መግቢያ

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ዮሐንስ ጌታን የሚወድ አዲስ ክርስቲያን ነበር። ኢየሱስ ከኃጢአቱ እንዳዳነው ያውቃል። ልቡ በደስታ የተሞላ ከመሆኑ የተነሣ እግዚአብሔር በሕይወቱ ስላደረገው ለውጥ ላገኛቸው ሰዎች ሁሉ ይናገር ነበር። አንድ ቀን አንድ ክርስቲያን አገኘውና መንፈስ ቅዱስ ተሞልተሃልን? በማለት ጠየቀው። ጥያቄውም ራ አጋባው። «ወመንፈስ ቅዱስ እርሱ ማን ነው? ወይም ምንድን ነው? መንፈስ ቅዱስ እንደተሞላሁ እንዴት አውቃለሁ?» በአእምሮው ጥርጣሬ ሞላሰትና ወዲያውኑ ደስታው ከእርሱ ተለየ። በርካታ ክርስቲያኖችን ስለ መንፈስ ቅዱስ የተለያዩ ጥያቄዎች መጠየቅ ጀመረ። አንዳንዶች ላላ መንፈስ ቅዱስ መጨነቅ አያስፈልግህም ኢየሱስ ብቻ ይበቃል አሉት። ይህን ወዳሉት ክርስቲያኖች ሕይወት ሲመለከት ግን ሕይወታቸው ደስታ፥ ኃይል እና መታዘዝም የማይታይበት መሰለው። ሌሎች ደግሞ ስለ መንፈስ ቅዱስ ከመጠን በላይ ይናገራሉ። እንዳ በሆኑ ቋንቋዎች እየጮችና ሰውነታቸው እየተንቀጠቀጠ ይጸልያሉ። ለመንፈስ ቅዱስ መገኘት እውነተኛ ምልክት ይህ ነውን? ትክክለኛው ማን ነበር? ሰው ስለ መንፈስ ቅዱስ እውነተኛውን ነገር ለማወቅ ወደየት ነው መሄድ ያለበት? 

ጥያቄ፡– መንፈስ ቅድስን በሚመለከት በክርስቲያኖች መካከል ያለውን እንዲህ ያለ ግራ መጋባት እንዴት አየኸው? 

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በኢትዮጵያም ሆነ በዓለም ዙሪያ እጅግ አስደናቂ በሆኑ መንገዶች እየሠራ ለመሆኑ ምንም የሚያጠራጥር ነገር የለም። በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች በእምነት ወደ ክርስቶስ እየመጡ እየጻኑ ነው። ሰዎች መንፈሳዊና ሥጋዊ ፈውስን እያገኙ ናቸው። በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ክፍተኛ መንፈሳዊ ረሃብ በሕዝቡ ሕይወት ይታያል። በዚህች ታላቅ ምድር ለመኖርና ለመሥራት መታደላችን እንዴት ደስ የሚያሰኝ ነው! 

ይሁንና፥ ይህ ዘመን በርካታ አብያተ ክርስቲያኖቻችንን እየበከሉ ኑፋቄዎችና ሐሰተኛ ትምህርቶች በምድሪቱ በፍጥነት የሚስፋፉበትም ነው። እራሱን የብርሃን መልአክ አድርጐ የሚያቀርበው ሰይጣን (2ኛ ቆሮ. 11፡14) በሥራ ላይ ነው። አብዛኛው የሰይጣን ሐሰተኛ ትምህርት የሚያተኩረው በመንፈስ ቅዱስ፥ ህልውናው በሚረጋገጥበት መንገድ እና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ባለው ተቀዳሚ ሚና ላይ የተሳሳቱ አሳቦችን በመናኘቱ ተግባር ላይ ነው። ሰይጣን ግራ መጋባትን ለመፍጠርና የእግዚአብሔርን ሥራ ለማደናቀፍ የሚያደርጋቸውን ሙከራዎች ነቅተን መገንዘብ አለብን። 

አንድ ሰው ስለ መንፈስ ቅዱስ መጽሐፍ ለመጻፍ በሚነሣበት ወቅት ከአሳቡ ጋር የማይስማሙ በርካታ ክርስቲያኖች ሊገጥሙት እንደሚችሉ ገና ከጅምሩ ያውቀዋል። መንፈስ ቅዱስ ማን ነው? ዛሬ በዓለም ላይ የሚሠራው ሥራና ዓላማው ምንድን ነው? ህልውናው የሚገለጠው እንዴት ነው? በልሳናት በመናገርና በተአምራታዊ ፈውሶች ነውን? እነዚህ ጥያቄዎች በሺህ በሚቆጠሩ ክርስቲያኖች የሚጠየቁ ሲሆን፥ በበርካታ የተለያዩ መንገዶችም ክርስቲያኖች መልስ ይሰጡባቸዋል። የሚያሳዝነው ሰይጣን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እጅግ አስፈላጊ ከሆኑት እውነቶች አንዱ የሆነውን የመንፈስ ቅዱስ በክርስቲያኖች ማደር ጉዳይ ወደ ጸብና ክርክር መለወጡ ነው። አንድነታችን እንቆብርና በኃይል ተሞልተን ወንጌል የሚጠይቀውን ዓይነት ሕይወት መኖር እንድንችል እግዚአብሔር ላቤተ ክርስቲያን የሰጠውን መንፈስ ቅዱስ ሰዎች በተሳሳተ መንገድ ይረዱታል። በዓለም ዙሪያ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ታላቅ መከፋፈልን ላማምጣት ሰይጣን ይህን ሁኔታ እየተጠቀመበት ነው። ይህ እንዴት አሳዛኝ እውነታ ነው! በክርስቲያኖች መካከል በሚከናወን እንዲህ ዓይነት መከፋፈል አንጀቱ የሚርሰው ሳይጣን ብቻ ነው። 

ጥያቄ፡- በኢትዮጵያ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት በመንፈስ ቅዱስ ወይም ከአገልግሎቶቹ በአንዱ ክርስቲያኖች እንዴት ሊለያዩ እንዳየህ ግለጽ። 

የዚህ የጥናት መጽሐፍ ዓላማ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሚያስተምረውን መመርመር ነው። ጌታን የሚወዱና የሚያገለግሉ ግን ስለ መንፈስ ቅዱስ የተለዩ እምነቶች ያሏቸው ክርስቲያኖች እንዳሉ ሰላማውቅ፥ ስለ መንፈስ ቅዱስ ሚዛናዊ የሆነ አመለካከትን ለማቅረብ እሞክራለሁ። ጸሎታችን እግዚአብሔር በአብያተ ክርቲያናት መካከል አንድነትን ለማምጣት ይህን መጽሐፍ እንዲጠቀምበትሩ ክርስቲያኖች ዛሬ በየአብያተ ክርስቲያናቱ ሾልከው በመግባት የሚሰጡትን ትምህርቶች በመቀበል ወደ ስሕተት እንዳይወድቁና ሁሉ በላይ ደግሞ «በመንፈስ እንመላለስ። (ገላ. 5፡5) ዘንድ እንዲረዳን ነው። መልስ የምንሰጥበት ተቀዳሚ ጥያቄ «መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሚያስተምረው ምንድን ነው?» የሚለውን ነው።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

2 thoughts on “መግቢያ”

  1. yifat denbarga

    ይህንን እንድታዘጋጁ ጸጋዉን የሰጣችሁን እና በእናንተ ዉስጥ የሰራዉን እግዚአብሔርን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አመሰግናለሁ እባርካለሁ። በጣም ጥሩ ድህረ ገጽ ነዉ ባጣም እየተማርኩበት ነዉ ተባርኬአለሁ።ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ይባርካቸሁ ቀጥሉበት።

  2. ውድ ቤተ ሰቦቼ ተባረኩልኝ!!! የጌታ ጸጋ ከዚህ በላይ ይብዛላችሁ!!!
    (የዘወትር ተከታታያችሁ ገበየሁ ነኝ)

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading