈስ ቅዱስን ስለመሞላት የተጠቀሱ ክፍሎችን ስንመለከት ከተአምራት፥ በልሳናት ከመናገር ወይም ከመስበክ ጋር የተያያዙ አለመሆናቸውን ልብ ማለት መልካም ነው። ይልቁኑ በመንግሥታት መሪዎች ፊት ቆመው መልስ በሚሰጡበት ወቅት ኢየሱስ አስቀድሞ ስላ መንፈስ ቅዱስ እንደተናገረው ኃይል እንደሰጣቸው እንመለከታለን (በማቴ. 10፡17-20)። ደቀ መዛሙርት ተቃውሞን የሚቋቋሙበትንና ወንጌልን በግልጽነት የሚሰብኩበትን ድፍረት የሰጣቸው መንፈስ ቅዱስ ነው። ደቀ መዛሙርት በዚህ መልክ በሚገባ ወንጌልን ይናገሩ በነበሩበት ጊዜ የሕዝብ መሪዎች ከኢየሱስ ጋር የነበሩ መሆናቸውን እንዳወቁ እንመለከታለን የሐዋ. 4፡13)። ቆይተው ደቀ መዛሙርት የጸለዩት ተአምራትን እንዲያደርጉ ሳይሆን ወንጌልን በፍጹም ግልጽነት እንዲናገሩ ነበር። እግዚአብሔር የጸሎታቸውን መልስ ሰጠ። የነበሩበት ስፍራ ተናወጠ፥ «በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው።» የዚህ ሙላት ውጤት ምን ነበር? «የእግዚአብሔርን ቃል በግልጥነት መናገራቸው ነበር።» (የሐዋ. 4፡31)። እስጢፋኖስ በድንጋይ በተወገረ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በግልጥ እንዲናገር ከማስቻሉም ሌላ ወደ ሰማይ በማተኮር ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲመለከት አድርጎት ነበር። 

ለ. መንፈስ ቅዱስ ደቀ መዛሙርት ታላላቅ ተአምራትን እንዲያደርጉ አስቻላቸው፡= በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ደቀ መዛሙርት ሰዎችን መፈወስን፥ አጋንንትን ማስወጣትን የመሳሰሉ ተአምራቶችን በተደጋጋሚ ማድረጋቸውን እንመለከታለን። እነዚህ ተአምራት ስደቀ መዛሙርት ሕይወት መንፈስ ቅዱስ የመኖሩ ቀጥተኛ ምልክት ሆነው የቀረቡበት ጊዜ ግን ፈጽሞ የለም። በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ውጤት ተደርገውም አልቀረቡም። ነገር ግን የመንፈስ ቅዱስ ህልውና አንዳንድ ክርስቲያኖችን ወንጌልን በልጽነት እንዲሰበኩ ማድረግ ብቻ ሳይሆን የመልእክታቸውን እውነተኛነትና ሥልጣን ለማረጋገጥ ተአምራትን እንዲያደርጉ ችሎታን እንደሰጣቸው መገመት እንችላለን። ተአምራትን የማድረግና ወንጌልን የመስበክ ሥራ ብዙ ጊዜ ተቆራኝተው የሚቀርቡ መሆናቸው የሚያስገርም ነው። የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ትኩረት የወንጌል መስበክ ነው። ተአምራትን ማድረግ ተቀዳሚ የአገልግሎት ዓላማው ሆኖ የቀረበበት ስፍራ ፈጽሞ የለም። ደቀ መዛሙርት ያለ ወንጌል ስብከት ተአምራትን ላለማድረጋቸው የተጻፈ አንድም ስፍራ አናነብም። ተአምራትን ሳያደርጉ ወንጌል ስለመሰበካቸው ግን እናነባለን። ይህ የሚያመለክተን የደቀ መዛሙርት ተቀዳሚ ዓላማዎች የእግዚአብሔርን ቃል መስበክ እንጂ ተአምራትን ማድረግ እንዳልነበረ ነው። በተጨማሪ የ መዛሙርት ተአምራትን ያደረጉት በቅድሚያ ለክርስቲያኖች ጥቅም እንደነበረ አናነብም። ሐዋርያት ትኩረታቸው ፈውስ ላይ አልነበረም። ይልቁኑ ውላ ሆነ አጋንንትን የማውጣት ተግባር ያተኮረው በቅድሚያ ሰማያምኑ ሰዎች ላይ ነበር። «ሕዝቡም የፊልጶስን ቃል በሰሙ ጊዜ ያደርጋት የነበረውን ምልክት ባዩ ጊዜ፥ የተናገረውን በአንድ ልብ እደመጡ» ተብሎ ተጽፎአ ( የሐዋ. 8፡6)። በኋላም የሚቀጥለውን ቃል እናገኛለን። «ምልክትና ድንቅ በእጃቸው ይደረግ ዘንድ እየሰጠ ለጸጋው ቃል ስለ መሰከረው ለለ ጌታ ገልጠው እየተናገሩ ረጅም ወራት ተቀመጡ።» (የሐዋ. 14፡3)። ተአምራትን የማድረግ ሥራ እንደ ሐዋርያት ባሉ የተወሰኑ ክርስቲያኖችና እንል እስጢፋኖስ ባሉ ስጦታ በነበራቸው ሌሎች ጥቂት የቤተ ክርስቲያን መሪ የተከናወነ ይመስላል። ለሁሉም ክርስቲያኖች የሚሰጥ ስጦታ አልነበረም፡፡ 

ሐ. መንፈስ ቅዱስ የቤተ ክርስቲያን መሪዎችን በትክክል እንሩ አስችሎአቸዋል (የሐዋ. 1፡6)። የክርስቲያኖች ቁጥር ሐዋርያት በረ ሊመሯቸው ወደማይችሉበት ደረጃ ሲደርስ ለሚነሡት አንዳንድ ችግሮች መፍትሔ መስጠት እንዲቻል ሌሎች መሪዎች ተመረጡ። መመረጥ የነበረባቸው እንዴት ነበር? ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስና ጥበብ የሞላባቸውን ሰዎች እንዲመርጡ ለደቀ መዛሙርት ነገሩአቸው። የተመረጡት ሰባት መሪዎች ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የቅርብ ግንኙነት እንዳላቸው በሕይወታቸው ያረጋገጡ ነበሩ። ይህ በሕይወታቸው የተረጋገጠው እንዴት እንደነበር አልተጻፈም። ነገር ግን ሕዝቡ ልዩነቱን ስለሚያውቁ ለመመስከር ችለው ነበር። መንፈስ ቅዱስ ከሰባቱ ጋር እንደነበር እና የእዚአብሐርን ሕዝብ ለመምራት ጥበብ እንደነበራቸው ያውቁ ነበር። 

መ. ሰዎች መንፈስ ቅዱስን ሊዋሹት፥ ሊፈታተኑትና ሊቃወሙት ይችላሉ ( የሐዋ. 5፡1-11)። ይህ መንፈስ ቅዱስ ዝም ብሎ ኃይል ብቻ እንዳይደለ ነገር የን እካላዊ ህልውና ያላውና ከሰዎች ጋር ሕያው የሆነ ቀንኙነት የሚያደርግ መሆኑን ያመለክታል። መንፈስ ቅዱስ፥ ለፊልጶስ ኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ እንዲያነጋግር ግልጽ የሆነ ትእዛዝ ሰጥቶታል (የሐዋ. 8፡29)። 

ሠ. መንፈስ ቅዱስ ለሰማርያ አማኞች በሐዋርያት እጅ መጣን ተሰጠ። (ወደፊት በምናጠናው ትምህርት ስለዚህ ጉዳይ በጥልቀት እንመለከታለን። የሐዋ. 8፡14-17) 

ጥያቄ፡- ሀ) ዛሬ በቤተ ክርስቲያን ከእነዚህ አንዳንዶቹ ወይም ሁሉም የመንፈስ ቅዱስ እገልግሎቶች አስፈላጊ የሆኑት በምን መንገድ ነው? ለ) መንፈስ ቅዱስ በቤተ ክርስቲያንህ ተመሳሳይ ነገሮች ያደረበትን ጊዜ ግለጽ።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 ) በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading