የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ ትምሕርት ጥናት

አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን

አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ምንድን ናት?  ዛሬ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ምን ምን ማሟላት አለባት? በሚለው ጥያቄ ላይ ሰፊ ውይይት አለ። ቤተ ክርስቲያን ሁለት ወይም ሦስት አማኞች በኢየሱስ ስም የሚያደርጉት ስብሰባ ነው? ምን ያህል ድርጅት ያስፈልጋታል? ለቤተ ክርስቲያን አባልነት ጥምቀት አስፈላጊ ነው? የሚሉና ሌሎችም ጥያቄዎች ይነሱ ይሆናል። አዲስ ኪዳን ስለ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የሚያስረዳው ግልጥ ማብራሪያ የሌለ መሆኑ ያሳዝናል። የጉባኤው እንቅስቃሴ እንዴት መካሄድ አለበት? ለሚለው ጥያቄ ነው መጽሐፉ መልስ የሚሰጠው። እኛም ከዚህ መንደርደሪያ አሳብ በመነሳት ስለ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ምንነት የሚከተለውን ማብራሪያ ለመስጠት ሞክረናል። በአዲስ ኪዳን እንደምናየው አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ክርስቶስን የተቀበሉ አማኞች ጉባኤ ሲሆን አባላቱም የተጠመቁና የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማድረግ የተደራጁ መሆን አለባቸው። ማለት፡- 1. የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አባል የሚሆነው ማመኑን የገለጠ ሰው ብቻ ነው፤ 2. አዲስ ኪዳን ያልተጠመቀ ሰው የቤተ ክርስቲያን አባል ስለመሆኑ የሚገልጠው ነገር የለም፤ 3. ቤተ ክርስቲያናት በተቻለ መጠን በፍጥነት ነበር የሚደራጁት (ሐዋ. 14፡23)። ሰለዚህ በአሁኑ ጊዜም ቢሆን ያልተደራጀ የአማኞች ኅብረት፥ ቤተ ክርስቲያን ተብሎ ሊጠራ አይችልም፤ 4. ቤተ ክርስቲያን ዓላማ አላት። ይህም በተለያየ መንገድ የሚገለጠውን የእግዚአብሔር ፈቃድ መፈጸም ይሆናል (የተለያዩ ትእዛዞችንና ሥርዓቶችን መፈጸም፥ በየትኛውም የዕድሜ ክልል፥ በየትኛውም የዓለም ክፍል ላሉ ሰዎች አገልግሎት መስጠት ወዘተ.)።  ይህ የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ትርጉም በወጉ ቢገለጥም የሁለትና ሦስት ሰዎች ለኅብረት መሰብሰብ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አያሰኘውም። ምክንያቱም ይህ ዓይነቱ ጉባኤ፥ ቢያንስ በአካባቢው ላሉና በየዕድሜው ክልል የሚገኙ ሰዎችን ለማገልገል የተዘጋጀ አይሆንም። እንዲሁም የክርስቲያን ትምህርት ቤት፥ ወይም ከቤተ ክርስቲያን ውጭ የሆነ ክርስቲያናዊ ድርጅት ቤተ ክርስቲያን ሊሆን አይችልም።  እርግጥ ይህ መግለጫ የሚለዋውጥበት ሁኔታ ይኖራል። አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የግድ ለሷ ተብሎ በተሠራ ሕንፃ ውስጥ ትሰብሰብ አይልም። ምን ዓይነት ወይም ስንት ስብስሳዎች መካሄድ እንዳለባቸው አያመለክትም። እንዲሁም ስለ ጥምቀት ዓይነትና ስለ መሪዎች አመራረጥ (ወደፊት በስፋት እናየዋለን) አይወሰንም። የመግለጫው ዋና ጥረት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ከሌሎች ቡድኖች፥ ከዚያም አልፎ ከቤተ ክርስቲያናት ጋር ከተዛመዱ ድርጅቶች የምትለይበትን ሁኔታ ለማመልከት ነው።  እነማን ናቸው የቤተክርስቲያን መሪዎች?  ቤተ ክርስቲያን አመራር ይኖራት ዘንድ መለኮታዊ ትእዛዝ ነው (ዕብ. 13፡7፥ 17)። መደራጀት ሥጋዊ ድርጊት፥ ወይም ስሕተት አይደለም። ሰዎች ግን ለዚህ ጉዳይ ከመጠን ያለፈ ትኩረት ይሰጡታል። አንዳንዶች ድርጅቱ እጅግ ሳይሰፋ አነስተኛ ቢሆን ይመረጣል ይላሉ፥ በተግባር ሲታይ ግን የበቂ ድርጅት አለመኖር የታሰበውን ሥራ ያደናቅፋል። በሌላ አቅጣጫ ስናየው ደግሞ አንዳንድ ቤተ ክርስቲያናት እጅግ ከመጠናከራቸው የተነሳ የቤተ ክርስቲያኑ መሪ (እግዚአብሔር) የሚሰጠው ምክርም ሆን ውሳኔ ተቀባይነት የሚያጣበት ጊዜ ይኖራል። ያም ሆነ ይህ ቤተ ክርስቲያን መሪዎች የሚያስፈልጓት ስለመሆኑ በአዲስ ኪዳን በየደረጃው ተገልጧል።  1.ሽማግሌዎች። ያለጥርጥር ሽማግሌዎች የአዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን ዋና መሪዎች ነበሩ። ብዙዎች ባይስማሙበት እንኳን፥ ሽማግሌዎችና ጳጳሳት በቤተ ክርስቲያን እኩል ሥልጣን እንዳላቸው ይገመታል። ሽማግሌ የሚለው ቃል ሥልጣንን ሲያመለክት፥ ጳጳስ የሚለው ደግሞ ሥራ አስፈጻሚነትን፥ አጠቃላይ ተቆጣጣሪነትንና ከበላይ ሆኖ መመልከትን ይገልጣል። ቢያንስ ቢያንስ በኤፈሶን ቤተ ክርስቲያን የሽማግሌና የጳጳስ ሥራ ተመሳሳይ ነበር (ሐዋ. 20፡17፥ 28)። በመሆኑም ሽማግሌዎች ከአጠቃላይ ሥራቸው በተጨማሪ በመሪነትም አገልግለዋል (1ኛ ጢሞ. 5፡17)፤ እውነትን ጠብቀዋል፥ አስተምረዋል (ቲቶ 1፡9)፣ የገንዘብ ገቢና ወጪም ተቆጣጥረዋል (ሐዋ. 11፡30)። በእያንዳንዱ ቤተ ክርስቲያን ምን ያህል ሽማግሌዎች ነበሩ የሚለው ጥያቄ አከራካሪ ሆኗል። ምንም እንኳን በግልጥ እንደሚታየው ቤተ ክርስቲያናት በነበሩባቸው ከተሞች ብዙ ሽማግሌዎች ነበሩ (ሐዋ. 14፡23፤ ፊልጵ. 1፡1)። ነገር ግን በየመኖሪያ ቤቱ በሚካሄዱት ስብሰባዎች ላይ ብዙ ሽግሌዎች፥ ወይም አንድ ሽማግሌ ብቻ እንደነበር የታወቀ ነገር የለም። በ1ኛ ጢሞቴዎስ 3 ጳጳስ የሚለው ቃል (በነጠላ) ከቁ. 1-7 ተጠቅሷል፤ ሰለ ዲያቆናት ግን (በብዙ) ከቁ. 8-13 ተገልጧል። ሽማግሌዎች ለተለየ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በተለየ መንገድ ይመረጡ እንደነበር ደግሞ ከሚከተለው ጥቅስ ለመረዳት እንችላለን (1ኛ ጢሞ. 4፡14፤ ቲቶ 1፡5)።  የሽማግሌዎች መምረጫ ስለነበሩት መመዘኛ ነጥቦች በ1ኛ ጢሞቴዎስ 3፡1-7 እና ቲቶ 1፡5-9 ተብራርቷል። የመጀመሪያውን ጥቅስ እንደሚከተለው ዘርዝሮታል፡- የማይነቀፍ (ለወቀሳ ያልተጋለጠ) የአንዲት ሚስት ባል፥ (ይህ ማለት አንዲት ሚስት ብቻ ያገባ ማለት ሲሆን ቃሉም በግሪክ 1ኛ ጢሞቴዎስ 5፡9 ከተጠቀሰው ጋር አንድ ነው፤ ብዙ ሚስት ማግባት በግሪኮችና በሮማውያኑ ዘንድ የሚታወቅ አልነበረም፤ ወይም ከተፋቱ በኋላ የሚያገቡትንም የሚከለክል ሊሆን ይችላል)፥ ልከኛ፥ ራሱን የሚገዛ፥ እንደሚገባው የሚሠራ፥ እንግዳ ተቀባይ፥ ለማስተማር የሚበቃ፥ የማይሰክር፥ የማይጨቃጨቅ፥ የማይከራከር፥ ገንዘብ የማይወድ፥ ቤቱን በመልካም የሚያስተዳድር (የቤቱን ጥቂት ሰዎች በመልካም ሁኔታ ማስተዳደሩ፥ ቤተ ክርስቲያንን ለማስተዳደር የሚችል መሆኑን ያመለክታል)፥ አዲስ ክርስቲያን ያልሆነ (የበሰለ)፣ በኅብረተሰቡ ዘንድ መልካም ምስክርነት ያለው። በቲቶ መልእክት ውስጥ ያለው ክፍል ደግሞ በዚህ ላይ በመጨመር፥ የማይኮራ፥ የማይቆጣ በጎ የሆነውን ነገር የሚወድ (ሰዎችንም ሁኔታዎችንም)፥ ጻድቅና ቅዱስ (ንጹሕ) የሆነ የሚሉትን ያጠቃልላል።  የዚህ ሁሉ ዝርዝር ገለጣ አስፈላጊነት ቤተ ክርስቲያን መመራት የሚኖርባት ብቃት ባላቸው ሰዎች መሆኑን ለማስገንዘብና መመዘኛውን ከማያሟሉ ብዙ ሰዎች ይልቅ፥ ብቃት ባላቸው ጥቂቶች መመራት እንደሚሻላት ለመጠቆም ነው።  2. ከሽማግሌዎች በታች ያሉት ደግም ዲያቆናት ነበሩ። ዲያቆን የሚለው ቃል አገልጋይ ማለት ነው። ምንም እንኳን ክርስቲያኖች በሙሉ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ መሆን ቢችሉም፥ ዲያቆናት የታወቀ ልዩ አገልግሎት አላቸው። የሽማግሌዎች ረዳት ሲሆኑ (ሐዋ. 6፡1-6) በግልጥ የታወቀ የሥራ ድርሻም ነበራቸው (ፊልጵ. 1፡1)። የዲያቆናት ምርጫ መመዘኛ እንደ ሽማግሌዎች በጣም ዝርዝር ባይሆንም፥ አንዳንድ ተመሳሳይ መመዘኛዎችን ይጨምራል። በተለይ “በቃላቸው የሚታመኑ” (1ኛ ጢሞ. 3፡8) የሚል ቃል ታክሎበታል። ይህ የሚያስገነዝበን፣ ምናልባት ዲያቆናት ከምእመናን ጋር በየዕለቱ ፊት ለፊት የሚገናኙና ቤት ለቤት እየዞሩ እርዳታ የሚያደርጉ፥ የታመሙትን የሚጠይቁ በመሆናቸው፥ በዚህ አጋጣሚ ለአንድ ሰው አንድ ነገር፥ ለሌላው ሌላ እንዳይናገሩ ለማስጠንቀቅ ሲባል የተደረገ ይሆናል። በቲቶ መልእክት ዲያቆናት አለመጠቀሳቸው አሰፈላጊነታቸው ውሱን ነው ማለት አይደለም። ምናልባት የቀርጤስ ቤተ ክርስቲያን ትንሽ ከመሆኗ የተነሳ ዲያቆናት ሳያስፈልጓት፥ ወይም ዲያቆናት ኖረዋት ሽማግሌዎች ሳያስፈልጓት ቀርቶ ይሆናል።  3. ሴቶች ዲያቆናት ሊሆኑ ይችላሉን? በአዲስ ኪዳን ውስጥ ሁለት ጥቅሶች ብቻ ናቸው ሴት ዲያቆናት እንደነበሩ የሚያስረዱ (በሮሜ 16፡2)። ፌበን “አገልጋይ” ተብላ ተጠርታለች (ቃሉ “ዲያቆን” ማለት ነው)። ጥያቄው፣ የቃሉ አጠቃቀም የሚያስረዳው ይህች ሴት በድቁና የታወቀች (የሴት ዲያቆን) እንደነበረች ወይስ ተራ አገልጋይ? የሚል ይሆናል። ምናልባት (እንደ 1ኛ ቆሮንቶስ 16፡15 ገለጣ ከሆነ) አገልጋይ ብሎ መቀበሉ ይሻል ይሆናል። ሌላው ጥቅስ 1ኛ ጢሞ. 3፡11 ሲሆን እዚያም የተወሰኑ ሴቶች ስም ተጠቅሷል። እዚህም ላይ የሚነሳው ጥያቄ፥ እነዚህ ሴቶች የዲያቆናት ሚስቶች ናቸው? ወይስ ሴት ዲያቆናት? የሚል ይሆናል (ቃሉ በግሪክ “ሴቶች” ማለት ነው)። ሴት ዲያቆናት ቢሆኑ ኖሮ ስለ ዲያቆናት በሚገልጠው አንቀጽ መካከል ከሚሆን ይልቅ፥ ከቁጥር 13 በኋላ ሰለ ዲያቆናት የተሰጠው ማብራሪያ እንዳለቀ መጠቀስ ይኖርባቸው ነበር። ስለዚህ ምናልባት የዲያቆናት ሚስቶች ይሆናሉ የሚለውን አሳብ ያጠናክረዋል። በጥንቷ ቤተ ክርስቲያን፥ በግልጥ የታወቁ የሴት ዲያቆናት መኖራቸው በጣም አጠራጣሪ ነው።  4. በአዲስ ኪዳን ንብረት ጠባቂ የሚል የሥራ ድርሻ አልነበረም። ዛሬ ግን በማኅበሩ ስም የቤተ ክርስቲያንን ንብረት የሚጠብቁ ሰዎች አስፈላጊ ሆነዋል። የአዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያናት ስብሰባ የሚያደርጉት በየቤቱ ስለነበር ንብረት ጠባቂ አላሻቸውም። ዛሬ ግን ቤተ ክርስቲያናት የራሳቸው ሕንፃ ያላቸው ስለሆነ ንብረታቸው በግለሰቦች ሊያዝ አይገባም። በነገራችን ላይ በ2ኛ ቆሮንቶስ 8፡17-24 ገንዘብ ያዦችና የንብረት ባለ አደራዎች መኖራቸው ተገልጧል። እርግጥ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ አቋም ባልነበራት በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን የነዚህ ሰዎች አስፈላጊነት በአሁኑ ዘመን ካለው ሁኔታ እጅግ ይለያል፡፡ እስካሁን ስለ ቤተ ክርስቲያን አመራርና መሪዎቿ ተነጋግረናል። ነገር ግን የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የተከናወነው በእነርሱ ብቻ እንዳልሆነ ማስታወስ ጠቃሚ ነው። እነርሱ ይመራሉ፥ ያስተዳድራሉ፥ ይጠብቃሉ፥ ያገለግላሉ። ነገር ግን ስጦታ ያላቸው ሌሎች ሰዎችም በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ሊካፈሉ ይችሉ ነበር። ሽማግሌ ወይም

አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን Read More »

ቤተ ክርስቲያን በሚለው ፅንሰ አሳብ ውስጥ የሚካተተው ምንድነው?

እንዳንድ ክርስቲያኖች የሥነ-መለኮት ሰዎች እና የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ስለ ቤተ ክርስቲያን ምንነት ግራ የተጋቡ ይመስላሉ። ብዙ አማኞች ስለ ቤተ ክርስቲያን ያላቸው እውቀት፥ ቤተ ክርስቲያኒቱ የምትገኝበትን አካባቢ ከማወቅና የአምልኮ ቦታችን ነው ብሎ ከመናገር የሚዘል አይደለም። የሥነ-መለኮት ሰዎች፣ ለምሳሌ ቤተ ክርስቲያን መቼ ተጀመረች በሚለው መሠረታዊ ነጥብ ላይ ግራ ተጋብተውና የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችም፥ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር፥ ግብና እንቅስቃሴዋ የተለያየ አሳብ ይዘው እናገኛቸዋለን። በተጨማሪም በአሁኑ ጊዜ በብዙዎች ዘንድ ቤተ ክርስቲያን ከእንግዲህ የምትሰጠው ጥቅም የለም፤ እሷ የምትሰጠውን አገልግሎት ሌሎች ድርጅቶች ሊሠሩት ይችላሉ የሚል አመለካከት አለ።  በስሕተት ለተሞላ ለዚህ አመለካከት የሚሰጠው መልስ፥ እግዚአብሔር ለቤተ ክርስቲያን የሚሠራውን ሥራ አላቋረጠም የሚል ይሆናል። የቱንም ያህል በስሕተት ብትወድቅና ዓለማዊ ብትሆን፥ ክርስቶስ አሁንም በቤተ ክርስቲያን ሊሠራ ይፈልጋል (ራእይ 2-3)፤ እግዚአብሔር ለሥራ የመረጣቸው ሁለት ድርጅቶች፥ ቤትና ቤተ ክርስቲያን ናቸው። ይህ ሲባል ግን እግዚአብሔር እንደ አስፈላጊነቱ በሌሎች ድርጅቶች አይጠቀምም ማለት ሳይሆኑ የመጀመሪያ ዓላማዎቹን ለማከናወን የሚጠቀምባት ቤተ ክርስቲያን መሆኗን ለማጠናከር ነው። ቤተ ክርስቲያንን ስንተው የእግዚአብሔርን ድርጅት መተዋችን ነው (1ኛ ጢሞ. 3፡15)።  ቤተ ክርስቲያን ብለን የተረጎምነው የግሪክ ቃል ከሁለት ቃላት የተውጣጣ ሲሆን ትርጉሙ “የተጠሩ” ማለት ነው። ጐባኤ ወይም ስብሰባ ማለትም ይሆናል። የማን ጉባኤ? የሚለውም ጥያቄ መልስ ይሻል። ስለሆነም ጕባኤ የሚለው ቃል እንደ ሌሎቹ ጠቃሚ ቃላት ሁሉ ሊብራራ ይገባል። 1. አንዳንድ ጊዜ (በአዲስ ኪዳን እንኳን) የአንድ ከተማ ጉባኤ ስንል፥ ለተወሰነ ዓላማ የተጠራ የሕዝብ ስብሰባ ማለት ይሆናል (ሐዋ. 19፡32፥ 39፣ 41)፣ 2. በአንድ ወቅት ደግሞ፥ በበረሃ የተደረገን የአይሁድ ሕዝብ ጉባኤ በማስመልከት ተጽፏል (ሐዋ. 7፡38)፤ 3. ብዙ ጊዜም በአንድ አካባቢ የሚኖሩ ክርስቲያኖችን ለማመልከት አገልግሏል (1ኛ ቆሮ. 1፡2፤ 1ኛ ተሰ. 1፡1፤ ራእይ 1፡11 እና ሌሎችም) 4. በመጨረሻም “ቤተ ክርስቲያን” የሚለው ቃል “ሁሉን አቀፍ የሆነች ቤተ ክርስቲያን” የሚል ትርጉም ተሰጥቶት ይገኛል። ይህም በሁሉም ዘመናት የነበሩ የሰው ዘሮችን በሙሉ የሚያካትቱ አማኞችን ማለት ሲሆን “የክርስቶስ አካል” ከሚለው ጋር ተመሳሳይ ነው (ማቴ. 16፡18፤ ኤፌ. 1፡22-23፤ 3፡10፥ 21፤ 5፡23፥ 25፣ 27፥ 29፥ 32፤ ቈላ. 1፡18፤ ዕብ. 12፡23) መሆኑን ያመለክታል።  ሲጠቃለል “ቤተ ከርስቲያን” የሚለው ቃል ሰዎች የሚሰበሰቡበት ቤት ሳይሆን፥ ለጉባኤ የተጠሩ ሰዎች እንደማለት ነበር። የጉባኤው ዓይነት ቃሉ ከሚገኝበት ምንባብ ይዘት የሚታወቅ ይሆናል። የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ከላይ 3ኛውና በ4ኛው ተራ ቁጥር የተጠቀሱትን ብቻ ያካትታል። ምንጭ፡- “የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ ትምህርት ጥናት”፣ በዶክተር ቻርልስ ሲ. ራይሪ ተጽፎ፣ በሲሳይ ደሳለኝ የተተረጎመ እና በየላፕስሊ/ብሩክስ ፋውንዴሽን የታተመ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

ቤተ ክርስቲያን በሚለው ፅንሰ አሳብ ውስጥ የሚካተተው ምንድነው? Read More »

የድነት (የደኅንነት) ቃላት

ድነት (ደኅንነት) በእምነት ብቻ የሚገኝ መሆኑ በአዲስ ኪዳን ከ200 ጊዜ በላይ ተገልጧል። ይህም እምነት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ፋንታ ስለ ኃጢአታችን እንደሞተ መገንዘብና መቀበል ነው (ዮሐ. 3፡16፤ ሐዋ. 16፡31)። ድነት (ደኅንነት) ነጻ ስጦታ ነው። ስለዚህ በማንኛውም ሁኔታ ቢሆን ድነትን እኛ ለእግዚአብሔር አንዳች ስጦታ አበርክተን እንዳገኘነው ከማስመሰል መጠንቀቅ ይኖርብናል። እርሱ ሁሉንም ስለሰጠን፥ በእምነት እንቀበላለን (ዮሐ. 1፡12)።  ድነት በእምነት አማካይነት በጸጋ እንደሚገኝ የማይገልጥ ልዩ ወንጌል መስበከ፥ በገላትያ 1፡8-9 ያለውን መርገም [Anathema/አናቴማ] ያስከትላል። እንዲህ ዓይነት የሐሰት ወንጌል ዋጋ ቢስ (ውጉዝ) ነው። ይህ ከባድና ብርቱ ማስጠንቀቂያ ቢሆንም፥ ባለንበትም ሆነ ባለፉት ዘመናት ብዙዎች የሐሰት ወንጌል ሰብከዋል።  ማመንና ራስን መስጠት  እዚህ ላይ ትልቁ ጥያቄ፡- ለመዳን ክርስቶስን እንደ ሕይወት ጌታ መቀበል ያስፈልጋልን? የሚል ነው። በአሁኑ ጊዜ ብዙዎች አዎን ያስፈልጋል ይላሉ። ለምሳሌ በጣም የታወቀ አንድ ጸሃፊ ወንጌልን በተሳሳተ ሁኔታ ሰለሚያቀርቡ ሰዎች ሲጽፍ፥ “ከሰዎች የሚፈለገው፥ ጌታን የኃጢአት ተሸካሚ አድርገው እንዲያምነት ብቻ ነውን? ራሳቸውን በመካድ የሕይወታቸው ገዥ ሊያደርጉትስ አይገባም?” ብሏል። በሌላ አባባል አንድ ሰው ለመዳን በጌታ ማመንና ራሱን ለርሱ ቁጥጥር አሳልፎ መስጠት አለበት። ሕይወት መስጠትን ባያጠቃልልም እንኳን፥ አንዳንድ ጊዜ ራስን የመስጠት ፈቃደኝነት ሊኖር ይገባል ይባላል። ይህ ቢያንስ ለሥጋዊ ክርስቲያኖች መኖር (ዛሬ በጣም ብዙ ናቸው) በር ይከፍታል። ታዲያ ፈቃደኝነትና እምነት በድነት ወቅት የሚያስፈልግ ከሆነ ምን ያህል ፈቃደኝነት ነው የሚያሻው? ለመዳን ራስን አሳልፎ መስጠት ካስፈለገ፥ ለምንድን ነው ታዲያ አዲስ ኪዳን የዳኑ አማኞች ጭምር ራሳቸውን እንዲሰጡ የሚጠይቅ (ሮሜ 12፡1)?  ይህን ትምህርት በተመለከተ አራት ነገሮችን ለመጥቀስ ይቻላል፡- 1. የሰዎች እምነት ጥልቀት እንዲኖረው ከመጓጓት የመነጨ ቅን ሙከራ ነው፣ 2. “ጌታ” የሚለው ቃል፥ ያሉትን የተለያዩ ትርጉሞች ካለመረዳት ነው፤ 3. አማኙ ሕይወቱን በእግዚአብሔር ዓላማ መምራትን በመማሩ ረገድ እያደገ የሚሄድበት መንገድ ግልጥ አይደለም፤ 4. በቀላሉ “ማመን ብቻ” የሚለውን አሳብ ለመቃወም ነው፤ እርግጥ የነገሩ መጨረሻ የሚወሰነው መጽሐፍ ቅዱስ ስለማመን፥ ስለመታዘዝና ራስን ስለመሰጠት የሚገልጠው እውነት ላይ በመመሥረት ብቻ ይሆናል።  ጥልቀት የሌለው እምነት ቃሉ በሚሰበክበት ጊዜ የምንጠብቀው ጉዳይ መሆኑን ጌታ ራሱ ገልጧል (ሉቃስ 8፡12-15)። ራሳቸውን ያልሰጡ ብዙ አማኞች እንደነበሩ ለሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት በራእይ 2-3 በተጻፈው ደብዳቤ ተገልጧል (በተለይ ራእይ 2፡13-14፥ 2፡19-20ን በጥንቃቄ ይመልከቱ)። ሥጋዊ ክርስቲያኖች ለሽልማት ባይበቁም፣ ሕይወታቸው እንደሚድን ተጽፏል (1ኛ ቆሮ. 3፡15)። አንድ ሰው የውሽት አማኞችና ሐሰተኛ ሊቃውንት በቤተ ክርስቲያን እንዳይኖሩ ቢመኝም፥ እንደ መጽሐፍ ቅዱስ አባባል ይህ የማይቻል ነገር ነው።  “ጌታ” የሚለው ቃል የተለያዩ ትርጉሞች አሉት። አንዳንዴ የማዕረግ፥ ወይም የአክብሮት ቃል ይሆናል፣ “ጌቶች” እንደምንለው ዓይነት ( ዮሐ. 4፡11)። አንዳንድ ጊዜም የበላይ አለቃ እንደማለት ነው (ሉቃስ 6፡46)። በአዲስ ኪዳን ያለው አብዛኛው ትርጉም ግን፥ በብሉይ ኪዳን “ያህዌ” ከሚለው የእግዚአብሔር ስም ጋር የሚስተካከል ነው። የናዝሬቱ ኢየሱስ አምላክነቱን በገለጠና ተከታዮቹም ጌታ (ጌታ ኢየሱስ) ባሉት ጊዜ እሱ (የናዝሬቱ ኢየሱስ) ሥጋ የለበሰ የብሉይ ኪዳኑ ያህዌ ለመሆኑ ግልጥ ማስረጃ ነበር። አምላክ ሰው ለሆነበትም መግለጫ ነበር። “ክቡር ኢየሱስ” ቢባል፥ ወይም ሌላ የማዕረግ ስም ቢሰጠው ኖሮ፣ በጊዜው የነበሩ ሰዎች ሊወግሩት ወይም ሊሰቅሉት ባልተነሱ ነበር፤ “ያህዌ ኢየሱስ” መባሉ ነው ለሞት የዳረገው። እርግጥ በመለኮታዊነቱ ትርጉም መሠረት፡- ጌትነቱ ለአዳኝነት ተግባሩ ፍጹም አስፈላጊ ነበር። አዳኝ የማዳን ከህሎት ይኖረው ዘንድ፥ ሥጋ የለበሰ አምላክ መሆን ነበረበት፤ ለመሞት ሰው፥ ሞቱ ዋጋ ያለው የኃጢአት ከፍያ ይሆን ዘንድ ደግሞ፥ እግዚአብሔር መሆን አለበት። ይህ ነው የሮሜ 10፡9 እና የሐዋርያት ሥራ 2፡36 ትርጉም።  ደቀ መዝሙር ተማሪ ነው። ልክ እንደ ይሁዳ ያልዳኑ የጌታ ደቀ መዛሙርት ሊኖሩ ይችላሉ። ደቀ መዛሙርት የማፍራት ተግባር ያመኑትን በማጥመቅና ያለማቋረጥ በማስተማር ይከናወናል (ማቴ. 28፡19)። ግራ መጋባት የሚፈጠረው ለመንፈሳዊ እድገት የሚያስፈልጉ ነገሮችን ደቀ መዛሙርት ለመሆን እንደሚያስፈልጉ ግዳጆች አድርገን ስንወስድ፥ ወይም የደቀ መዛሙርትነት ባሕርያትን ለደቀ መዝሙርነት መመልመያ መመዘኛ ስናደርግ ነው። እነዚህን ሁለት የደቀ መዝሙርነት ፅንስ አሳቦች ጌታ እንዴት ጎን ለጎን እንዳስቀመጣቸው በጥንቃቄ ያስተውሉ። በሉቃስ 14፡16-24 ላይ በተጠቀሰው ታላቅ የእራት ግብዣ ምሳሌ ወደ ግብዣው ማንም ሊገባ እንደሚችልና ጥሪው ለሁሉ ነጻ መሆኑን ሲጠቅስ፥ በሉቃስ 14፡25-33 ላይ እንዲሁ ደቀ መዝሙርነት ሳያቋርጡ እርሱን መከተል መሆኑንና ዕድሉም ለጥቂቶች የተወሰነ መሆኑን እስተምሯል። እነዚህን የአገልግሎት መመዘኛዎች የሕይወት ማግኛ ግዴታዎች ማድረግ ግን ወንጌልን ማምታታትና እንደ ንጹሕ ውኃ የጠራውን የእግዚአብሔር ጸጋ በሰው ሥራ ማደፍረስ ነው። በተጨማሪም ደቀ መዝሙርነት ድርጊትን እንጂ፥ ፈቃደኝነትን ብቻ እንደማይሻ ማስተዋል ይጠቅማል።  ለመሆኑ ራሳቸውን ያልሰጡና ያልታዘዙ፥ ግን የእውነተኛ አማኞች ምሳሌ የሆኑ ሰዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሉን? አዎ አሉ። በአዲስ ኪዳን “ጻድቅ” ተብሎ የተጠራው ሎጥ (2ኛ ጴጥ. 2፡7) በዘመኑ ሁሉ የእግዚአብሔርን ጌትነት ችላ ያለ ደካማ ሰው ምሳሌ ነበር። ጴጥርስ ለምሳሌ “ጌታ ሆይ አይሆንም” በማለት ለጥቂት ጊዜም ቢሆን የጌታን ጌትነት አልቀበልም ብሎ ነበር (ሐዋ. 10፡14)። ምናልባት በጣም ግልጥ የሆነው ምሳሌ፥ በኤፌሶን አማኞች ዘንድ የታየው ይሆናል (ሐዋ. 19፡8-19)። አንዳንዶች የአስማትና የጥንቆላ መጻሕፍታቸውን ከማቃጠላቸውና በእነዚህ መጻሕፍት መጠቀም ኃጢአት መሆኑን ከመናዘዛቸው በፊት ለሁለት ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ የዳኑ ነበሩ። በሌላ ቃል በአስማት መጻሕፍት መጠቀም እንደሌላባቸው ያወቁ፥ ግን ያላስወግዱ፤ ክርስቲያን ከሆኑ ሁለት ዓመት የሞላቸውና ከርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው የተቀበሉ ነበሩ። ያ ድርጊታቸው አማኝ ተብሎ ለመጠራት አልከለከላቸውም፡፡ ድነታቸው በእምነትና የአስማትን ዕቃ ለማስወገድ ፈቃደኛ በመሆናቸው ላይ የተመሠረተ አልነበረም።  ማመን ቀላል ነገር ነውን? በእምነት ውስጥ የሚካተቱት ነገሮች እስከታወቁ ድረስ መልሱ አይደለም ይሆናል። ምክንያቱም እምነታችን የማይታመንን ነገር እንዲታመን ሰለሚጠይቅ ነው። ይሄውም ሰዎች ባላዩት፥ ወይም ዛሬ በሕይወት ከሚኖሩ ሰዎች መካከል አይቼዋለሁ ብሎ የሚናገርለት ምስክር በማይገኝለት ሰው፥ በጓደኞቹ የተጻፈን ታሪክ ብቻ በመመልከት እንዲያምኑ ስለምንጠይቅ ነው። በእውነት በማይታየው ክርስቶስ ማመን ቀላል ነውን? እንዲሁም ሰዎችን በዚህ ባልታየው ሰው እንዲያምኑ፥ በርሱም ሞት ምክንያት የኃጢአት ይቅርታና የዘላለም ሕይወት እንዲያገኙ፥ የኃጢአታቸውም ዋጋ የተከፈለ መሆኑን አሜን ብለው እንዲቀበሉ እንጠይቃዋለን። ታዲያ ይህ ቀላል ጥያቄ ነው?  በዚህ ባልተቀየጠ የእግዚአብሔር ጸጋ ላይ አንዳች ነገር ሳይጨምሩ (ከበጎ አሳብ ቢመነጭም እንኳ) በመጀመሪያ የእምነትዎን መሠረት ለሰዎች በጣም ግልጥ ያደርጉላቸው፤ ደግሞም ስለ እርሱ ምን ማመን እንደሚገባቸው ያስረዷቸው። ከዚያም ወደ ጌታ ኢየሱስ፣ ሰው ወደሆነው አዳኝ፥ ላመኑ ሁሉ የዘላለም ሕይወትና የኃጢአት ይቅርታ ወደሚሰጠው አምላክ ያመልክቷቸው። ይህን ነው ጌታ ራሱ በምድራዊ አገልግሎቱ ወቅት ከኃጢአተኞች ጋር በመገናኘት ያከናወነው። ለሰማሪያይቱም ሴት “የእግዚአብሔርን ስጦታና ውኃ አጠጪኝ የሚልሽ ማን መሆንስ ብታውቂ አንቺ ትለምኝው ነበርሽ የሕይወትም ውኃ ይሰጥሽ ነበር” አላት (ዮሐ. 4፡10)። የጠየቃት ነገር ቢኖር ክርስቶስ (መሲህ) መሆኑን (ቁ. 26) እንድታውቅና የዘላለምን ሕይወት ስጦታ ከእርሱ እንድትቀበል ነበር። ለመዳን ይቻላት ዘንድ ውስብስብ የነበረውን የኃጢአት ሕይወቷን እንድታስተካክል አልነበረም የነገራት።  ማመንና መጠመቅ  ጥምቀት ከእግዚአብሔር የተሰጠና በጣም ጠቃሚ የሆነ የእምነት መመስከሪያ መንገድ እንጂ የድነት መመዘኛ አይደለም። ሳይጠመቁ ወደ መንግሥተ ሰማያት ሊሄዱ ይችላሉ (በመስቀል ላይ እንደነበረው ወንበዴ)። ጥምቀት ለድነት ያስፈልጋል የሚሉ ሰዎች (ሌሎች በመቶ የሚቆጠሩ ጥቅሶችን ወደ ጎን በመተው) አንዳንድ ጥቅሶችን ለመደርደር ይሞክራሉ። በሐዋርያት ሥራ 2፡38 ላይ ያለው ቃል “ኃጢአት ስለተሠረየ ተጠመቁ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል። እዚህ ላይ “አይስ” የሚለው የግሪክ መስተዋድድ የአማኙን የጥምቀት መሠረት ያመለክታል። መጠመቅ ያለበት ኃጢአቱ ይቅር እንዲባልለት ሳይሆን ኃጢአቱ ይቅር ስለተባለለት ነው። ይህ የመስተዋድዱ የተለመደ ትርጉም ባይሆንም፥ በማቴዎስ 12፡41 ላይ ይህን የመሰለ ትርጉም መቅረቡ እንደ ምሳሌ ሊቆጠር ይችላል። ስለዚህ የኃጢአት ሥርየት የመጠመቅ መሠረት እንጂ፥ የጥምቀት ዓላማ ሊሆን አይችልም።  የሐዋርያት ሥራ 22፡16 ጥምቀት የጳውሎስን ኃጢአት እንዳነጻ የሚናገር ይማሰላል። በትክክል ሲታይ ግን የጥቅሱ አሳብ ይህ አይደለም። በዚህ ቁጥር

የድነት (የደኅንነት) ቃላት Read More »

የአማኙ ዋስትና

ከእውነተኛ አማኝ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ነው የዘላለማዊ ዋስትና ጥያቄ ትምህርት መቅረብ ያለበት። እርግጥ በአንድ ወቅት ያምንበት የነበረውን እውነት የካደ የሚመስልን ሰው መዳን አለመዳን በቅድሚያ መናገር ያስቸግራል። በተጨማሪም ሥጋዊ ክርስቲያኖች በመንግሥተ ሰማያት እንደሚኖሩና ሥራቸውም እንደ እንጨት፥ ሳርና አገዳ እንደሚቃጠል ይታወቃል። ቢሆንም እነዚህ ክርስቲያኖች የዳኑ መሆናቸውን እናውቃለን (1ኛ ቆሮ. 3፡15)። ሕይወታቸውን ስንመለከት ግን ከእነርሱ አንዳንዶች ድነታቸውን (ደኅንነታቸውን) አጥተዋል ወደሚል ማጠቃለያ እንደርስ ይሆናል። ዋናው ጥያቄ ግን ይህ ነው። እውነተኛ አማኝ ኃጢአት በመሥራቱ፥ እምነቱን በመጣሉና በሌላ ምክንያት ድነቱን (ደኅንነቱን) ያጣል?  የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫ  በመጨረሻም፥ የዋስትና ትምህርት በእግዚአብሔር ከንውን ላይ የሚመሠረት ነው። ይህ ሳይሆን ቀርቶ አንድ ሰው ድነቱን (ደኅንነቱን) ቢያጣ፥ አንዳንድ የእግዚአብሔር ሥራዎች ሊቀለበሱ ነው ማለት ይሆናል። ለምሳሌ፡-  1. በዳንን ጊዜ መንፈስ ቅዱስ የክርስቶስ አካል አድርጎናል (1ኛ ቆሮ. 12፡13)። አማኝ ድነቱን የሚያጣ ከሆነ ደግሞ ከዚያ አካል ይወጣል ማለት ነው! እንዲህ ያለው አሳብ በቅዱስ ቃሉ አልተመለከተም፡፡ 2. መንፈስ ቅዱስ አስከ ቤዛ ቀን ድረስ አማኙን አትሞታል (ኤፌ. 1፡13፥ 4፡30)። ድነት (ደኅንነት) የሚታጣ ከሆነ፥ ይህ ማኅተም ከቤዛ ቀን በፊት ይሰበራል ማለት ይሆናል።  3. ደግሞም በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ እኛን መጠበቅ የአብ ዓላማና ተግባር ነው (ዮሐ. 10፡28-30፥ 13፡1)። በመጨረሻ ያለ ነውርና ነቀፋ በፊቱ የሚያቀርበንም እርሱ ነው(ይሁዳ 24)።  4. አጥጋቢ የሆነው የዋስትና ማሳመኛ ቃል ያለጥርጥር በሮሜ 8፡29-39 ላይ ተጽፏል። የመረጃዎቹን ጥንካሬ ያስተውሉ። በመጀመሪያ የተወሰኑት ተጠሩ፥ ጸደቁ፥ ከበሩ። የኀላፊ ጊዜ የሆነውን ግስ ለወደፊት ድርጊቶች ልንጠቀምበት እንችላለን፤ ምክንያቱም አንድም የዳነ ሰው እንደማይጠፋ እርግጠኞች ነንና። አስቀድሞ ከማወቅ እስከ መወሰን ድረስ ያለው ሰንሰለት፥ ማለትም መጠራትና መጽደቅ እስከሚከብሩ ድረስ እንደጻኑ ይቆያሉ። ሁለተኛው፥ የእግዚአብሔርን ምርጦች በመክሰስ ድነታቸውን የሚያሳጣ አንዳችም ኃይል አይኖርም፤ ክስ ሁሉ የሚቀርብለት ፈራጅም ሆነ አጽዳቂ እግዚአብሔር ነውና (ቁ. 33)። ዳኛው ጻድቃን ናቸው ብሎ የበየነላቸውን አማኞች፥ የመርታት ዕድል የሚኖረው ምን ዓይነት ከሳሽ ነው? ሦስተኛ፥ ጌታ ስለ እኛ ያለማቋረጥ እየማለደ ነው። ይህ ራሱ ለደኅንነታችን በቂ ዋስትና ነው (ቁጥር 34ን ከ1ኛ ዮሐንስ 2፡1 ጋር ያነጻጽሩ)። አራተኛ፥ ምዕራፉ እርግጠኛና ጽኑ በሆነ ቃል ኪዳን የተደመደመ ሲሆን፥ ምንም ዓይነት ሁኔታ (እኛንም ሆነ ማንኛውንም ሌላ ፍጡር፥ ቁ. 39) በጌታችን በክርስቶስ ካለው ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን አይችልም። ይህ ማንኛውንም ቀዳዳ የሚደፍን ማረጋገጫ ይሆናል።  እርግጥ አንዳንድ ሰዎች ድነታችንን እናጣለን ብለው ሳይሰጉ፥ የዘላለም ዋስትናን ትምህርት እንደ ፈቃድ ወረቀት እየተጠቀሙ በኃጢአት ሲኖሩ ይታያሉ። ይህ ተገቢ አይደለም፤ እግዚአብሔርን በጣም የምናመሰግንና ቅዱስ ኑሮን ለመኖር የምንጥር መሆን አለብን (ሮሜ 6፡1-14)። ይህም እንደ ማንኛውም እውነት ሁሉ ይጣመምና ይዋሽበት ይሆናል። “ዋሥትና የለም” የሚለው ትምህርትም ቢሆን በኃጢአት የመኖሪያ ፈቃድ ሊሆን ይችላል።  አንዳንድ አስቸጋሪ ጥቅሶች  “ዋስትና የለም” ብለው የሚያስተምሩት ብዙዎቹ ጥቅሶች የተጻፉት፥ በቤተ ክርስቲያን ተግባራዊ ችግር መኖሩን በማስመልከት ነበር። በአዲስ ኪዳን ጊዜም ከቤተ ክርስቲያን አባላት መካከል በእውነት የዳነው ማን መሆኑን ማወቁ ከባድ ነበር። ስለዚህ ቃሉን የሚጽፈው ሐዋርያ አንዳንዶችን የእምነታቸው ማረጋገጫ የሚሆን ፍሬ በተጨባጭ እንዲያሳዩ ሲጠይቅ፥ አንዳንዶችንም የድነት እምነት ያላቸው ስለመሆኑ እርግጠኞች እንዲሆኑ መከሯቸዋል።  ለምሳሌ ዕብ. 6፡4-6 በተለያየ መንገድ ቢተረጎምም፥ አእምሯቸው ላልበሰለና የጸና ሕይወት ለሌላቸው አማኞች ማስጠንቀቂያ ነው። ስለዚህ ጸሐፊው እንደግ ይላል (ቁ. 1)። ምከንያቱም በከርስትና ሕይወት እንደገና “ሀ” ብሎ መጀመር የሚባል ነገር ስለሌለ፥ አማራጩ ባሉበት መቆም፥ ወይም ወደፊት መራመድ ይሆናል። ይህ ጥቅስ አንድ ሰው ድነቱን ሊያጣ እንደሚችል የሚያስተምር ከሆነ፥ እንግዲያው በድጋሚ ለመዳን እንደማይቻልም በግልጥ ያብራራል። በዚህ ምክንያት የአማኙ የዘላለም ዋስትና ልክ አለመሆኑን ለማስረዳት ይህን ጥቅስ ለመጠቀም መሞከር፥ ልክ አለመሆኑን ለማረጋገጥ ካለማስቻሉም በላይ ሌሎች ሊደረስባቸው የማይችሉና አስቸጋሪ የሆኑ ችግሮችን ይፈጥራል።።  በጸሐፊው ግምት በዮሐንስ 15፡6 የተገለጠው ዋጋ የሌለው ሥራ ሁሉ ክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት እንደሚቃጠል ነው (1ኛ ቆሮንቶስ 3፡15 መሠረት)። ያም ቢሆን ድነት የተረጋገጠ ነው። በአንጻሩ ብዙ ሰዎች እነዚህ ሁለት ጥቅሶች፥ ለአፋዊ አማኞችና በእውነት ዳግም ላልተወለዱ ሰዎች የተነገሩ ናቸው ይላሉ።  ያዕቆብ 2፡14-26 የማይሠራ እምነት መጀመሪያውኑ የሚያድን እምነት አይደለም ይላል። በሌላ አነጋገር “እምነት ብቻ ነው የሚያድነው፤ ነገር ግን የሚያድነው እምነት ብቻውን ሆኖ አያውቅም”፡፡ ምንጭ፡- “የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ ትምህርት ጥናት”፣ በዶክተር ቻርልስ ሲ. ራይሪ ተጽፎ፣ በሲሳይ ደሳለኝ የተተረጎመ እና በየላፕስሊ/ብሩክስ ፋውንዴሽን የታተመ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የአማኙ ዋስትና Read More »

በክርስቶስ ሞት የተገኙ አንዳንድ ጥቅሞች

ከአያሌ የድነት (ደኅንነት) በረከቶች ውስጥ ብዙዎቹ፣ ለምሳሌ ጸሎትን የመሳሰሉት በአማኞች ልምምድ ስለሚታዩ ግልጥ ናቸው። ነገር ግን ልንለማመዳቸው የማይቻለን ሌሎች በረከቶችም አሉ፥ ለምሳሌ ጽድቅ (ውጤታቸውን ግን እናውቀዋለን)። እዚህ የማንለማመዳቸው በረከቶች ቢሆኑም፥ ለትክክለኛው የክርስትና ሕይወት ልምምድ መሠረቶች ናቸው።  የክርስቶስ ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ ለሚኖረን ተቀባይነት መሠረት ነው የክርስቶስ ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት የሚያስገኝልን መሆኑ በብዙ የክርስትና ትምህርቶች ተገልጧል። በመዋጀት (ሮሜ 3፡24)፥ በእርቅ (2ኛ ቆሮ. 5፡19-21)፥ በይቅርታ (ሮሜ 3፡25)፣ ከኃጢአት አርነት በመውጣት (ቁላ. 1፡13)፣ በውድ ልጁ ተቀባይነት (ኤፌ. 1፡6)፣ በወደፊቱ ክብር እርግጠኞት(ሮሜ 8፡30)፥ እና ሰጽድቅ (ሮሜ 3፡24)፡፡ ጽድቅ የሚለው ቃል ሌላ ማብራሪያ ይሻ ይሆናል። ማጽደቅ እንድን ሰው ጻድቅ ነው ብሎ ማወጅ ነው። በፍርድ ቤት ቋንቋ ወስደን ስንመለከተው፥ አንድን ተከሳሽ ጥፋተኛ አይደለም ብሎ ከማንኛውም ቅጣት ወይም ፍርድ ነጻ ማድረግን ያመለክታል። እርግጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጽድቅ የፍርድ ተቃራኒ ስለመሆኑ ተገልጧል (ዘዳግ. 25፡1፤ ሮሜ 5፡16፥ 8፡33-34)። መጽደቅ በጽድቅ መንገድ ነው የሚከናወነው፤ ማለትም ከእግዚአብሔር ሕግ የሚፈለግበትን ሁሉ አሟልቷል። ጽድቅ የተገኘው እግዚአብሔር ኃጢአትን አይቶ እንዳላየ ስለሆነ፥ ወይም ፍርድን ስላቆየ ወይም ጽድቁን ስለለወጠ ሳይሆን፥ ሕግጋቱ ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ ስለተሟሉ ብቻ ነው። የክርስቶስ ለሕግጋቱ ፍጹም ታዛዥ መሆንና ቅጣቱን የከፈለው ቤዛዊ ሞቱ ለጽድቃችን መሠረት ናቸው (ሮ 5፡9)። እግዚአብሔር ሰው ጨርሶ የማይቻለውን ፍጹም ታዛዥነት ስለሚጠይቅ፥ ጽድቅ በእኛ መልካም ሥራ ላይ እይመሠረትም።  የጽድቅ ማግኛው መንገድ እምነት ነው (ሮሜ 3፡22፥ 25፥ 28፥ 30)። ይሁን እንጂ እምነት የጽድቅ መሠረት አይደለም። እምነት በእግዚአብሔር ጸጋ አማካይነት ኃጢአተኛ የነበረው አማኝ ዕዳ በክርስቶስ ጽድቅ የተከፈለበት መንገድ ነው። በምናምንበት ጊዜ እግዚአብሔር በክርስቶስ ያለውን ሁሉ ለእኛ ይቆጥርልናል፤ ከፍርድም ነጻ አድርጎ ጽድቃችንን በትክክለኛው መንገድ ያውጃል። መጽሐፍ ቅዱስ የጸደቅነው በማመናችን ነው አይልም፤ ይህ ከሆነ እንግዲያው ጽድቅ በሥራ ሊሆን ነው። እምነት የክርስቶስን ጽድቅ የምንቀበልበት መንገድ ነው። በዚህ አኳኋን በክርስቶስ ውስጥ ስለሆን ነው አማኙ የሚጸድቀው። በክርስቶስ ውስጥ ሲሆን፥ እግዚአብሔር ጽድቁን ያረጋግጥለታል፤ ይህ ነው ጽድቃችን ማለት።  በክርስቶስ ማመን አዲስ ስፍራ ያሰጣል  የሰማይ ዜግነትን (ፊልጵ. 3፡20)፣ በንጉሣዊው ክህነትና (1ኛ ጴጥ. 2፡5፥ 9)፥ በእግዚአብሔር ቤተሰብ አባልነትን (ኤፌ. 2፡19)፥ መንፈሳዊ ልደትን (ዮሐ. 3፡5)፥ በበጉ ሰርግ መታደምን (ራእይ 19፡7) እና ልጅነትን (ገላ. 4፡5) ይጨምራል።  እነዚህ በእግዚአብሔርና እርሱን በሚያምኑት መካከል የተመሠረተውን አዲስ የቅርብ ግንኙነት ለማሳየት የቀረቡ ምሳሌዎች ናቸው።  በ“አዲስ ልደት” እና “በማደጎ ልጅነት” መካከል ልዩነት እንዳለ ማስተዋል ያስፈልጋል። ሐዋርያው ዮሐንስ በእግዚአብሔር ቤተሰብ ውስጥ የእግዚአብሔር ልጅ (በግሪክ “ፓይዲዮን” ወይም “ቴክኖን”0 ስለመሆናችን ብዙ ይናገራል። ይህ ግንኙነት የሚመሠረተው “እንደገና በመወለድ” ነው (ዮሐንስ ምዕራፍ 1 እና 2)። የሚያመለክተውም ልደቱንና የበሰለ ሰው እስከሚሆን ድረስ ያለውን እድገት ይሆናል።  ሆኖም ሐዋርያው ጳውሎስ የእግዚአብሔር ልጅ ለመሆን (በግሪክ “ሁዮስ”) ወደ እግዚአብሔር ቤተሰብነት በማደጎ መስጠት” የሚል ሌላ ምሳሌ ይጠቅሳል። ይህም ቤተሰብነት፥ አንድ ሰው የራሱ ያልሆነን ሕጻን እንደ እውነተኛ ልጆቹ ባለመብትና ወራሽ ሲያደርገው የሚታይ ዓይነት አዲስ ግንኙነት ነው (የማደጎ ልጅ የሚባለው ዓይነት)። በዚህ አኳኋን የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሁሉ፥ በልደቱ በእድገቱ፥ በብስለቱ ሁሉ ለልጅ የሚሰጠውን ማንኛውንም ጥቅሞችና መብቶች ከእግዚአብሔር ቤተሰብ ጋር ይካፈላል። ይህ ዓይነቱ ልጅነት ክርስቶስን ለሚቀበሉ ሁሉ የሚሰጥ አዲስ ሥልጣን ነው።  የልጅነት መብት ውጤቶች፥ ከባርነት፥ ከሞግዚቶች፥ ከሥጋ ኃጢአት ነጻ መውጣት (ገላ. 4፡1-5፤ ሮሜ 8፡14-17) ሲሆን፥ ከዚህ መብት እንድንካፈልና እንድንረካበት የሚያደርገን ደግሞ መንፈስ ቅዱስ ነው።  የክርስቶስ ሞት ለአማኙ ውርስ ያስገኛል  ይህም በክርስቶስ ሙሉ መሆንን (ቁላ. 2፡9-10)። መንፈሳዊ በረከትን ሁሉ ማግኘትን (ኤፌ. 1፡3)፥ ስለ መንግሥተ ሰማይ ውርስ እርግጠኛ መሆን (1ኛ ጴጥ. 1፡4) ያጠቃልላል።  ለክርስትና ሕይወት አስፈላጊ የሆነው ብርታትና ኃይል በክርስቶስ ምት ተረጋግጧል  የድነት (ደኅንነት) በረከት ከጸጋ በታች መሆንን (በኃጢአት እንዳንቀጥል ሮሜ 6፡14)፥ ከሕግ ነጻ መሆንን (2ኛ ቆሮ 3፡6-13)፥ በእያንዳንዱ የሥላሴ አካላት መሞላትን (ኤፌ. 4፡6፤ ገላ. 2፡20፤ 1ኛ ቆሮ. 6፡19) ይጨምራል።  ከክርስቶስ ሞት የሚገኝ ሌላ በረከት ቅድስና ነው  “መቀደስ” የሚለው ቃል፥ “መለየት” ማለት ሲሆን፥ ቅድስና ለክርስቲያን ሦስት ትርጉም አለው። አንደኛ፥ አማኙ የእግዚአብሔር ቤተሰብ ሆኖ ተለይቷል። ይህ ስፍራዊ ቅድስና ይባላል። አማኙ ከእግዚአብሔር ቤተሰብ እንደ አንዱ ተቆጠረ ማለት ነው። መንፈሳዊ ሁኔታ ምንም ይሁን ምን መንፈሳዊ ስፍራን ይመለከታልና ይህ ለማንኛውም አማኝ እውነት ነው። 1ኛ ቆሮ. 6፡11ን በማንበብ የአማኞችን ሥጋዊ ሁኔታ ያስታውሱ። ይህ ስፍራዊ ቅድስና በክርስቶስ ሞት ላይ የተመሠረተ መሆኑን ዕብ. 10፡10 ግልጥ ያደርገዋል።  ተግባራዊ (ልምምዳዊ) ቅድስና ደግሞ ሌላው ጉዳይ ነው። አማኞች የተለየን ስለሆንን፥ የተለየ ሰው ኑሮ እንኖራለን (1ኛ ጴጥ. 1፡16ን። በቅድስና የሚገኝ ስፍራን በተመለከተ ማንም ከማንም በላይ ቅዱስ አይደለም። አንድ አማኝ ከሌላው በቅድስና አኗኗሩ የሚበልጥ መሆኑን ግን መናገር ይቻላል። የአዲስ ኪዳን ምክሮች ሁሉ በመንፈሳዊ እድግት ሊታይ ስለሚገባው ተግባራዊ ቅድስና የተጻፉ ናቸው።  በተጨማሪም ስፍራችንና ተግባራችን አንድ እስካልሆነ ድረስ ለእግዚአብሔር በፍጹም ቅድስና ተለይተናል ለማለት አንችልም። ይህ እውነት የሚሆነው ከርስቶስን ስናየውና እንደ እርሱ ስንሆን ብቻ ነው (1ኛ ዮሐ. 3፡1-3)። ስለዚህ አንዱ የቅድስና መልክ የወደፊት ቅድስና የሚባል ሲሆን፥ ይህም የትንሣኤ አካል በመልበስ ከሌሎች ቅዱሳን ጋር በሙሉ ክብር የምንገኝበት ጊዜ ነው (ኤፌ. 5፡26-273 ይሁዳ 24-25)።  ምንጭ፡- “የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ ትምህርት ጥናት”፣ በዶክተር ቻርልስ ሲ. ራይሪ ተጽፎ፣ በሲሳይ ደሳለኝ የተተረጎመ እና በየላፕስሊ/ብሩክስ ፋውንዴሽን የታተመ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

በክርስቶስ ሞት የተገኙ አንዳንድ ጥቅሞች Read More »

የክርስቶስ ሞት

ውጤቶቹ  ለኃጢአት ምትክ ነበር። የክርስቶስ ሞት ትርጉም ብዙ ገጽታዎች ቢኖሩትም፥ ዋናውና ያለ እርሱ ሌሎቹ ትርጉም የለሽ የሚሆንበት ፅንሰ አሳብ ግን ለኃጢአት ምትክ መሆኑ ነው። ይህም በቀላሉ ክርስቶስ በኃጢአተኛች ፋንታ መሞቱን ያመለክታል። “አንታይ” የሚለውን ግሪክኛ መስተዋድድ “ምትክ” (“ፋንታ”) የሚለው ቃል ይወከለዋል። ይህ ቃል፥ ለምሳሌ ከክርስቶስ ሞት ጋር ባልተያያዘ ክፍል ጥቅም ላይ ውሏል (ሉቃስ 11፡11)። ጌታችን ስለ ራሱ ሞት ትርጉም በገለጠባቸው ክፍሎች ግን ይበልጥ ጉልህ ሆኖ ይታያል (ማቴ. 20፡28፤ ማር. 18፡45)። ሞቱ ለብዙዎች ቤዛነት እንደሆነ ተናግሯል።  “ሁፐር [huper] የሚል ሌላ መስተዋድድ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ጥቅም ላይ ውሏል። ቃሉ ሁለት ትርጉሞች አሉት። አንዳንዴ “ለሌሎች ጥቅም ሲል” የሚል ትርጉም ሲኖረው፥ አንዳንዴ ግን “ምትክ” የሚል ትርጉም አለው። ክርስቶስ የሞተው በእኛ ፋንታና ለእኛ ጥቅም ሲል ስለሆነ፥ “ሁፖር” የሚለው ቃል እነዚህን የከርስቶስን ሞት የሚገልጡ ሁለት አሳቦች የማይዝበት ምክንያት አይኖርም። ለምሳሌ 2ኛ ቆሮ. 5፡21 እና 1ኛ ጴጥ. 3፡18ን ይመልከቱ። “ምትክ” ለሚለው ቃል ትርጉም ጥሩ ምሳሌ የሚሆን በፊሊሞና 13 ውስጥ ይገኛል።  አሳቡ ግልጥ ነው። ጳውሎስ ሮም ሁኖ በፊት ከጌታው የሸሸውንና ኋላም አዲስ አማኝ የሆነውን ባሪያ፥ አናሲሞስን በቈላስይል ወደሚኖረው ጌታው ወደ ፊሊሞና ሲመልሰው ያሳያል። “አሁን” ይላል ጳውሎስ ለፊሊሞና “አናሲሞስን በሮም ከእኔ ጋር በወንጌል እሥራት ያገለግለኝ ዘንድ ባንተ ምትክ (ሁፐር) ባስቀረው እወድ ነበር።” የዚህ ቃል ትርጉም ስለ ፊሊሞና ጥቅም ሲባል ማለት አይሆንም፥ ምከንያቱም ፊሊሞና ሳይሆን ጳውሎስ ነበር በአናሲሞስ ሮም መቆየትና በፊልሞና ፋንታ ቢያገለግለው የሚጠቀመው። ቃሉ ከአዲስ ኪዳን ውጭም የምትክነትን አሳብ መያዙ ሌላው ምሳሌ ነው።  የክርስቶስ ሞት ከኃጢአት መዋጀትን አስገኝቷል። የመዋጀት ትምህርት በሦስት የአዲስ ኪዳን ቃላት ላይ የተመሠረተ ነው። የመጀመሪያው ቀላል ትርጉም “መግዛት ወይም የአንድን ነገር ዋጋ መክፈል ነው”። ይህ በየቀኑ ጥቅም ላይ የሚውል ቃል ነው። መሬት ውስጥ ስለተሸሽገው መዝገብ (ሀብት) በተነገረው ምሳሌ ሰውየው መሬቱን እንዲገዛ (እንዲዋጅ የገፋፋውን ምክንያት በማጤን ስለ ቃሉ ይበልጥ ለመረዳት ይቻላል (ማቴ. 13፡44)። ከድነታችን (ከደኅንነታችን) ጋር በተያያዘ ሁኔታ ደግሞ ቃሉ የሚያመለክተው ስለ ኃጢአታችን የሚጠየቀው ዋጋ ተከፍሎ መቤዠታችንን ነው። የመዋጀት ክልል ያልዳኑትን የሐሰት አስተማሪዎች እንኳን እንደሚጨምር በ2ኛ ጴጥሮስ 2፡1 ላይ ተገልጿል። ለዚህም የሚያበቃቸው የክርስቶስ ቤዛነት ነው። በራእይ 5:9 ላይ መዋጃው የክርስቶስ ደም መሆኑን፥ የመዋጀት ውጤቱ ደግሞ በሥጋችን እግዚአብሔርን ማክበር መሆኑን በ1ኛ ቆሮንቶስ 6፡19-20 የተጠቀሰውን ያንብቡ።  ሁለተኛውም ቃል የሚገልጠው ከላይ የተጠቀሰውን መሠረታዊ ቃል ሆኖ፥ ትርጉሙን በጣም ለማጠናከር መስተዋድድ ተጨምሮበታል። ይህ በቀላሉ ወደ አማርኛ ሲመለስ የመስተዋድዱ ትርጉም “ከ…ውስጥ” የሚል ይሆናል። ሁለተኛው ትርጉም “ከገበያ ውስጥ መግዛት” ማለት ነው። ይህ አሳብ የከርስቶስ ሞት የኃጢአትን ዋጋ መክፈሉን ብቻ ሳይሆን፥ ወደ ኃጢአት እሥራትና ቅጣት ላለመመለስ ሙሉ እርግጠኞች እንሆን ዘንድ ከኃጢአት ገበያ ያወጣን መሆኑንም ያመለክታል። የክርስቶስ ሞት ዓላማ፡- “እንደ ልጆች እንሆን ዘንድ ከሕግም በታች ያሉትን ይዋጅ ዘንድ” (ገላ. 4፡5) ነበር። በዚህ ጥቅስ የተገለጠው ድርብ ትርጉም የሚያስረዳው የልጅነት ጸጋችንን እንደማናጣ፥ ወደ ባርነትም እንደማንመለስ ዋስትና የተሰጠን መሆኑን ነው።  ስለ መዋጀት የተጠቀሰው ሦስተኛው ቃል በጣም የተለየ ነው። መሠረታዊ ትርጉሙ መፍታት ማለት ሲሆን፥ ይህም የተገዛ ሰው ወይም ባሪያ ነጻ መሆኑን ወይም ሙሉ ነጻነት ማግኘቱን ያመለክታል። ይህ ነጻነት በክርስቶስ ምትክነት የተገኘ ነው (1ኛ ጢሞ. 2፡6)፤ መሠረቱ የክርስቶስ ደም ሲሆን (ዕብ. 9፡12)፥ የመጨረሻ ውጤቱም መልካም ሥራ ለማድረግ ከፍተኛ ፍላጎት ያለውን ሕዝብ ማንጻት ነው (ቲቶ 2፡14)። ስለዚህ የመዋጀት ትምህርት ማለት፥ አንድ አማኝ በክርስቶስ ደም ተገዝቷል፥ ከእሥራት ተላቋል፥ ነጻ ሆኗል የሚለውን የምስራች የሚያበስር ፅንሰ አሳብ ማለት ነው።  የከርስቶስ ደም ያስታርቃል። ማስታረቅ ማለት መለወጥ ማለት ነው። በክርስቶስ ሞት እርቅ ማግኘት ማለት ከእግዚአብሔር ተለይቶ የነበረው ሰው ድነትን (ደኅንነት) ያገኝ ዘንድ ተለወጠ ማለት ነው (2ኛ ቆሮ. 5፡19)። አንድ ሰው ሲያምን ከእግዚአብሔር ተለይቶ ከመኖር ወደ እግዚአብሔር ቤተሰብ አባልነት ይለወጣል (2ኛ ቆሮ. 5፡19)። እግዚአብሔር በደልን ሽሮ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ፍቅሩን ለመስጠት የሚችል በመሆኑ የማስታረቁ ሥራ ዓላምን ሁሉ ይመለከታል እንላለን። እኛ አማኞችም ይህን ስጦታ በግል ስንቀበል እንድናለን (ሮሜ 5፡1)። የእርቅ መሠረቱ የክርስቶስ ሞት ነው (ሮሜ 5፡10)። በዚህ እርቅ የሚለወጠው ሰው እንጂ እግዚአብሔር እንዳልሆነ ማስተዋል ጠቃሚ ይሆናል። ምክንያቱም እግዚአብሔር የሚለውጥ ከሆነ ባሕሪው ወይም ቅድስናው ጥያቄ ውስጥ ይገባል። መለወጥ የሚያስፈልገው ሰው እንጂ እግዚአብሔር አይደለም። በእርቅ ጊዜ የሚከናወነውም ይህ ነው።  ማስተስሪያን ይሰጣል [Popitiation/ፕሮፒቪኤሽን]፡፡ ማስተስረይ ማለት አምላከን ማርካት ወይም ቁጣውን ማብረድ ማለት ነው። ይህ አባባል ለምንድነው የአምላክን ቁጣ ማብረድ የሚያስፈልገው? የሚል ጥያቄ በእእምሮአችን ይፈጥራል። ለዚህ ጥያቄ የመጽሐፍ ቅዱስ መልስ እውነተኛው አምላክ በሰው ልጅ ኃጢአት ምክንያት ተቆጥቶ ስለነበር ነው ይላል። የክርስቶስን ትምህርት ጨምሮ የእግዚአብሔርን ቁጣ በተመለከተ የተጻፉ ብዙ ከፍሎች መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሉ (ማር. 3፡29፤ 14፡21)። ቁጣው የምከንያትና ውጤት ቀላል አሠራር ሳይሆን፥ በሰው ጉዳይ የእግዚአብሔርን ጣልቃ ገብነት ያሳያል (ሮማ 1፡18፤ ኤፌ. 5፡6)።  የክርስቶስ ሞት እግዚአብሔርን አርክቶታል፤ ቁጣውን በመመለስም በአረካው ልጁ የሚያምኑትን ሁሉ እንደ ቤተሰቡ ሊቀበላቸው ፈቅዷል። የክርስቶስ እግዚአብሔርን የማርካት ተግባር ስለ ዓለም ሁሉ የሚሆን ነው (1ኛ ዮሐ. 2፡2)፣ የፈሰሰ ደሙ ነው የዚህ ሁሉ መሠረት (ሮሜ 3፡25)።  በከርስቶስ ሞት እግዚአብሔር ረክቷል። ይህን በተመለከተ ከሰው የምንጠይቀው ነገር ሊኖር አይገባም። የረካን ለማርካት መሞከር የማያስፈልግ ድካም ይሆናል። ይህ ቢሆንማ ሰው ክርስቶስ ከመሰቀሉ በፊት እግዚአብሔር መርካት አለመርካቱን ለማወቅ እርግጠኛ መሆን ባልቻለም ነበር። ለዚህ ነው ቀራጩ ሰውዩ ቃል በቃል ሲጸልይ “እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ” (ሉቃስ 18፡13)፣ ወይም በግሪክ ቋንቋ እንደሚለው “በእኔ እርካ” ያለው። ዛሬ ይህ ዓይነቱ ጸሎት አስፈላጊ አይደለም። እግዚአብሔር በክርስቶስ ሞት ረክቷል። ስለዚህ ለሰዎች የምናስተላልፈው መልእክት፥ እግዚአብሔርን ምንም በማድረግ ሊያስደስቱት እንደማይችሉ፥ ነገር ግን የእርሱን ቁጣ የመለሰው የክርስቶስ መሥዋዕትነት በቂ መሆኑን እንዲያምኑ ነው።  የክርስቶስ ሞት በኃጢአት ባሕርይ ላይ ፈርዷል (ሮሜ 6፡1-10)። የክርስቶስ ሞት የኃጢአት ባሕርይ ኃይል በሥጋችን እንዳይነግሥ በማድረግ ረገድ ታላቅ ጥቅም አለው። ይህ ለመረዳት የሚከብድ አሳብ ቢሆንም፥ ጳውሎስ እንዳለው፥ ከክርስቶስ ጋር በጥምቀት አንድ የሆነው ሞቱን በመካፈል ለኃጢአት መምታችንን ለማሳየት ነው። ጥምቀቱ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት መሆን አለበት። ምክንያቱም ምንም ዓይነት የውኃ ብዛት በዚህ ክፍል የተጠቀሰውን ሥራ ሊያከናውነው አይችልም፡፡ ተደጋግሞ እንደተገለጠው፥ የሥጋ ሞት ለሚያምነውም ሆነ ለማያምነው መጥፋትን ወይም አለመኖርን ሳይሆን የመንፈስን ከሥጋ መለየት ነው የሚያመለክተው። መንፈሳዊ ሞትም ከእግዚአብሔር መለየትን እንጂ፥ እንቅስቃሴ ማቆምን ወይም ሥጋዊ ሞትን አይገልጥም። ያልዳኑ ሰዎች በሥጋ ሕያው ቢሆኑም በመንፈስ ከእግዚአብሔር የተለዩ ናቸው። ዘላለማዊ ሞት እንኳን መጥፋት ማለት እይደለም፤ ከእግዚአብሔር ተለይቶ ለዘላለም በእሳት ባሕር መኖር ማለት ነው።  ክርስቲያን ከክርስቶስ ጋር ተሰቅሏል ማለት በሕይወቱ ነግሦ ከነበረው ኃጢአት ተለይቷል ማለት ነው። በቁጥር 1 ላይ “በኃጢአት እንኑርን?” ለሚለው ጥያቄ መልሱ ከክርስቶስ ጋር ሞተናልና አይሆንም ነው። ይህ ከክርስቶስ ጋር መሞት የኃጢአት አገልጋይ የሆነውን ሥጋ “እጥፍቶታል”። “ማጥፋት” የሚለው ቃል ግን ፍጹም ማጥፋት ማለት አይደለም። ይህ ቢሆን ኖሮ የኃጢአት ባሕሪያችን ሙሉ በሙሉ በተወገደ ነበር። ይህ እንደማይቻል ከሰዎች ጋር የምናደርገው የዕለት ከዕለት ግንኙነት ያረጋግጥልናል፡፡ ማጥፋት ማለት የኃጢአት ባሕርይ ውጤታማ እንዳይሆን ማድረግ ነው። እኛ ግን ከክርስቶስ ጋር ተሰቅለናል ስንል ከክርስቶስ ጋር በአዲስ ሕይወት ተነስተናል ማለታችን ነው (ሮሜ 6፡4)። ይህ የሚያሳየው ከአሮጌው ሥጋ መለየታችንን ብቻ ሳይሆን፥ ከክርስቶስ ትንሣኤ ጋር አዲስ ኅብረት እንዳለን ነው። ከቁጥር 4 እስከ 10 ባሉት ክፍሎች የተብራራውም ይህ ነው። ስለዚህ ከክርስቶስ ጋር አንድ መሆን የሚለው ቃል የሚያብራራልን የአርጌውን ኃይል ከእኛ መወገድ ብቻ ሳይሆን ከክርስቶስ ጋር አንድ መሆናችንንና በዚህም አዲስ ኃይል የምንኖር መሆናችንን ነው።  ይህ የሆነው

የክርስቶስ ሞት Read More »

ምርጫ ምንን ያካትታል?

የድነት (የደኅንነት) ትምህርት ቀላልም ውስብስብም ነው። ብዙ ሰዎች በአንድ በኩል ቢያንስ ዮሐ. 3፡16ን ወይም ጳውሎስ የፊልጵስዩስ እሥረኞች ጠባቂ ስለመዳን ላቀረበለት ጥያቄ የሰጠውን መልስ ሊጠቅሱ ይችላሉ (ሐዋ. 16፡31)። በሌላ በኩል ግን ሰው የሆነው ቅዱስ አምላከ እንደ ኃጢአተኛ እንደተቆጠረና እንደሞተ ማን ሊያብራራ ይችላል? እጅግ ጥልቅ የሆነውን የምርጫ ጉዳይ ማን ይመረምራል? (ይህ የድነት ትምህርት አንዱ ክፍል ነው) ድነት በትክክል ልንረዳው የሚገባ፥ እጅግ ወሳኝ የእምነት ትምህርት ነው። ምክንያቱም ማንኛውም ፍጡር (መላእክትም ሆኑ ወይም ሰባኪ) ከእውነተኛው ወንጌል የተለየ ትምህርት ቢሰብክ መርገም በራሱ ይሸከማል። ስለዚህ የድነትን (ደኅንነትን) ወንጌል በትክክል መረዳትና ያለማዛነፍ ለመግለጥ መቻል በጣም አስፈላጊ ነው። የዚህን ጠቀሜታ ይበልጥ የምንረዳው፣ አንዳንድ በራሪ ጽሑፎችን በምናነብበት ጊዜ፥ ወይም በራድዮ የሚተላለፉትን መንፈሳዊ መልእክተች በምንሰማበት ወቅት ግልጥ ያልሆነና ግራ የሚያጋባ የወንጌል ትምህርት ደጋግሞ ሲያጋጥመን ነው።  የድነት ትምህርት ከዚህ በፊት ካጠናነው የክርስቶስ ትምህርት ተለይቶ የማይታይና በእጅጉ የተያያዘ ነው። የግንኙነቱ ምክንያትም ግልጥ ነው! የድነት ታላቅነት በአዳኙ ታላቅነት ላይ ይመሠረታልና። እርሱ እንደ ሰዎች ኃጢአተኛ ቢሆን ኖሮ፥ ሞቱ ከራሱ ኃጢአት በስተቀር የማንንም ዕዳ ሊከፍል ባልቻለም ነበር። በብሉይ ኪዳን የፋሲካ በግ ከመታረዱ በፊት ያለ ነውር መሆን እንዳለበት ሁሉ፥ የጌታችን ሕይወትም ፍጹምና ለኃጢአታችን ምሥዋዕትነት ብቁ መሆኑ ተረጋገጠ (ዘዳግ. 12:5-6)። ይህን ጉዳይ ምዕራፍ 4 ላይ በሚገባ የተመለከትነው ስለሆነ እዚህ አንደግመውም። ቀጥለን የምንመለከተው የመዋጀትን ሥራና ገጽታዎቹን ይሆናል።  የምርጫን ትምህርት መረዳቱ ለማንም ቢሆን አስቸጋሪ መሆኑ አያከራክርም። ቢሆንም ትምህርቱ መጽሐፍ ቅዱሳዊና ከድነት ጋር የተያያዘ ስለሆነ ወደ ጐን ብለን የምናልፈው ጉዳይ አይሆንም።  ፅንሰ አሳቡ  ምርጫ ለድነት በዋናነት የሚታይ ባይሆንም በዙሪያችን ያለ ጉዳይ ነው። የተወለድነው ከተለያየ ቤተሰብ እንደመሆኑ የአእምሮ ችሎታችንም እኩል አይደለም፤ በዘር እንለያያለን፥ የተለያዩ የሕይወት ገጠመኞች ይኖሩናል ወዘተ። እነዚህ ሁሉ የአጋጣሚ ጉዳዮች ናቸው ብለን እንደ ዋዛ እንለፋቸው እንጂ፥ የመታደል ወይም የፍርጃ፥ አለበለዚያም የአካባቢ ተጽዕኖ ጣልቃ ገብነት እንዳለባቸው አድርገን የምንወስዳቸው ናቸው።  የመጽሐፍ ቅዱስ የምርጫ ትምህርት ይህንኑ ያለመመሳሰል መመሪያ ይይዛል። ይህን ጉዳይ እግዚአብሔር የተለያዩ ሰዎችን ለተለያየ ዓላማ መምረጡን ያመለክታል ብሎ መተርጎም ይቻላል። ትርጉሙ ሰፋ ያለበት ምክንያት በመጽሐፍ ቅዱስ የተለያዩ ሰዎች፥ ወይም ቡድኖች፥ መመረጣቸውን ለማካተት ነው። ለምሳሌ፡- 1. እስራኤል በመንግሥትነት ተመርጣ ነበር (ዘዳግ. 4፡37፤ 1ኛ ዜና 16፡13)። ይህ ዳግም የተወለዱትንና ያልተመለዱትን የሚያጠቃልል ነበር፤ 2. ንጉሥ ቂሮስ ምንም እንኳን እኛ እስከምናውቀው ያልዳነ ቢሆንም፥ በእግዚአብሐር የተመረጠ ተብሎ ተጠርቷል (ኢሳ. 45፡1-4)፤ 3. ክርስቶስ በእግዚአብሔር የተመረጠ ተብሏል (ኢሳ. 42፡1)፤ 4. በፍዳ ዘመን ከቤተ ክርስቲያን የተለዩና የተመረጡ ሕዝቦች ይኖራሉ (ማቴ. 24፡ 22፥ 24፥31)፤ 3. በኢየሱስ ያመኑትን እግዚአብሔር ዛሬ በመምረጥ ላይ ነው (ቈላ. 3፡ 12፤ ቲቶ 1፡1)። በዚህ በመጨረሻው ነጥብ መሠረት ምርጫ የክርስቶስ አካል ለመሆን የሚድኑትን ለመምረጥ እግዚአብሔር የሚፈጽመው ተግባር ነው።  የምርጫ ፅንሰ አሳብ በእግዚአብሔር ባሕርይ (አሠራር) ላይ የተመሠረተ ነው። በሌላ አባባል ምርጫ ከሌሎች አሠራሮቹ ጋር የተስማ የእግዚአብሔር ተግባር ነው። ይህም ማለት፡-  1. ምርጫ ፍቅር ነው፥ ስለሆነም ፍቅር የሆነው እግዚአብሔር ከፍቅር ውጭ አንዳች ነገር አያደርግም (ኤፌ. 1፡4)።  2. የእግዚአብሔር ምርጫ በጥበብ ነው፥ ምክንያቱም እርሱ ጥበብ ነውና (ይሁዳ 25)።  3. የእግዚአብሔር የምርጫ ዓላማ ዓለም ሳይፈጠር በፊት የተወሰነ ነው (ኤፌ. 1፡ 4)፤ ወደፊትም ለዘላለም ይቀጥላል (ሮሜ 8፡30)።  4. የምርጫ ክንዋኔ፥ እግዚእብሔር የፈጠረውንና እርሱም የሚያከብረውን የተፈጥሮ ሕግ የሚጥል አይሆንም። ስለሆነም ምርጦቹ የሚድኑት፥ ድንገት መልአክ ከሰማይ ወርዶና ወንጌል ሰብኮላቸው ሳይሆን፥ እንደ ማንኛውም ሁኔታ ከሰዎች ምስክርነት በመስማትና በማመን ነው (ሮሜ 10፡ 14)። የመዝራትና የማጨድ ተፈጥሯዊ ሕጎችም ተግባራዊ ይሆናሉ። ስለዚህም ባለማመኑ የሚጸና ሰው ያለማመኑ ውጤት ለሆነው የእሳት ባሕር ይዳረጋል። በሌላ አነጋገር የሰው ልጅ ኅላፊነቱን በተግባር የመተርጎም ብቃቱ በአጠቃላዩ የምርጫ ዕቅድ ውስጥ ድርሻ አለው።  5. ምርጫ በመጨረሻ ውጤቱ የእግዚአብሔርን ታላቅነት ያከብራል (ኤፌ. 1፡12-14)። በአንዳንድ ሁኔታዎች የተነሳ ይህን ሀቅ ለመመስከር ያስቸግረን ይሆናል። ከእግዚአብሔር አጠቃላይ ዕቅዶች የምናየው በጣም ትንሹን ክፍል ብቻ በመሆኑ እርሱ በሚያደርገው ነገር ላይ ፍርድ ለመስጠት በምንም አኳኋን የማንችል መሆናችንን ማስታወስ አለብን።  መጽሐፍ ቅዱሳዊው መሠረት  በአዲስ ኪዳን ስለ ምርጫ የሚናገሩት ክፍሎች ኤፈ. 1፡3-14 ፤ ሮሜ 9፡6-24፥ 8፡28-30፤ ዮሐ. 6፡44፤ ሐዋ. 13፡48፤ 1ኛ ጴጥ. 2፡8 እና ራእይ 17፡8 ናቸው። እነዚህ ክፍሎች የኛን መብት ከእግዚአብሔር የመምረጥ መብት ጋር በማመላከት ለሚነሳው ጥያቄ መልስ የሚሰጡ ሲሆን፥ እግዚአብሔር የሚያድናቸውን ሰዎች መርጦ ሌሎችን እንደሚተው ያመለክታሉ። በእነዚህ ምንባቦች የተጠቀሱትን ብዙ ቁም ነገሮች መረዳቱ ቀላል አይደለም። ነገር ግን ማመን ብንጀምር (ሙሉ በሙሉ ባይገቡንም ምርጫን ከእግዚአብሔር አንጻር መመልከት እንጀምራለን።  አሠራሩ  በግልጥ እንደሚታየው የተመረጠ ሕዝብ አለ። በኤፈሶን 1፡4-5 እንደተገለጠው ይህ ሕዝብ ዓለም ከመፈጠሩ በፊት በፍቅር የተመረጠ ነው። እንደ 2ኛ ዮሐንስ 1፡13፤ ሮሜ 6፡131 እና ገላ. 1፡ 15-16 ያሉ ጥቅሶች ይህ ሕዝብ የተመረጡ ግለሰቦች ስብስብ መሆኑን ሲያሳይ፥ ዮሐ. 13፡18፤ ሮሜ 9፡22፤ 1ኛ ጴጥ. 2፡8 ደግሞ፣ የተወሰኑ ወገኖች ወይም ሰዎች ከዚህ ሕዝብ ጋር እንዳልተደመሩ ያሳያሉ። እግዚአብሔር ምርጫውን ለምን በዚህ አኳኋን አደረገው ለሚለው ጥያቄ መልስ የለንም። ከባሕሪው የሚቃረን ነገር እንደማያደርግ ግን እርግጠኞች ነን። ምርጫ ማን እንደሚያምን አስቀድሞ ከማወቅ የላቀ ነው፤ ምርጫ  ማን እንደሚያምን የመምረጥ ተግባር ነው።  የመምረጥን ሂደት ፍሬያማ የሚያደርግ የአሠራር መንገድ አለ። ከነዚህም የአሠራር መንገዶች ውስጥ፥ አዳኝ የሆነውን ክርስቶስን እንዲሞት መላክ፥ ሥጋ ለብሶ ከመጣ በኋላም ሊፈጸሙ የሚገባቸውን ሁኔታዎች ማመቻቸት፥ ዛሬ ደግሞ ወንጌልን በመላው ዓለም እንዲሰበክ ማድረግና ሰዎችም ይድኑ ዘንድ እምነት አስፈላጊ መሆኑ ይገኙበታል። ምርጫ የሰውን የኅላፊነት ግዴታዎች አይደመሰስም። ሰዎች እንዲያምኑ ታዘዋል (ሐዋ. 16፡31፤ 17፡30)፥ ማንም ሳያምን አይድንም (ኤፈ. 2፡8-9)። በሌላ አገላለጥ እንዲህ ማለትም እንችላለን፡- ዛሬ በሕይወት ከሚኖሩት ውስጥ ያልዳኑ፥ ግን የተመረጡ ሰዎች አሉ። እነዚህ ቢመረጡም እንኳን እስካላመኑ ድረስ አይድኑም፥ የጠፉ ናቸው። ይህ አሳብ ራሱን በራሱ የሚቃረን ቢመስልም እውነት ነው። ይህን አለማስተዋል የዚህን ትምህርተ ሃይማኖት ሁሉ አሳብ አለመረዳት ይሆናል።  የምርጫው ውጤት አለ፤ እሱም መልካም የሚያደርጉ ሰዎች ናቸው (ኤፌ. 2፡10)። እንደ “እግዚአብሔር ምርጦች” ለመታወቅ እኛም “ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትሕትናን፥ የዋህነትን፣ ትዕግሥትን” መልበስ አለብን (ቆላ. 3፡12)። የእግዚአብሔርን ሁሉን ቻይነትና ሉዓላዊነት መረዳት ወደ ኃጢአት የሚመራ ሳይሆን በአስደናቂ አኳኋን ትሁት የሚያደርግና ወደሚቀድስ ምስጋና የሚወስድ ነው (ሮሜ 11፡33-36)። ምንጭ፡- “የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ ትምህርት ጥናት”፣ በዶክተር ቻርልስ ሲ. ራይሪ ተጽፎ፣ በሲሳይ ደሳለኝ የተተረጎመ እና በየላፕስሊ/ብሩክስ ፋውንዴሽን የታተመ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

ምርጫ ምንን ያካትታል? Read More »

የሰው ኃጢአት

የኃጢአ ትርጉም  ይህ የቀረበው ጽሑፍ የኃጢአትን ሥነ-መለኮታዊ ትርጉም፣ የውርስ ባሕርይዋን፣ በክርስቲያን ሕይወት ላይ የምታመጣውን ተጽዕኖና መለኮታዊ መፍትሔዋን በግልጽ የሚያስረዳ እጅግ ጥልቅ የትምህርት ስብስብ ነው። በጽሑፉ ውስጥ የነበሩትን የፊደል ግድፈቶች፣ የተሳሳቱ የቃላት አጻጻፎችንና የሥርዓተ-ነጥብ ክፍተቶችን ሙሉ በሙሉ አስተካክያለሁ። ለማንበብና ለጥናት ይበልጥ ምቹ፣ ሥርዓታማና ማራኪ እንዲሆን በንዑስ አርዕስትና በደመቁ ነጥቦች ከፋፍዬ ያቀረብኩት የተስተካከለው ሙሉ ጽሑፍ የሚከተለው ነው፦ የኃጢአት ትርጉምና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይዘት ኃጢአት የሚለውን ቃል ለመተርጎም በየጊዜው ብዙ የተለያዩ አስተሳሰቦች ተሰጥተዋል፤ ትርጉሞቹም በግልጽ ክፍሎች ይመደባሉ፦ የኃጢአት አጠቃላይ መለኪያ፦ ቁልጭ ያለ ማብራሪያ በ1ኛ ቆሮንቶስ 10፡31 ላይ እናገኛለን። አማኞች የሚያደርጉትን ሁሉ ለእግዚአብሔር ክብር እንዲያደርጉ ታዘዋል። ስለዚህ የኃጢአት አጠቃላይ ትርጉም ከእግዚአብሔር ክብር የሚያንስ ማንኛውንም ነገር መፈጸም ማለት ነው። ይህ እርግጠኛው የኃጢአት መለኪያ ስለመሆኑ በሮሜ 3፡23 ላይ ተጽፏል። የግል ኃጢአት በብሉይ ኪዳን ኃጢአትን የሚገልጡ ስምንት መሠረታዊ ቃላት ሲኖሩ፥ በአዲስ ኪዳን ደግሞ ቢያንስ አሥራ ሁለት አሉ። እነርሱም የሚያመለክቱት፦ (ለዚህ የሚረዱ ጥቅሶች፦ ዘፍጥ. 38፡7፤ ሕዝ. 48፡11፤ 1ኛ ነገሥ. 8፡50፤ ማቴ. 5፡21፤ 1ኛ ቆሮ. 6፡9፤ ገላ. 6፡1፤ 1ኛ ጢሞ. 4፡2 ናቸው።) የግል ኃጢአት ማለት ዒላማን መሳት ማለት ብቻ አይደለም፤ እግዚአብሔር ያቀደልንን ዓላማዎችና ግቦችን አለሟሟላት ማለትም ነው። የኃጢአታዊ ተፈጥሮ ውርስና አጠቃላይ ጎዶሎነት ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች እንደሆንን ሐዋርያው ጳውሎስ ይገልጣል (ኤፌ. 2፡3)። ይህ ኃጢአታዊ ተፈጥሮ፥ ሰዎች ሁሉ በትውልድ የወረሱት፥ በእግዚአብሔር ዘንድ የማያስመሰግን መልካም፥ ክፉ ወይም ገለልተኛ ነገር የማድረግ ዝንባሌ ነው። የሰው ባሕርይ በየአቅጣጫው እንደተበላሸ የሚነግሩን ብዙ ጥቅሶች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሉ። አእምሮው (2ኛ ቆሮ. 4፡4፤ ሮሜ 1፡28)፥ ሕሊናው (1ኛ ጢሞ. 4፡2)፥ ፈቃዱ (ሮሜ 1፡28)፥ ልቦናው (ኤፌ. 4:18)፥ ሁለንተናው (ሮሜ 1፡18-3፡20) ሁሉ ተበላሽቷል። ይህ የአጠቃላይ ጎዶሎነት (Total Depravity/ቶታል ዲፕራቪቲ) ትምህርት ይባላል። አጠቃላይ ጎዶሎነት ሲባል ሁሉም ሰው በድርጊቱ ፍጹም ክፉ ሆኗል፥ ወይም ሁሉም ሰው በማንኛውም ዓይነት ኃጢአት ውስጥ ሁልጊዜ ይዘፈቃል፥ ወይም አንድ ሰው በጎ ድርጊትን ፈጽሞ አይወድም እንዲሁም አያደርግም ማለት አይደለም። ለማለት የተፈለገው፦ ኃጢአት የሰዎችን ሁለንተና (አእምሮ፣ ስሜት፣ ፈቃድ) ሙሉ በሙሉ እንደሚበክልና በዚህም የተነሳ ተፈጥሯዊ ሰው በእግዚአብሔር ፊት በራሱ ጥረት የዘላለም ዋጋ የሚያስገኝለትን ነገር እንደሚያጣ ነው። የኃጢአት ብክለትና ማስተላለፍ (Imputation) የሥነ-መለኮት ምሁራን የኃጢአትን ብክለትና ፍርድ ማስተላለፍ (Imputation/ኢምፒውቴሽን) በተመለከተ ብዙ ተከራክረዋል። ብዙዎች የአዳም ኃጢአት ከእርሱ በኋላ በተወለዱት ሁሉ ላይ ተላልፏል ሲሉ፤ ሌሎች ደግሞ አዳም የሰውን ልጅ ወክሎ ቢያጠፋም፥ የእርሱ የግል በደል ፍርድ ወደ ሌሎቹ በቀጥታ አይተላለፍም ይላሉ። ይህ ሁሉ ክርክር የሮሜ 5፡12ን ትርጉም መነሻ በማድረግ ሲሆን፥ በተለይ “ሁሉ ኃጢአትን አደረጉ” የሚሉትን ቃላት በተመለከተ ነው። የቃላቱ ትርጉም «ሰዎች ሁሉ ኃጢአተኞች ናቸው (ኃጢአታዊ ተፈጥሮ አላቸው)» ማለት ነው? ወይስ «አዳም ኃጢአት በፈጸመ ጊዜ በአንዳች ተወካያዊ ሁኔታ የሰው ዘር ሁሉ አብሮ ኃጢአት ሠራ» ማለት? ሁለተኛው አስተሳሰብ እውነት ከሆነ የኃጢአትን ፍርድ ማስተላለፍ (Imputation) ያመለክታል። ብዙዎች ይህን አሳብ ልክ አይደለም፥ ምክንያቱም «አንድ ሰው ገና ሳይወለድ ለተሠራው ኃጢአት እንዴት ጥፋተኛ ይሆናል?» ይላሉ። መደምደሚያው በሰዎች ፍትሕ ሚዛን ቀላል ባይሆንም፥ ይህ የጋራ ተጠያቂነት አሳብ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በግልጽ የሚገኝ ሐቅ ነው። (በመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ 1ኛ ሳሙ. 22፡15፤ 2ኛ ቆሮ. 5፡21፤ ዕብ. 7:9-10ን እንደ ምሳሌ ይመልከቱ።) ተግባራዊ ምሳሌ፦ የሌባ ወይም የነፍሰ ገዳይ ልጆች ምንም እንኳን ወላጃቸው ወንጀሉን በፈጸመበት ጊዜ ሕጻናት ቢሆኑና ስለ ወንጀሉም ምንም የማያውቁ ቢሆኑም፥ በወላጃቸው ስም ምክንያት ዕድሜ ልካቸውን በማኅበረሰቡ ዘንድ በእፍረትና በጭንቀት እንደሚኖሩ ይታወቃል። (በሌላ በኩል አንዳንድ ሰዎች ሌሎች በሠሩት መልካም ሥራ ሲጠቀሙና የማይገባቸውን ነገር ሲያገኙ ይታያል፤ ለምሳሌ ያህል ገና ያልተወለዱ ልጆች እንኳ ስለ ወላጆቻቸው የውርስ ጉዳይ በፍርድ ቤት በሚሰጡ ውሳኔዎች ምክንያት ብዙ ጊዜ በነጻ ጥቅም ያገኛሉ።) በኃጢአት የመበከልና የመቆጠር አሳብ በመጽሐፍ ቅዱስ የተረጋገጠ ሲሆን፥ ከዚህ ጋር ሰው በግሉ የሚሠራው ኃጢአትና የተፈጥሮ ደካማነቱ (እነዚህ ሦስቱ) አንድ ላይ ተዳምረው ነው እግዚአብሔር በሰዎች ኃጢአት ላይ በጽድቅ እንዲፈርድ ምክንያት የሚሆኑት። ኃጢአትና ክርስቲያን ፩. የኃጢአት እርግጠኛነት (የማያቋርጥ ውጊያ) ክርስቲያን መሆን አንድን ሰው ኃጢአት ፈጽሞ ከመሥራት ነጻ አያደርገውም። እርግጥ በምድራዊ ሕይወትም ቢሆን ክርስቲያን ከኃጢአት ባሕርይ ሙሉ በሙሉ የነጻ ሊሆን ይችላል (Sinless Perfection) ብለው የሚያስተምሩ አሉ። የአዲስ ኪዳን ትምህርት ግን ከዚህ የተለየ ነው። ለማስረጃም ያህል ሐዋርያው ዮሐንስ በእርሱ ዘመን የነበሩ ሰዎች በሐሰት የሚናገሯቸው ሦስት ነገሮች እንዳሉ በ1ኛ ዮሐንስ 1፡8-10 አረጋግጧል፦ ፪. የአማኝ ግዴታዎች (በብርሃን መመላለስ) የአማኝ ዋና ግዴታው “በብርሃን መመላለስ” ነው (1ኛ ዮሐ. 1፡7)። ከእግዚአብሔር ጋር እውነተኛ ኅብረት የሚገኘው ይህ መለኮታዊ ብርሃን መልካምንና ክፉውን እንዲገልጥ በጸሎት በመማለድና ለዚህ ብርሃን ሳያቋርጡ ታዛዥ በመሆን ነው። ክርስቲያን በዚህ ምድራዊ አካል እስካለ ድረስ ራሱ የብርሃን ምንጭ መሆን አይችልም፤ ነገር ግን በብርሃን ውስጥ መመላለስ መቻል ይኖርበታል። ይህን ሲያደርግ ሁለት ነገሮች ይከናወናሉ፦ በመጀመሪያ ከሌሎች አማኞች ጋር እውነተኛ ኅብረት ይኖረዋል፥ ሁለተኛ በደሙ ይነጻል። ይህ መንጻት በብርሃን የመመላለሱ ቀጣይነት ያለው ውበት እንጂ፥ የደረቀ ሥርዓታዊ ኑዛዜ ውጤት ብቻ ሊሆን አይችልም። በሌላ አነጋገር በብርሃን መመላለሳችን ድካምና ኃጢአታችንን ይበልጥ ስለሚያሳየን የማያቋርጥ መንጻት እንፈልጋለን። ይህ የሚገኘው ደግሞ በክርስቶስ መስቀል ሞት በኩል ነው። በብርሃን መመላለስ የሚያሰናክሉንን የሕይወት ጨለማ ጎኖች በመገንዘብ ወዲያው ንስሐ እንድንገባ ያደርገናል። በዚህ ብርሃን በበለጠ መመላለሳችንም በርቀት ያለውን ጨለማ በማስወገድ፥ ከበፊቱ የበለጠ መለኮታዊ ብርሃን ያስገኝልናል። ፫. የኃጢአት መከላከያ ምንጊዜም ቢሆን በበሽታ ከመለከፍ አስቀድሞ መከላከያ ክትባት መውሰድ ይመረጣል። እግዚአብሔርም ለአማኞች የኃጢአት መከላከያ መንገዶችን አዘጋጅቷል፦ ፬. የኃጢአት ቅጣት ፭. የኃጢአት መፍትሔ (ኑዛዜና ንስሐ) ማንኛውም ጊዜ ኃጢአት ማድረጋችን ሲታወቀን በፈቃዳችን ለመናዘዝ የተዘጋጀን መሆን አለብን። በግሪክ “መናዘዝ” (Homologeo) የሚለው ቃል “አንድን ቃል አብሮ መልሶ መናገር” ወይም “መስማማት” ያመለክታል። አማኝ ኃጢአቱን ሲናዘዝ፥ እግዚአብሔር ስለዚያ ኃጢአት በተናገረው ፍርድ ላይ በሙሉ ልብ መስማማቱ ነው፤ ያለፈ ስሕተቱንና ጥፋቱን መገንዘቡን ያሳያል (1ኛ ዮሐ. 1፡9)። መናዘዝ ፈጣን ይቅርታ ለማግኘት ብቻ የሚደረግ ከንፈር የማንቀሳቀስ ማነብነብ አይደለም። እውነተኛ ንስሐ መግባት ኑዛዜንና ኃጢአትን ፍጹም የመተው ጽኑ መሻትን ያጠቃልላል (ሐዋ. 19፡18)። ይሁን እንጂ አንድ አማኝ በተናዘዘበት ኃጢአት ላይ ደግሞ ደጋግሞ ቢወድቅ፥ ይህ ሁኔታ በኑዛዜው ላይ የግድ የጎደለ ነገር መኖሩን አያመለክትም፤ ምናልባት ከንስሐ በኋላ የተወሰዱት ተግባራዊ እርምጃዎች በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ላይ ያልተደገፉ በመሆኑ ሊሆን ይችላል። በኃጢአት ምክንያት የተቋረጠው የእግዚአብሔር የቅርብ ኅብረት፥ በንስሐ ጊዜ ተመልሶ ይመሠረታል። ኃጢአት አንድን እውነተኛ አማኝ ከእግዚአብሔር ቤተሰብ አባልነቱ ፈጽሞ አይሰርዘውም (ልጅነቱ አይጠፋም)፤ ነገር ግን የቤተሰቡን ሙሉ ሰላምና ደስታ ተካፋይ እንዳይሆን ያግደዋል። መናዘዝ ግንኙነቱን ያድሰዋል። በዚህ መለኮታዊ ቤተሰብ ውስጥ ያለው ዘላለማዊ ድነት ጨርሶ ሊበላሽ አይችልም። ነገር ግን በኃጢአት ምክንያት የዕለት ተዕለት ደስታው ሊቋረጥ ይችላል። የአንድ ሰው ኃጢአት ሌሎቹን የቤተሰብ አባላትም ሊጎዳ ስለሚችል፥ ግንኙነቶቹን ለማስተካከል ተገቢው እርምጃ ሊወሰድ ይገባል። ኃጢአት እጅግ ከባድ ነገር ነው፤ እግዚአብሔርን ያሳዝናል፥ ሌሎችንና እኛንም ይጎዳል። ምንጭ፦ “የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ-ትምህርት ጥናት”፣ በዶክተር ቻርልስ ሲ. ራይሪ ተጽፎ፥ በሲሳይ ደሳለኝ የተተረጎመ እና በየላፕስሊ/ብሩክስ ፋውንዴሽን የታተመ ነው። ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው። ይህን ጽሑፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሑፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው።

የሰው ኃጢአት Read More »

የሰው ልጅ ውድቀትና የታሪክ መለወጥ (ዘፍጥረት 3)

«ኃጢአት ለምን ከእግዚአብሔር ዕቅድ ውስጥ ገባ?» የሚለው ጥያቄ ሰው በቀላሉ ሊመልሰው የማይችለው ምስጢር ነው። ሆኖም በምን አኳኋን ኃጢአት በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ እንደገባ በመጽሐፍ ቅዱስ ዘፍጥረት ምዕራፍ 3 ላይ በግልጽ ተዘግቧል። ይህን ምዕራፍ የይዘቱን ታሪካዊነት «ተረት፥ እውነተኛ ተረት፥ აፈ-ታሪክ፥ የተቀደሰ አፈ-ታሪክ» ወዘተ. እያሉ የሚክዱ ብዙ ነቃፊዎች አሉ። ይሁን እንጂ ታሪካዊ ያልሆነ ነገር ግን “እውነተኛ” ባሕርይ እንዳለው አድርገው አጥብቀው ይይዛሉ (ይህም መጨረሻው ውሸት የሆነ ታሪክ ማለት ነው)። እንዲህ ያለውን የተዛባ ሥነ-መለኮታዊ አመለካከት የሚያሳይ አንድ ምሳሌ እነሆ፦ «ጠንካራ ወግ አጥባቂዎች ካልሆንን በዘፍጥረት 3 ላይ የተጻፈውን ታሪክ “እውነተኛ አፈ-ታሪክ” ነው እንላለን። ይህም ማለት ኤደን በካርታ ላይ ባትገኝም፥ እንዲሁም የአዳም እውቀት ከሰው ልጅ የታሪክ ቀመር ወይም መዘክር ጋር ባይታረቅም፥ ምዕራፉ ልክ በሰው ልጅ የታሪክ ጅማሬ ወቅት እንደነበረው ሁሉ ዛሬ ያለውን የሰው ልጅ የኑሮ ልምድ ስፋት ያሳያል ማለት ነው። በቀላል ቋንቋ ለመናገር፥ እኛ የወደቅን ፍጡሮች ነን፤ የአዳምና የሔዋን ታሪክም የእኔና የእናንተ ታሪክ ነው።» ይህ አባባል በዚህ መልኩ ይቅረብ እንጂ፥ የታሪኩን መዋቅር፥ ዝርዝር ሁኔታውንና ተከታታይ ጥቅሶቹን ልብ ብሎ ያጤነ ሰው ታሪኩ ፍጹም እውነታ እንዳለው ይረዳል። (ማቴ. 19:3-6 እና ሮሜ 5:12-21፤ እንደዚሁም ሉቃስ 3:38 እና ይሁዳ 14 አዳም ማለት ጠቅላላ የሰው ዘር ማለት ሳይሆን፥ አንድ የተወሰነ ግለሰብ መሆኑን ነው የሚያመለክቱት።) ፈተናው አዳምና ሔዋን የተፈተኑበት ሁኔታ ታላቅ ትርጉም ያለው ሲሆን፥ በአንጻሩ ደግሞ ቀላል ነው። ቀላልነቱም በኤደን ገነት ካሉት እጅግ ብዙ ፍሬዎች መካከል አንዱን ብቻ ከመከልከላቸው አንጻር ሲታይ ነው። ክፉን ነገር በሙከራ እንዳያውቁ መከልከላቸው የእግዚአብሔር በረከት እንጂ፥ የሕይወታቸው ጉድለት አይደለም። በሌላ አቅጣጫ ስንመለከተው ግን እገዳው የሞት ወይም የሕይወት ጉዳይ ነውና ታላቅ ጠቀሜታ ነበረው። ትእዛዙን ማክበር ወይም መጣስ፥ ለእግዚአብሔር ፈቃድ መገዛትን ወይም አለመገዛትን (መዛትን) የሚያሳይ ነበር። (እርግጥ አዳምና ሔዋን ሌላም ኃላፊነት ነበረባቸው፤ ለምሳሌ የኤደን ገነትን መንከባከብ።) በኋላ በግልጽ እንደሚታየው ክፉውንና መልካሙን የምታስታውቀው ዛፍ እውነተኛ ዛፍ ስትሆን፥ እግዚአብሔር ይህንኑ እውቀት እንድታስተላልፍ መሣሪያ ያደረጋት ነበረች። የፈተናው ሂደት የሰይጣን ጥቃት በማባበል የተጀመረው በዘፍጥረት 3፡1 ላይ ነው። እግዚአብሔር አንዳች ነገር እስካልነፈጋቸው ድረስ ለእነርሱ መልካም አለመሆኑን ሔዋን እንድታምን ማድረግ ነበር የሰይጣን ዋና ሙከራ። ቁጥር 2 ላይ እንደተገለጠው የእርሷ መልስም እግዚአብሔር ሁሉን እንደፈቀደላቸውና አንድ ነገር መከልከሉ ቀላልና የማይጎዳቸው መሆኑን የሚገልጽ ነበር። የሰይጣን ሥራ ሔዋን በእግዚአብሔር ቅር እንድትሰኝ ማድረግ ነበርና ማታለያው እንዲህ የሚል ነበር፦ “እግዚአብሔር መልካም ቢሆንማ አንዳችም ነገር አይከለከላችሁም ነበር። ነገር ግን የዚህን ዛፍ ፍሬ እንዳትበሉ ከልክሏልና መልካም ሊሆን አይችልም። በተቃራኒው የእኔ ዕቅድ እግዚአብሔር የከለከላችሁን ሁሉ እንድታደርጉ ይፈቅድላችኋል።” የዚህ አሳብ መንደርደሪያ ነጥብ፥ የምክንያት አደራደር ቅደም-ተከተልን የተከተለ ነበር። ሔዋንም ልትፈጽመው ስለወሰነችው ስሕተት ራሷን በራሷ ትክክለኛ ለማድረግ ምክንያቶቿን በሕሊናዋ ደረደረች። የተከለከለውን ፍሬ በመመልከት፥ ለምግብነት መልካም ነው ብላ አሰበች። ደግሞም እግዚአብሔር ጣፋጭና የተለያየ ምግብ ለእነርሱ የማዘጋጀት ኃላፊነት እንደጣለባት በማስታወስ፥ ይህን መልካም ፍሬ መመገብ በምን አኳኋን ስሕተት ይሆናል ብላ አመነች። ስለ ፍሬውም ማማርና የእውቀት ምንጭነት የተለመደ ምክንያቷን አቀረበች። እግዚአብሔር ያን ፍሬ እንዳይበሉ የመከልከሉ እውነት ከአእምሮዋ ጠፋ። ድርጊቱን መልካም ለማስመሰል በምታደርገው ጥረት የተነሳ አእምሮዋ በምክንያቶች የተሞላ ስለነበር፥ እሱና አዳም የእግዚአብሔርን ፈቃድ በግልጽ በመጣስ ከፍሬው በሉ። የኃጢአታቸው ውጤቶች በዚህ ኃጢአት የተነሳ ቀጥሎ ያሉት መለኮታዊ ፍርዶችና ሁኔታዎች ተከሰቱ፦ ምንጭ፦ “የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ-ትምህርት ጥናት”፣ በዶክተር ቻርልስ ሲ. ራይሪ ተጽፎ፥ በሲሳይ ደሳለኝ የተተረጎመ እና በየላፕስሊ/ብሩክስ ፋውንዴሽን የታተመ ነው። ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው። ይህን ጽሑፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሑፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው።

የሰው ልጅ ውድቀትና የታሪክ መለወጥ (ዘፍጥረት 3) Read More »

የሰው ተፈጥሮ፡- የሰው ባሕርይ

«ሰው ምንድ ነው?» የሚለው ጥያቄ ያለጥርጥር እጅግ መሠረታዊ የሆነ የፍልስፍናና የሥነ-መለኮት ተግባራዊ ጥያቄ ነው። ሰዎች መጀመሪያ ከየት መጣን? ለምንስ መጣን? መሄጃችንስ ወዴት ይሆናል? የሚሉና ሌሎችም ተመሳሳይ ጥያቄዎች ናቸው። ፍልስፍና እነዚህን ጥያቄዎች ለማጥናትና መልስ ለማግኘት በየዘመናቱ በተነሱ ፈላስፋዎቹ አማካይነት የተለያዩ ሙከራዎችን አድርጓል። የብዙዎቹን ፍልስፍናዎች የአጠናን ዘዴና መልሶቻቸውን ስናይ፥ ሰዎች ለነዚህ ጥያቄዎች እርግጠኛ መልስ ለማግኘት አለመቻላቸውን እንረዳለን። ፍልስፍና ሰዎች ስለ ሰው ያሰቡትን ሊያስተምረን ሲጥር፥ መጽሐፍ ቅዱስ ግን የሰውን አፈጣጠር በማስመልከት በሥልጣን የተደገፈና የተሟላ ትምህርት ይሰጠናል። ለሌሎች መሠረታዊ ጥያቄዎችም አጥጋቢ መልስ አለው። 1. ሰው ፍጡር ነው አንድ ሰው ስለ ሰው ዘር አመጣጥ ያለው አመለካከት ስለ ሰብአዊ ፍጡር የሚኖረውን እውቀትና አስተሳሰብ ይወስነዋል። ለምሳሌ ሰው በአዝጋሚ ለውጥ (Evolution) የመጣ ነው ብሎ ካመነ፥ የኃጢአትን አስከፊነትና የአዳኝን አስፈላጊነት ሙሉ በሙሉ ባይሰርዘው እንኳን እጅግ አቃልሎ ይመለከተዋል። በሌላ በኩል ሰው በአምላክ የተፈጠረ ነው ብሎ የሚያምን ከሆነ፥ ይህ ፅንሰ-አሳብ ሰው ኃላፊነት አለበት የሚለውን የተያያዘ አሳብ ይይዛል። ሰው በእግዚአብሔር ከተፈጠረ፥ በፈጣሪና በፍጡሩ መካከል የበላይና የበታች ግንኙነት አለ ማለት ነው። ይህ ከሆነ እንግዲህ ሰው የራሱን ዕድል በራሱ የሚወስን አይሆንም፤ ወይም ለራሱ ተጠያቂ የሆነ የመጨረሻ ባለሥልጣንም ለመሆን አይችልም። ፍጡራን በፈጣሪያቸው ተገዢ መሆናቸውን ነው የሥነ-ፍጥረት ትምህርት የሚያመለክተው። ነገር ግን ሰው ከዝቅተኛ የሕይወት አካል በአዝጋሚ ለውጥ ከተገኘ፥ ፈጣሪ ሊጠየቅበት አይችልም ማለት ነው። የአዝጋሚ ለውጥ ትምህርት በየደረጃው በሰፊው የሚሰጥ ስለሆነ፥ በዚህ ክፍል ስለዚህ ፅንሰ-አሳብ ጥቂት አስተያየት መሰንዘሩ ብቻ በቂ ይሆናል። ይህ ፅንሰ-አሳብ ፍጥረት ሁሉ ከመጀመሪያይቱ “ሕዋስ” ቀስ በቀስ በተፈጥሮ ሂደት የተገኘ ነው ቢልም፥ የመጀመሪያዋ ሕዋስ ከየት እንደመጣች ግን አያመለክትም። በተወሰነ ደረጃ አንዳንድ ለውጦች መኖራቸውን ማንኛውም ክርስቲያን አይክድም። ነገር ግን የአዝጋሚ ለውጥ ፅንሰ-አሳብ ከዚህም የገዘፉ የለውጥ ትምህርቶችን ያካትታል። የቅርጽ፥ የዘርና ሌሎች ውስጣዊና ረቂቅ ለውጦች ሁሉ ያለ ፈጣሪ ተሳትፎ ይፈጸማሉ ብሎ ያስተምራል። እንዴት ነው ይህ መሆን የሚችለው? እንደ አዝጋሚ ለውጥ እምነት አራማጆች (Evolutionists/ኢቮሉሽኒስቶች) አባባል፥ ይህ የሚከናወነው በሚውቴሽን (Mutation) ነው። «ሚውቴሽን» ማለት በአንድ ድንገተኛ ሁኔታ የተነሳ በፍጥረታት ሕይወት መዋለድ ላይ የሚመጣ መላምታዊና ድንገታዊ ለውጥ ነው። በዚህም ረገድ ከወላጆቻቸው የተለዩ አዳዲስ ፍጡራን የሚፈጠሩ ሲሆን፥ አዲስ የሆኑት ልጆችም ራሳቸውን እንጂ አያት ቅድመ-አያቶቻቸውን የማይመስሉ ዘሮችን ይተካሉ። ጠንካራ ጠንካራዎቹ በተፈጥሮ ምርጫ እየተጠበቁ በመቆየታቸው አዲስ የዘር ዓይነት ተገኘ እንደሚሉም ማስተዋል ይጠቅማል። በሂሳብ ጥበብ ቋንቋ ቀመሩ የሚከተለውን ይመስላል፦ {ሚውቴሽን} + {የተፈጥሮ ምርጫ} + {ጊዜ} = {አዝጋሚ ለውጥ} አንድ ጸሐፊ ሲጽፍ፦ «ሜንደል (Mendel) በተባለ የለውጥ ተመራማሪ ለረዥም ጊዜ የታየው የለውጥ ሙከራ የተመሠረተው ሕያው በሆኑት ባሕርያት ላይ ብቻ እንጂ፥ አዳዲስ ባሕርያት በመፍጠር እንዳልሆነ ነው። ፍጹም የሆኑ አዳዲስ አካላት ማግኘቱን ያረጋገጠ ሙከራም የለም። ይሁን እንጂ በአዝጋሚ ለውጥ ትምህርት የዋናዎቹን የለውጥ ደረጃዎች ክልል የሚያመለክተው በፍጥረታት ውስጥ የአዳዲስ ባሕርያት መከሰት ነው» ብሏል። ይህ መልስ ያላገኘ የአዝጋሚ ለውጥ እምነት አራማጆች መሠረታዊ ችግር ነው። እነዚህ አዳዲስ ነገሮች በምንም እኳኋን ይሁን በአዝጋሚ ለውጥ ተከስተዋል ብለው ማመን አለባቸው። ለምሳሌ አንድ እውቅ የሰው ዘር አመጣጥ ተመራማሪ (Anthropologist/አንትሮፖሎጂስት) የጀርባ አጥንት ያላቸው ፍጥረታት፥ አጥንት ከሌላቸው በእድገት እንደተገኙ ሲጽፍ፦ “ይህ በጣም ውስብስብ፥ ግልጥ ያልሆነና አሻሚ ጉዳይ ነው። ያም ሆነ ይህ አጥንት የሌላቸው እንስሳት በሆነ መንገድ የጀርባ አጥንት በማግኘት በኢቮሉሽን ተለውጠዋል” ብሏል። ይህ የግል እምነቱ ቢሆንም፥ የአስተሳሰብ ድክመት ይታይበታል። የቅሪተ-አካል ዘገባም ከዚህ በፊት ሆነዋል የሚባሉ ነገሮችን ያመለክታል። አዝጋሚ ለውጥ ትክክል ቢሆን ኖሮ ለውጡ ሳይቋረጥ ከቀላል ወደ ውስብስብ የተሸጋገረበትን ሂደት ሊያመለክት ይገባ ነበር። ነገር ግን በቢሊዮን ከሚቆጠሩት የታወቁ ቅሪተ-አካላት ግኝቶችና ከፍተኛ የሕይወት ምድቦች መካከል ያለው ሽግግር ሆነ ተብሎ ተዘሏል! “አገናኞቹ ቀለበቶችም ከሚፈለጉበት ስፍራ ጠፍተዋል፤ ምናልባት ወደፊትም ብዙ አገናኝ ቀለበቶች ይጠፉ ይሆናል” በማለት አንድ ጸሐፊ ተናግረዋል። 2. መጽሐፍ ቅዱሳዊ የሰው አፈጣጠር ማስረጃዎች መጽሐፍ ቅዱስ የሰውን አፈጣጠር አስመልክቶ በዝርዝር ስላሰፈረው ጉዳይ የተለያዩ አስተሳሰቦች ቢኖሩም፥ እውነተኛዎቹ ማስረጃዎች ግን በዚሁ መጽሐፍ ውስጥ ነው በግልጥ የሚገኙት። ዋና ዋናዎቹም ማስረጃዎች የሚከተሉት ናቸው፦ 3. ሰው ባለ ብዙ ገጽ ፍጡር ነው በመሠረቱ ሰው ቁሳዊ (አካል) እና ቁሳዊ ያልሆነ (መንፈስ ወይም ነፍስ ያለው) ፍጡር ነው። ሁለቱም አሠራሮች የእግዚአብሔር ቀጥተኛ የፈጣሪነት ሥራ ውጤቶች ናቸው (ዘፍጥ. 2፡7)። እግዚአብሔር ሰውን በመልኩና በምሳሌው ፈጠረ (ዘፍጥ. 1:26፥ 5፡1)። ሰውን እጅግ ልዩ የሚያደርገው እግዚአብሔርን መምሰሉ ሲሆን፥ በኃጢአት ከወደቀ በኋላም ቢሆን ይህ አምሳያነቱ ሙሉ በሙሉ አልጠፋም። (1ኛ ቆሮ. 11፡7 እና ያዕ. 3፡9 ላይ የሰፈሩት ምክሮች ሰው የእግዚአብሔር አምሳያ መሆኑን ያረጋግጣሉ።) ያ አምሳያነት ምንድነው? ለዚህ ጥያቄ ለዘመናት የተለያዩ መልሶች ሲሰጡ ኖረዋል። ከእነዚህም መልሶች ውስጥ የሰው የእግዚአብሔር አምሳያነቱ ከተፈጥሯዊ አካሉ ነው፥ ወይም ለሥነ-ምግባርና ለመንፈሳዊ ጉዳይ ባለው ችሎታ ነው (ችሎታው አሁንም ይኖረው ወይም ፈጽሞ ያጣው ይሆናል) የሚሉት ይገኙበታል። ምናልባት እውነቱ የብዙ ነገሮች ስብስብ በመሆኑ ይሆናል። ሰው የእግዚአብሔር አምሳል በመሆኑ ምድርን የመግዛት ሥልጣንና ሥነ-ምግባር የማስከበር ኃላፊነት ተሰጥቶታል፤ በኋላም ይህን ኃላፊነት በኃጢአት የተነሳ ተነጥቋል። ከዓለም ገዥነቱ ተሽሯል፥ በሥነ-ምግባሩም ተበላሽቷል። ያም ሆኖ ከፍጥረታት ሁሉ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረ እርሱ ብቻ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል። የሰው አካል (ቁሳዊው ክፍሉ) በጣም ብዙ ሥራ እንደሚያከናውን ግልጥ ነው። ማየት እንደ መስማት አይደለም። የስሜት ሥሮች አሠራር የተለያየና ራሱን የቻለ ቢሆንም፥ ከማየት፥ ከመስማትና ከሌሎችም ስሜቶች ጋር የሚያያዝበት መንገድ ይኖራል። ቁሳዊ ያልሆነውንም የሰው ክፍል በዚህ ሁኔታ ማየቱ ምናልባት አስፈላጊ ይሆናል። ነፍስ፥ መንፈስ፥ ልብ፥ አእምሮ፥ ፈቃድና ሕሊና ቁሳዊ ያልሆኑ የሰው አካል ክፍሎች ሲሆኑ፥ በመካከላቸው ጥርት ያለ ልዩነት መፍጠሩ ያስቸግራል። ሰውን አካል፥ ነፍስና መንፈስ ነው ማለት በጣም ማቃለል ይመስላል። ምክንያቱም ነፍስና መንፈስ የሰውን ቁሳዊ ያልሆነ ክፍል በሙሉ ካለመግለጣቸውም በላይ ልዩነታቸው ሁልጊዜ ጉልህ ባለመሆኑ ነው። “ልብ” (ደም የሚረጨውን የውስጥ አካል ማለት አይደለም) እንዲሁ የሰውን ቁሳዊ ያልሆነ ክፍል ሁሉ የሚያጠቃልል ይመስላል። የሰው ሕይወት የእውቀት ማኅደር እንደሆነም ተገልጧል (ማቴ. 15፡19-20)፤ ስሜታዊውን ሕይወት (መዝ. 37፡4፤ ሮሜ 9፡2)፥ ፈቃዳዊውን ሕይወት (ዘዳግ. 7፡23፥ ዕብ. 4፡7)፥ መንፈሳዊውን ሕይወት (ሮሜ 10፡9-10፤ ኤፌ. 3፡17) ሁሉ ያጠቃልላል። ሕሊና በሰው ውድቀት የተጎዳ አካል ቢሆንም፥ አማኞችንም ሆነ የማያምኑትን ሰዎች ሊመራ የሚችል ውስጣዊ ምስክር ነው። ሮሜ 2፡15 እና 1ኛ ጢሞ. 4፡2ን በመመልከት በማያምኑት ሰዎች ውስጥ የሚታየውን ሕሊና ያስተውሉ። አማኙን በተመለከተ ግን ሕሊናው ከመንግሥት (ሮሜ 13፡5)፥ ከአሠሪው (1ኛ ጴጥ. 2:19)፥ ከወንድሞቹ (1ኛ ቆሮ. 8:7፥ 10፥ 12) ጋር መልካም ግንኙነት እንዲኖረው ይመራዋል። በጌታ ደኅንነት ያላገኘ ሰው አእምሮ በአዲስ ኪዳን ውስጥ መልካም ያልሆነ ስም ተሰጥቶታል። የማይረባ (ሮሜ 1:28)፥ ከንቱ (ኤፌ. 4:17)፥ የረከሰ (ቲቶ 1:15)፥ የጨለመ (ኤፌ. 4:18)፥ በሰይጣን የታወረ (2ኛ ቆሮ. 4:4) ተብሏል። ይሁን እንጂ አንድ ሰው ክርስቶስን አዳኝ አድርጎ ሲቀበል፥ ሕይወቱንም ለጌታ ሲሰጥ የአእምሮ መታደስን ያገኛል (ሮሜ 12፡2)። ከዚያ በኋላ እግዚአብሔርን መውደድ እንችላለን (ማቴ. 22፡37)፤ የጌታን ፈቃድ እንረዳለን (ኤፌ. 5፡17)፤ በማስተዋል እናመሰግነዋለን (1ኛ ቆሮ. 14:15)። የሰው ፈቃድ ሌላው በጣም ጠቃሚ የሆነና ቁሳዊ ያልሆነው የተፈጥሮ ክፍል ነው። ያልዳነ ሰው ፈቃድ መልካም ውጤት ይኖረው ይሆናል (ሐዋ. 27፡43)፤ የአማኞችም እንዲሁ ሊሆን ይችላል (ቲቶ 3፡8)፤ የዚህ ተቃራኒም ይሆን ይሆናል (1ኛ ጢሞ. 6:9፤ ያዕ. 4:4)። እነዚህ ሁሉ ማብራሪያዎች ክርስቲያን ሁለት የተለያዩ ችሎታዎች ወይም ባሕርያት እንዳሉት ያመለክታሉ። ከመዳኑ በፊት ችሎታውን የሚጠቀምበት ራሱን ለማገልገልና ለማስደሰት ነው። ይህ አሮጌ ወይም የኃጢአት ባሕርይ ክፉ ለማድረግ ከመቻል አንጻር ብቻ አይደለም የሚተረጎመው፤ ከዚያ የላቀ ሊሆን ይችላል። ከአሮጌው ባሕርይ የመነጩ፥ ግን ያልከፉ ነገሮች አሉ። የአሮጌው ባሕርይ ዋና መለያ በድርጊቱ

የሰው ተፈጥሮ፡- የሰው ባሕርይ Read More »